top of page

ኢትዮጵያ ባለፈው አመት ከካርበን ሽያጭ 4.8 ሚሊየን ዶላር ገቢ አገኘች፡፡

  • 1 day ago
  • 1 min read

ሐምሌ 22 2018


ኢትዮጵያ ባለፈው አመት ከካርበን ሽያጭ 4.8 ሚሊየን ዶላር ገቢ አገኘች፡፡



በአራት ዓመታት ውስጥ ከ140 ሺህ ቶን በላይ የካርበን ጋዝ ልቀት መቀነሱ ተሰምቷል፡፡


ይህ ገቢ የተገኘውም ከ2013-2017 ዓ.ም በተተገበረ የታዳሽ ሀይል ፕሮጀክቶች መሆኑም ተነግሯል።


ይህንን የነገሩን በፕላንና ልማት ሚኒስቴር የአየር ንብረት ለውጥ አማካሪና የካርበን ገበያ አስተባባሪ አቶ መንሱር ደሴ ናቸው።


ኢትዮጵያ ላለፉት አራት አመታት በተገበረቻቸው የባዮጋዝና የፀሐይ ሃይል ፕሮጀክቶች ኢትዮጵያ ገቢ እንድታገኝበት ከማድረግ ባሻገር የሀይል አቅርቦት የማያገኘው ህብረተሰብም ተጠቃሚ እንዲሆን አስችሏል ብለዋል።


ወደ አየር ሊለቀቅ የነበረውን የሙቀት አማቂ ጋዝ እንዲቀንስ ማድረጉም ሌላኛው ውጤት ነው ይላሉ።


በባዮጋዝ እና በፀሐይ ሃይል ላይ የተሰሩ ፕሮጀክቶች ከጤና አኳያም የራሱን አውንታዊ ሚና እንዳበረከተም አቶ መንሱር ነግረውናል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ...




ፍቅሩ አምባቸው

Recent Posts

See All
የሐምሌ 23 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ግብፅ በግብፅ የሜዴትራኒያን የባህር ዳርቻ የነበረ የአሜሪካ የጋዝ ማጠራቀሚያ መርከብ በድሮን ተመታ ተባለ፡፡ ሁለት የደህንነት ምንጮች መርከቡ በድሮን እንደተመታ አረጋግጠውልኛል ሲል ሬውተርስ ፅፏል፡፡ መርከቡ በድሮን እንደተመታ በእሳት መያያዙ ታውቋል፡፡ ቃጠሎው ወደ ሌላ መርከብም ተጋብቶ ነበር ተብሏል፡፡ ኋላ ግን

 
 
 
የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ማሳደግ፣አፍሪካዊያን የጋራ መጪ እድላቸውን እንዲቀርፁ ማገዝ ያስፈልጋል ተባለ።

ሐምሌ 23 2018 የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ማሳደግ፣አፍሪካዊያን የጋራ መጪ እድላቸውን እንዲቀርፁ ማገዝ ያስፈልጋል ተባለ። የአፍሪካ ሀገሮች እርስ በእርስ፣በአፍሪካና በሩሲያ እንዲሁም አፍሪካ ከተቀረው ዓለም ጋር ያላትን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ማሳደግን ዓለማው ያደረገ ዓለም አቀፍ ጉባኤ በተባበሩት መንግስታት የአ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page