top of page


ምርትና አገልግሎት ያላቸውን፣ ሸማቹንና አሻሻጭን የሚያገናኝ የሞባይል መተግበሪያ በይፉ ስራ መጀመሩ ተነገረ።
ታህሳስ 18/2018 ምርትና አገልግሎት ያላቸውን፣ ሸማቹንና አሻሻጭን የሚያገናኝ የሞባይል መተግበሪያ በይፉ ስራ መጀመሩ ተነገረ። መተግበሪያው "ዳንቴል" ይባላል። በዳንቴል ሶፍትዌር የተዘጋጀው "ዳንቴል" የሞባይል መተግበሪያ አምራቾች ምርታቸውን፣ አገልገሎት አቅራቢዎች ያላቸውን አገልግሎት ሙሉ መረጃ የሚያስቀምጡበት፣ መረጃውን ደግሞ በየራሳቸው የማህበራዊ ትስስር ገፆች የሚያጋሩና ሽያጭ እንዲከናወን የሚያደረጉ ደግሞ የኮሚሽን ክፍያ እንዲያገኙ የሚያስችል ስርዓት ይዞ የመጣ ነው። ይህም ለሸማቹ ገበያ ወጥቼ የት ምን አገኛለሁ የሚለውን የሚያቀልል፣ ለአምራቹም ሰፊ የገበያ እድል የሚፈጥር፣ በተለይ በሽያጭ ስራ ገቢ ለማግኘት ለሚፈልጉ ስልካቸውን ተጠቅመው ገቢ እንዲያገኙ የሚያስች እንደሆነ የድርጅቱ ሀላፊዎች በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል። መተግበ
Dec 27, 20251 min read


እስራኤል ለሶማሌላንድ ይፋዊ የነፃ አገርነት እውቅና መስጠቷ ሶማሊያን በእጅጉ አስቆጣት፡፡
ታህሳስ 18/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #እስራኤል እስራኤል ለሶማሌላንድ ይፋዊ የነፃ አገርነት እውቅና መስጠቷ ሶማሊያን በእጅጉ አስቆጣት፡፡ ሞቃዲሾ የእስራኤልን እርምጃ አጥብቃ ማውገዟን ዘ ኒው አረብ ፅፏል፡፡ ከሶማሊያ በተጓዳኝ ግብፅ ፣ ቱርክ እና ጂቡቲም እስራኤል ለሶማሌላንድ የነፃ አገርነት እውቅና መስጠቷን ኮንነውታል ተብሏል፡፡ አገሮቹ የሶማሊያ ሉአላዊነት እና የግዛት አንድነት እንዲከበር ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉ እወቁልን ብለዋል፡፡ ሶማሌላንድ ራሷን ከተቀረችው ሶማሊያ ከነጠለች 34 ዓመታት ሆኗታል፡፡ አለም አቀፋዊ እውቅና ባይኖራትም ከሶማሊያ በተሻለ የተረጋጋች እንደሆነች ይነገርላታል፡፡ በነፃ አገርነት ይፋዊ እውቅና ስታገኝ የእስራኤል የመጀመሪያው ሆኗል፡፡ ሶማሊያ እና አጋሮቿ ሌሎችም የእስራኤልን ፈለግ እንዳይከተሉ መስጋታቸው ተጠቅሷል፡፡
Dec 27, 20252 min read


በዚህ ዓመት ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ በትግራይ ማካሄድ ካልተቻለ በክልሉ ያለው ቀውስ ሊባባስ እንደሚችል የፖለቲካ ፓርቲዎች ተናገሩ፡፡
ታህሳስ 17/2018 በዚህ ዓመት ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ በትግራይ ማካሄድ ካልተቻለ በክልሉ ያለው ቀውስ ሊባባስ እንደሚችል የፖለቲካ ፓርቲዎች ተናገሩ፡፡ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እንዳሉት በትግራይ ክልል ያለውን የመብት ጥሰት እና መሰል ችግሮችን ለመፍታት በህዝብ የተመረጠ መንግስት ያስፈልጋል፡፡ ለምርጫ አስቻይ ሁኔታ አለ ወይስ የለም የሚለውን በተመለከተ ጊዜያዊ አስተዳደር በቅርቡ መግለጫ እሰጣለሁ ብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio
Dec 26, 20251 min read
የህፃናትን መብት ለማስጠበቅ
ታህሳስ 17/2018 የህፃናትን መብት ለማስጠበቅና ለመብት ጥሰት በተጋለጡ ጊዜም የሚያስፈልጋቸውን እገዛ እንዲያደርግ መንግስት በፈረማቸው አለም አቀፍ ስምምነቶች የሚገደድ ቢሆንም በበቂ ሁኔታ ሃላፊነቱን እየተወጣ አይደለም ተብሏል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከግጭቶችም ጋር ተያይዞ በብዛት ህፃናት ለተለያየ የመብት ጥሰቶች እየደረሰባቸው መሆኑ ይነገራል፡፡ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩል ህፃናት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከል እና ፍትህ እንዲያገኙ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ነግሮናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ፋሲካ ሙሉወርቅ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhc
Dec 26, 20251 min read


የኢትዮዽያ የሎጅስቲክስ ስርዓት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና
ታህሳስ 17/2018 የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የሀገራትን የምርት ልውውጥ ለማሳደግ ኢኮኖሚያቸውን ይደግፋል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ ኢትዮዽያም በዚሁ መስመር ወደ ቀጠናው የንግድ እና ጭነት ስራ ጀምራለች። ሆኖም የሎጀቲክስ ስራውም ጎን ለጎን ሊሰራበት እንደሚገባ ይመከራል። ኢትዮጵያ ከ 90 በመቶ በላይ ጭነቶችን በመኪና ታጓጉዛለች፡፡ በቀጠናው ሀገራት ጋር የሚኖራትን የንግድ ግንኙነት በባቡር እና በሌሎች መንገዶች ብታቀላጥፍ ደግሞ ሎጀስቲክሱ ይበልጥ ውጤት ያመጣል። ገቢ ወጭ እቃዎችን ከአንድ ላኪ ሐገር ወደ ኢትዮዽያ በባሕር፣ በአየር፣ በመሬት ወይም በባቡር ማቀላጠፍ የሎጀስቲክስ ዋና ዋና ስራዎችን ያቀላል። በተለይ በኢትዮጵያ ከገቢና ወጭ ጭነት ጋር በተገናኘ ፤ የመሀል ሐገር ኢኮኖሚው የተሻለ ውጤት እንዲቆጠርበት ፤የጭነት መኪኖች የመ
Dec 26, 20251 min read


የ1997 እና የ2005 ዓ.ም የጋራ መኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን የሚቆጥቡ የማህበረሰብ ክፍሎች
ታህሳስ 16/2018 የጋራ መኖሪያ ቤት ለማግኘት ተመዝግበው የሚጠባበቁ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አሉ፡፡ እጣ ፈንታችን ምንድነው? ሲሉም ይጠይቃሉ፡፡ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በበኩሉ በተለያየ መልኩ እየተተገበሩ ባሉ ፕሮግራሞች ቤት የማግኘት እድል አላቸው ብሏል፡፡ እነዚህ የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን የሚቆጥቡ የማህበረሰብ ክፍሎች የ1997 እና የ2005 ዓ.ም መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በዚህ ጉዳይ ከዚህ ቀደም የሚመለከታቸው የሚባሉ የስራ ሀላፊዎችን መጠየቃቸውና መፍትሄ ማግኘት እንዳልቻሉም ያስረዳሉ፡፡ ነዋሪዎቹ ቁጠባቸውን እንዳላቋረጡ እና አሁን የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር እያስገነባ ከሚገኘው ቤት የማግኘት እድል ይኖረናል ወይ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ የቤቶች ልማትና አስ
Dec 25, 20251 min read


ዳሽን ባንክ በ2017 በጀት ዓመት 6.7 ቢሊየን ብር አጠቃላይ ትርፍ አግኝቻለሁ አለ።
ታህሳስ 16/2018 ዳሽን ባንክ በ2017 በጀት ዓመት 6.7 ቢሊየን ብር አጠቃላይ ትርፍ አግኝቻለሁ አለ። አጠቃላይ ሃብቴም ከ254 ቢሊየን ብር ተሻግሯል ብሏል። የባንኩ ባለ አክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ በሚሊኒየም አዳራሽ ተካሂዷል። በዚሁ ወቅት ሲነገር እንደሰማነው የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ ከ202 ቢሊየን ብር በላይ የደረሰ ሲሆን ካፒታሉም 14 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ሆኗል። በበጀቱ ዓመቱ 1 ነጥብ 12 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የውጭ ምንዛሪ ማግኘቱን የጠቀሰው ዳሽን ባንክ አጠቃላይ የብድር ክምችት መጠኑ በሂሳብ ዓመቱ 134 ቢሊየን ብር መድረሱን አክሏል። አመቱ በአለም አቀፍ ደረጃ ተለዋዋጭ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የታየበት እንደነበር የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር አቶ ዱላ መኮንን ተናግረዋል። ዳሽን ባንክ ግን በኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን
Dec 25, 20251 min read


የከተሞች መስፋፋትን ተከትሎ የመሬት አጠቃቀም ላይ የሚታዩ ክፍተቶች የአርሶአደሮች የመሬት ይዞታ መብት መጠበቅ ላይ መሰራት አለበት ተባለ።
ታህሳስ 16/2018 በኢትዮጵያ የከተሞች መስፋፋትን ተከትሎ የመሬት አጠቃቀም ላይ የሚታዩ ክፍተቶች በተለይም የአርሶአደሮች የመሬት ይዞታ መብት መጠበቅ ላይ መሰራት አለበት ተባለ። ከመሬት አስተዳደር ጋር በተገናኘ ዘመናዊ አሰራሮችን በመከተል አርሶአደሩን በመሬቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረግ ያስፈልጋል ተብሏል። ይህ የተባለው 3ተኛውን የኢትዮጵያ የመሬት ቀን አስመልክቶ ላንድ ፎር ላይፍ በተባለ ሀገር በቀል ተቋም በተሰናዳ የፓናል ውይይት ላይ ነው። ላንድ ፎር ላይፍ ኢትዮጵያ፣ በመሬት አስተዳደር እና ኃላፊነት የተሞላበት የግብርና ኢንቨስትመንቶች ላይ የሚሰራ ድርጅት ነው ተብሏል። ምክክሩ የኢትዮጵያ የመሬት አስተዳደር ተቋማዊ እና የሕግ ማዕቀፎች ወቅታዊ ሁኔታዎች ፣ በፖሊሲ ጉዳዮች፣ የከተማ መሬት አስተዳደር ፣ ኃላፊነት በተሞላበት የግብርና ኢንቨስትመ
Dec 25, 20251 min read


የኢትዮዽያን የቴሌኮም ኢንዱስትሪ ሁለተኛ አቅራቢ ሆኖ የተቀላቀለው ሳፋሪኮም ኢትዮዽያ የታሪፍ ማሻሻያ ማድረጉ ተሰማ።
ታህሳስ 15/2018 የኢትዮዽያን የቴሌኮም ኢንዱስትሪ ሁለተኛ አቅራቢ ሆኖ የተቀላቀለው ሳፋሪኮም ኢትዮዽያ የታሪፍ ማሻሻያ ማድረጉ ተሰማ። ሳፊሪኮም ኢትዮዽያ ለደንበኞቹ የዋጋ ማሻሻያ ወይም የአገልግሎት ጭማሪ ማድረጉንም ከኦፕሬተሩ ሰምተናል። ጭማሪ ተደርጎበታል የተባለው የዳታ ጥቅል አገልግሎት ላይ ነው። ሳፋሪኮም ኢትዮዽያ ይህንን ጭማሪ ያደረገው የኢንቨስትመንት እና የኦፕሬሽናል ወጪዎች ከፍ ማለታቸውን ተከትሎ እንደሆነ ሰምተናል። ኩባንያው ለጊዜው ጭማሪ ያደረገበት የዳታ ጥቅል አገልግሎት ዋጋ ምን ያህል እንደሆነ አልጠቀሰም። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል ኢንተርኔት እያቀረበ ያለው ካወጣው ዋጋ ከእጥፍ በላይ እየቀነሰ ወይም እየከሰረ መሆኑንን መናገሩ ይታወሳል፡፡ ኩባንያው ስራውን እያስፋፋ፣ አገልግሎቱን እያቀረበ ያለውም በባለ አክሲዮኖቼ ድጋፍ ነው ብሎ
Dec 24, 20251 min read


ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት የተደረጉ ለውጦች የታሰበላቸው አላማ አላሳኩም ተባለ፡፡
ታህሳስ 15/2018 ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት የተደረጉ ለውጦች የታሰበላቸው አላማ አላሳኩም ተባለ፡፡ ይህ የተባለው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዲጂታል ቴክኖሎጂ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አተገባበር ዙሪያ በተደረገ ውይይት ነው፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋና ትምህርት ኮሌጅ ባልደረባ የሆኑት በላይ ተፈራ(ፕ/ር) በዚህ ዙሪያ የመወያያ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡ 75 ዓመታት ባስቆጠረው የኢትዮጵ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ታሪክ ውስጥ በርካታ ለውጦች ቢደረጉም ያሰቡት ግብ ማሳካት አልቻሉም ብለዋል፡፡ ለዚህ ብዙ ምክንያቶች ቢኖሩም ዋነኞች ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል ለውጦች ሲደረጉ ከታች እስከላይ ያለው አመራር በትክክል ተረድቶ አይሰራውም፣ ወዲያው የመጣው ለውጥ ውይይት ሳይደረግበት በጥናት ሳይደገፍ ይተገበራል ይላሉ፡፡
Dec 24, 20251 min read


የጤና ስርዓቱን ለመደገፍ የ1.466 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈረመ።
ታህሳስ 14/2018 የጤና ስርዓቱን ለመደገፍ የ1.466 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈረመ። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ፣ የጤና ሚኒስሯ መቅደስ ዳባ(ዶ/ር) እና በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቭን ማሲንጋ ፈርመውታል። በስምምነቱ መሰረት በ5 ዓመት ውስጥ አሜሪካ ለኢትዮጵያ የጤና ስርዓት መደገፊያ የሚውል 1.016 ቢሊዮን ዶላር የምትሰጥ ሲሆን ኢትዮጵያ ደግሞ 450 ሚሊዮን ዶላር ትበጅታለች ተብሏል። የሚተገበረውም እ.አ.አ ከ2026 እስከ 2030 መሆኑ ተነግሯል። ኤችአይቪ ኤድስ፣ ወባ፣ ቲቢ፣ የእናቶችና ህፃናት ጤና እንዲሁም ወረርሽኝ መከላከል እና መቆጣጠር በ1.466 ቢሊዮን ዶላሩ ከሚሰሩ ስራዎች መካከል መሆናቸው ተጠቅሷል። አሜሪካ ባለፉት 20 ዓመታት በኢትዮጵያ የጤና ስርዓት መደገፊያ የሚሆን ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ መስጠቷን በፊ
Dec 23, 20251 min read


የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል።
ታህሳስ 14/2018 የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድም ወደ ኢትዮጵያ ለመጡትን ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ አቀባበል አንዳደረጉላቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ተናግሯል፡፡ ጉብኝቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል ያለውን ጥልቅ፣ ታሪካዊ እና ወንድማዊ ግንኙነት የሚያንፀባርቅ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናግረዋል። "በውይይታችን የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን በሚጠናከርበት ሁኔታ ላይ እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ ሃሳብ ተለዋውጠናል፣ ይኽም በሰላም እና መረጋጋት፣ ንግግር ብሎም በአፍሪካ መር መፍትሔዎች ላይ ያለንን የወል ጽኑ አቋም የሚያሳይ ነው" ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ጽፈዋል። በቅርብ ቀናት ኢትዮጵያን የተለያዩ ሀገራት መሪዎች የጎ
Dec 23, 20251 min read


በአየር ንብረት ለውጥ፣ ስርዓተ ምግብና ስርዓተ ፆታ ተፅዕኖ ምክንያት የሚፈጠሩ ችግሮች ለመፍታት ሶስቱንም በአንድ ላይ መስራት ይገባል ተብሏል፡፡
ታህሳስ 14/2018 በአየር ንብረት ለውጥ፣ ስርዓተ ምግብና ስርዓተ ፆታ ተፅዕኖ ምክንያት የሚፈጠሩ ችግሮች እርስ በርስ የተሳሰሩ በመሆናቸው ችግሩን ለመፍታት ሶስቱንም በአንድ ላይ መስራት ይገባል ተብሏል፡፡ በአየር ንብረት ለውጥ ችግር ምክንያት የስርዓተ ምግብ መዛባት ይከሰታል፤ በዚህ ምክንያት የሚመጣው የምግብ እጥረትና ሌላውም ችግር ይበልጡን ሴቶችና ህፃናት ላይ እንደሚበረታ ጥናት አሳይቷል፡፡ የማህበራዊ ጥናት መድረክ (ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ) በቀረበ ጥናት በአንደኛው ምክንያት የሚፈጠረው ችግር ሌላኛውን እያባባሰው ነው፤ ይሁንና ይህንን በአንድ አስተባብሮ የሚሰራ ተቋም በጣም ጥቂት መሆኑ ታይቷል ብሏል፡፡ ተቋሙ ለ1 ዓመት ከ6 ወራት ያህል ጂካን (GCAN) በተባለው ፕሮጀክት በከወነው በዚህ ጥናት ላይ ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የተባሉ 15 ተቋማት
Dec 23, 20252 min read


የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ በተለያዩ ሀገሮች ተመድበው ሲሰሩ የቆዩ 29 የሀገሪቱን አምባሳደሮች ወደ አገር ቤት አስጠሯቸው፡፡
ታህሳስ 14/2018 የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ በተለያዩ ሀገሮች ተመድበው ሲሰሩ የቆዩ 29 የሀገሪቱን አምባሳደሮች ወደ አገር ቤት አስጠሯቸው፡፡ ወደ አገር ቤት የተጠሩት አምባሳደሮቹ በአፍሪካ ፣ በእስያ ፣ በምስራቅ አውሮፓ እና በላቲን አሜሪካ አገሮች ተመድበው ሲሰሩ የቆዩ መሆኑን AOL ፅፏል፡፡ ትራምፕ በ47ኛ ፕሬዘዳንትነት ወደ ዋይት ሐውስ እንደተመለሱ በቀድሞው ፕሬዘዳንት ጆ ባይደን የአስተዳደር ዘመን ተሾመው የነበሩ በርካታ አምባሳደሮችን እንዳባረሩ መረጃው አስታውሷል፡፡ ፕሬዘዳንቱ 29 አምባሳደሮችን ላባረሩበት እርምጃ የዋይት ሐውስ ሹሞች ይሄ የተለመደ አሰራር ነው ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ ትራምፕ የአሜሪካ ትቅደም አጀንዳቸውን የሚያራምዱላቸውን መርጠው የመሾም መብታቸው የተጠበቀ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ከየሀላፊነታቸው የሚነሱት አምባሳ
Dec 23, 20251 min read


የስራ ገበያው እና የተማረ ብቁ የሰው ሀይል
ታህሳስ 14/2018 የስራ ገበያው የተማረ እና ብቁ የሰው ሀይል ለማግኘት እየተቸገረ መሆኑን በተደጋጋሚ ይነገራል። ለዚህ ደግሞ እንደ ምክንያት ከሚነሱ ችግሮች መካከል አንዱ በኢትዮጵያ ያሉ ከፍተኛ የመንግስት የትምህርት ተቋማት ሲያሰለጥኑ ገበያው በምን ዘርፍ የሰለጠነ ሰው ሀይል ያስፈልገዋል ብለው ተማሪዎቻቸውን አለማሰልጠናቸው እንደሆነ የዘርፉ ባለሙያዎች ያነሳሉ፡፡ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለመማር ሲገቡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በምን ሙያ የሰለጠነ የሰው ሀይል ያስፈልገዋል የሚለውን ሳያጠኑ ነው ቀጥታ የሚገቡት ብለዋል ያነጋገርናቸው የትምህርት ባለሙያ። ዩኒቨርሲቲዎቹም ቢሆኑ ሀገሪቱ በምን ዘርፍ ምን ያህል የሰለጠነ የሰው ሀይል ያስፈልጋታል የሚለውን ጉዳይ ትኩረት ሲሰጡበት አይስተዋልም ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የትምህርት እ
Dec 23, 20251 min read


የከተማ ልማት
ታህሳስ 13/2018 #ጉዳያችን - የከተማ ልማት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ፕላን መምህር እና ተመራማሪ የሆኑት ውብሸት ብርሃኑ(ዶ/ር) በጉዳዩ ላይ የሰጡንን ማብራሪያ ለማድመጥ…. የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1 WhatsApp : https://whatsapp.com/channel/0029VaAOnG9J3juypE0M4G1O X : https://x.com/shegerfm?s=2
Dec 22, 20251 min read


ኢትዮጵያ በኮቪድ እና በአጎአ መታገድ ምክንያት አብዛኛውን በሀገር የምታመርተውን ምርት መሸጥ አልቻለችም፡፡
ታህሳስ 13/2018 ኢትዮጵያ በኮቪድ እና በአጎአ መታገድ ምክንያት አብዛኛውን በሀገር የምታመርተውን ምርት መሸጥ አልቻለችም፡፡ ይህን ተከትሎም መንግስት አምራቾች 50 በመቶውን ለሀገር ውስጥ ፈላጊዎች እንዲሸጡት ወስኗል፡፡ ለመሆኑ እነዚህ ምርቶች በተለይ በኢ-ኮሜርስ የዲጂታል ገበያ እንዲቀርቡ የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሸን ምን ዓይነት ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ ነው? መመሪያና ህጋቸውንስ እንዴት እያሻሻሉ ነው? ለመሆኑ ኢትዮ ቴሌኮም እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በኤክስፖርት የጥራት ደረጃ የተዘጋጁ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በ'ዘመን ገበያ' ለሀገር ውስጥ ሸማቾች ለማቅረብም መጀመራቸውን ተከትሎ ቅድሚያ ምን ዓይነት ስራዎች ተፈፅመው ይሆን? በአለም የንግድ መስመር አንቱ የተባሉ የጨርቃ ጨርቅና አልባሳትን፣ የቆዳና የቆዳ ውጤ
Dec 22, 20251 min read


ባንኮች ከጡረታ መዋጮ የአገልግሎት ክፍያ በሚል መቁረጥ አይችሉም ተባለ።
ታህሳስ 13/2018 ባንኮች ከጡረታ መዋጮ የአገልግሎት ክፍያ በሚል መቁረጥ አይችሉም ተባለ። አንዳንድ ባንኮች የጡረታ ክፍያ ለተጠቃሚዎች ሲክፍሉ የአገልግሎት ክፍያ በሚል እንደሚቆርጡ ተነግሯል። የአገልግሎት ክፍያውን እየቆረጡ ያሉት ብሄራዊ ባንክ መመሪያ አውጥቷል በሚል እንደሆነ ተጠቅሷል። በ2014 የወጣው የጡረታ አዋጅ ግን ከጡረታ መዋጮ ገንዘብ ላይ ቀንሶ ለአገልግሎት ክፍያ፣ ለገንዘብ ማስተላለፊያ እያሉ መጠቀም እንደማይቻል ይደነግጋል ተብሏል። ብሄራዊ ባንክ አወጣው የተባለው መመሪያ ከአዋጁ በላይ ሊሆን ስለማይችል ግን ተግባሩ ሊቆም ይገባል ሲሉ የአስተዳደሩ የህግ ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ግርማ ሢሣይ አሳስበዋል። የግል ድርጅት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር በጡረታ አዋጁ ዙሪያ ከሚመለከታቸው ጋር በኢሊሊ ሆቴል እያካሄደ ነው። ንጋቱ ረጋሳ የ
Dec 22, 20251 min read


ዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ "ሰው ሰራሽ አስተውህሎት ለእድገት" በሚል በአፍሪካ የዲጂታል መሠረተ ልማትን ለማስፋፋት 1 ቢሊዮን ዶላር መመደቧን ይፋ አደረገች።
ታህሳስ 13/2018 ዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ "ሰው ሰራሽ አስተውህሎት (AI) ለእድገት" በሚል ተነሳሽነት በመላው አፍሪካ የዲጂታል መሠረተ ልማትን ለማስፋፋት 1 ቢሊዮን ዶላር መመደቧን ይፋ አደረገች። 1 ቢሊዮን ዶላሩ በአፍሪካ ሀገራት ለሚካሄዱ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ፕሮጀክቶችን ለማበረታታት እና በገንዘብ ለመደገፍ የሚውል ነው ተብሏል። ዋና አላማውም የዲጂታል መሠረተ ልማትን በማጎልበት፣ የመንግስት አገልግሎቶችን በማቀላጠፍ እና ምርታማነትን በማሻሻል በአህጉሪቱ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ልማትን ለማበርታት መሆኑ ተጠቅሷል። የዩናይትድ አረብ ኢምሬትስን ይህንን እቅድ በቅርቡ ተካሂዶ በነበረው የG20 የመሪዎች ጉባኤ ወቅት የተናገሩት የአቡዳቢው ገዥ ሼክ ሞሃመድ ቢን ዛይድ መሆናቸው ተዘግቧል። ውጥኑ ተግባራዊ የሚሆነው የአቡዳቢ የልማት ፈንድ አ
Dec 22, 20251 min read


በጋምቤላ ክልል የተከሰተው ግጭት ተጨማሪ ጉዳት እንዳያደረስ በቂ የጸጥታ አካል ''በአስቸኳይ'' እንዲሰማራ ኢሰመኮ ጠየቀ፡፡
ታህሳስ 13/2018 በጋምቤላ ክልል የተከሰተው ግጭት ተጨማሪ ጉዳት እንዳያደረስ በቂ የጸጥታ አካል ''በአስቸኳይ'' እንዲሰማራ ኢሰመኮ ጠየቀ፡፡ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን(ኢሰመኮ) ይህን የጠየቀው በክልሉ የተከሰተውን ግጭት አስመልክቶ ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው፡፡ ኮሚሽኑ ከህዳር 28 ጀምሮ በጋምቤላ ከልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ፣ በጋምቤላ ወረዳ፣ በጋምቤላ ከተማ እና በዙሪያው ባሉ አካባቢዎች የተፈጠረውን ግጭት ተከትሎ የተፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን እየተከታተለ እንደሆነ አስረድቷል። ኮሚሽኑ የጋምቤላ ከተማ ፖሊስ ጸህፈት ቤት አዛዥ የነበሩት ዋና ኢንስፔክተር ኡሙድ ኡጁሉ መገደልን ተከትሎ በአካባቢው የተኩስ ልውውጥ ሲካሄድ በመቆቱ የሰው ሕይወት እንዲጠፋ፣ አካል እንዲጎድለም ምክንያት ሆኗል ብሏል። ኮሚሽኑ በመግለጫው የሰዓት ገበድ እላፊ ተጥሏል፤ የመ
Dec 22, 20251 min read


ትውልደ ኢትዮጵያዊው ደራሲና ፀሀፊ ዲናው መንግስቱ በኒውዮርክ የሚገኘውን ፔን አሜሪካን በፕሬዘዳንትነት እንዲመሩ ተመረጡ።
ታህሳስ 11/2018 ትውልደ ኢትዮጵያዊው ደራሲና ፀሀፊ ዲናው መንግስቱ በኒውዮርክ የሚገኘውን ፔን አሜሪካን በፕሬዘዳንትነት እንዲመሩ ተመረጡ። ከትናንት በስቲያ እሮብ የፔን አሜሪካ ዓመታዊ ጉባኤ ላይ በተደረገ ምርጫ ትውልደ ኢትዮጵያዊው ዲናው መንግስቱ ድርጅቱን በፕሬዘዳንትነት እንዲመሩ ተመርጠዋል። የ103 ዓመት እድሜ ያለው ታዋቂው ተቋም "ፔን አሜሪካ" ዋና መቀመጫውን በኒውዮርክ ያደረገና ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ነው፡፡ ተግባሩም ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትን መደገፍ ፣ ለስነ ፅሁፍ እድገትና ነፃነት መታገል፣እንዲሁም በአጠቃላይ በአለም ዙሪያ ሰብአዊ መብት እንዲከበር መስራት መሆኑ ይነገራል፡፡ ፔን በመላው አለም ለተመሳሳይ ዓላማ የቆሙ ከ100 በላይ ድርጅቶችን የያዘና በጋራ አሰባሳቢ ጥላው ፔን ኢንተርናሽናል በሚል መጠሪያ የሚታ
Dec 20, 20252 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page








