top of page

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ባለፉት ዘጠኝ ወራት 3,600 የውጪ ሃገር ዜጎች በሀሰት የኢትዮጵያ ፓስፖርት ለመያዝ ሲንቀሳቀሱ ደርሼባቸዋለሁ ብሏል።

  • 3 hours ago
  • 1 min read

ግንቦት 6/2018


የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ባለፉት ዘጠኝ ወራት 3,600 የውጪ ሃገር ዜጎች በሀሰት የኢትዮጵያ ፓስፖርት ለመያዝ ሲንቀሳቀሱ ደርሼባቸዋለሁ ብሏል።


አገልግሎቱ ከ10 ሺህ በላይ ሰዎች ሀሰተኛ የልደት ሰርተፍኬት፣ መታወቂያ እና ፋይዳ በመያዝ ህጋዊ አገልግሎት ለማግኘት ሲሉ እንደተደረሰባቸው ተናግሯል።


በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የፓስፖርት አገልግሎት ዳሬክተር የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ብርሃኑ ከድንበር አከባቢ የሚመጡ ኢትዮጵያውያን ከውጪ ሃገር ከሚመጡ ዜጎች ጋር የሚመሳሰል ማንነት ስላላቸው የውጪ ዜጎች ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ሃሰተኛ ሰነድ ለመያዝ ሙከራ እንደሚያደርጉ አስረድተዋል።


አቶ ሙሉጌታ ረጅም ዓመታትን በኢትዮጵያ የኖሩ ኤርትራዊያን የኢትዮጵያ ዜግነት ሊያገኙ የሚችሉበትን ሁኔታም አስረድተዋል።


በሪፈረንደሙ ወቅት ያልመረጡ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ የዜግነት መብት ይሰጣቸዋል፣ ሪፈረንደም የመረጡ ግን ህጉን ተከትለው የዜግነት ጥያቄ ማቅረብ ይችላሉ ብለዋል።


የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የሚነሱበትን ቅሬታዎች ለመፍታት እየሰራ መሆኑን ያነሱት ኃላፊው ፣ ሰዎችም ለአግልግሎት ሲመጡ የሚያጋጥማቸውን እንግልት ለመቀነስ የሚጠበቅባቸውን ሰነድ ሁሉ አሟልተው እንዲመጡ አሳስበዋል።


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…

ንጋት መኮንን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…











Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page