ትንባሆ በሚጨስባቸው የግል ትምህርት ቤቶች አካባቢ ብርቱ ቁጥጥር እያደረግሁ ነው ሲል የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ተናገረ፡፡
- 2 hours ago
- 1 min read
የሚያዝያ 29/2018
ትንባሆ በሚጨስባቸው የግል ትምህርት ቤቶች አካባቢ ብርቱ ቁጥጥር እያደረግሁ ነው ሲል የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ተናገረ፡፡
በትምህርት ቤቶቹ አካባቢ ትንባሆ ሲያጨሱ ተገኝተው እርምጃ የተወሰደባቸውም እንዳሉ ተጠቁሟል፡፡
ይህንን ያደረግሁትም ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር ነው ብሏል ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ፡፡
ትንባሆን በማንኛውም አይነት ሁኔታ መጠቀም የበዙ የጤና ችግሮች እንዳሉት ወጣቶች እንዲያወቁት የግንዛቤ ስራ እየሰራ መሆኑንም ተናግሯል፡፡

በተጨማሪም በህጉ መሰረት ሲጋራን በነጠላ መሸጥ በህግ ቢከለከልም አሁንም በነጠላ የሚሸጡ እና የሚገዙ በየቦታው እንደሚታዩም ተነስቷል፡፡
እንዲህ በሚያደርጉት ላይ የማስተማርና እርምጃ የመውሰድ ስራ እየተሰራ መሆኑን እና መልካም የሚባል መሻሻል መገኘቱን የተናገሩት ደግሞ በኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን የናርኮቲክ፣ ሳይኮትሮፒክ እና ትንባሆ ቁጥጥር ዴስክ ኃላፊ አቶ ቶሎሳ ገመዳ ናቸው፡፡
እንደ ኢትዮጵያ ያሉ አገራት የትንባሆ ቁጥጥር ስራዎችን በህግ በማስደገፍ ቢሰሩም ኢንዱስትሪዎች ደግሞ በተለይ ወጣቶችን በትንባሆ ሱስ ለማስያዝ የተለያዩ አማላይ ስልቶችን እየተጠቀሙ ስለሆነ በጊዜ ትምህርት መስጠትና መቆጣጠር አስፈላጊ መሆኑ የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን አስረድቷል፡፡
የትምባሆ ኢንዱስትሪዎች የትምባሆ ምርቶች በህፃናትና ወጣቶች ዘንድ ሳቢና ማራኪ እንዲሆኑ ለማስቻል እንደ ቸኮሌት፣ ቫኒላ፣ ኮኮናት፣ አፕልና የሌሎች ፍራፍሬዎችን ልዩ ልዩ ጣዕም የያዙ ማጣፈጫዎችን ይጠቀማሉ ሲባልም ሰምተናል፡፡
ትንባሆ መጠቀም፤ ለልብ እና የደም ዝውውር በሽታዎች፣ ለመተንፈሻ አካላት ችግሮች፣ ለስኳር በሽታ እና የሳንባ፣ የፊኛ፣ የጉሮሮ እና የአፍ ካንሰርን ጨምሮ ከ20 በላይ ለሚሆኑ የካንሰር አይነቶች የመጋለጥ እድልን እንደሚጨምር ተነግሯል።
ማንያዘዋል ጌታሁን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments