የሚያዝያ ወር የዋጋ ግሽበት ምጣኔ ከ11 በመቶ መሻገሩን መንግስት ተናገረ።
- 4 hours ago
- 1 min read
ሚያዝያ 30/2018
የሚያዝያ ወር የዋጋ ግሽበት ምጣኔ ከ11 በመቶ መሻገሩን መንግስት ተናገረ።
አምና በዚህ ወቅት የዋጋ ግሽበቱ 14.4 በመቶ እንደነበር ያስታወሰው የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት ሲሆን ዘንድሮ በመጠኑ ቅናሽ አሳይቷል ብሏል።
የዘንድሮ የሚያዝያ ወር የግሽበት ምጣኔ 11.7 በመቶ ነው።
ከባለፈው ወር ደግሞ 2.2 በመቶ ያህል ጨምሯል።

በተለይ ምግብ ነክ የሆኑና አልኮል የሌላቸው መጠጦች ደግሞ ከፍተኛ ሆኖ የዋጋ ግሽበት ምጣኔአቸው 13.5 በመቶ ደርሷል።
ለአብነትም አትክልት፣ ስጋ፣ የወተት ተዋፅዖዎች፣ እንቁላል፣ ፍራፍሬ፣ ዘይት እና ስኳር የመሳሰሉት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ጨምሯል ብሏል አገልግሎቱ ባወጣው መረጃ።
ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት 9.1 በመቶ የደረሰ ሲሆን የትራንስፖርት ዋጋ በ13 በመቶ ከፍ ብሏል።
በምግብ ቤቶች እና ሆቴሎች 10.5 በመቶ የዋጋ ጭማሪ ታይቷል።
እንዲሁም ሌሎች በሚል አገልግሎቱ በጠቀሳቸው እቃዎች እና አገልገሎቶች የ15.9 በመቶ መመዝገቡ ተጠቅሷል።
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments