በአጭር ጊዜ ለግንባታ የሚጠይቀውን በጀት አግኝተው ግንባታን ይከውኑት ይሆን?
- 3 hours ago
- 2 min read
የሚያዝያ 29/2018
የትምህርት ሚኒስቴር በቀሪዎቹ 4 ወራት 1,452 የቅድመ መደበኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሁሉም ክልሎች ለመገንባት በቅብሩ ከክልሎች ጋር ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
እነዚህ ትምህርት ቤቶች የሚገነቡት ግማሹ በትምህርት ሚኒስቴር ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በክልሎቹ በራሳቸው ወጪ ነው፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር ለሚያስገነባቸው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 40 ሚሊዮን ዶላር ፈንድ ከአጋር አካላት በእርዳታ ማግኘቱን ተነግሯል፡፡
ታዲያ ክልሎች በአጭር ጊዜ ለግንባታ የሚጠይቀውን በጀት አግኝተው ግንባታን ይከውኑት ይሆን? የተለያዩ ክልሎችን ጠይቀናል፡፡
የደቡብ ኢትዮጵ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዮት ደምሴ በክልሉ የሚገነባው 70 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

እነዚህ ትምህርት ቤቶች ሲገነቡ በክልሉ ውስጥ በሚኖሩ ሁሉም ወረዳዎች ቢያንስ 1 ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲኖረን ያስችላል ብለዋል፡፡
እነዚህ ትምህርት ቤቶች ለመገንባት የበጀት ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑን የነገሩን ሲሆን ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር እየመከርንበት ነው ሲሉም ጠቅሰዋል፡፡
የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) ባለፉት ጊዜያት ኢትዮጵያ ውስጥ የተገነባው ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርትቤት ቁጥር 34 ሺህ እንደሆነ ነግረውናል፡፡

ከዚህ ውስጥ 20,100 የሚሆኑት የተገነቡት በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ነው ያሉ ሲሆን ይህን ያህል ቁጥር ያለው ትምህርትቤት ለመገንባት የተቻለው በክልሉ ያለው ማህበረሰብን በማስተባበርና ከባለሀብቶች ጋር በመቀራረብ ነው ብሏል፡፡
አሁን የሚገነቡትም ትምህርት የፋይናንስ ክፍተት እንዳይፈጠር ቤቶች ህብረተሰቡን በማስተባበር እንሰራለን ብለዋል፡፡
የአፋር ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሳ አደም (ዶ/ር) በአፋር ክልል በ560 ትምህርት ቤቶች የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት እየሰጡ ነው ይላሉ፡፡

አሁን በክልሉ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በ4 ወራት ውስጥ ሚገነቡት ትምህርትቤቶች እውን ለማድረግ ክልሉ ከባለሃብቶች ጋር እየመከረበት ነው ሲሉም ጠቅሰዋል፡፡
ሶስቱም የክልል የትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርትቤት ግንባታውን በቀሪ 4 ወራት ውስጥ ገንብቶ ለማድረስ የፋይናንስ አቅርቦት እጥረት መኖሩን የጠቀሱ ሲሆን ችግሩን ለመፍታት ማህበረሰቡን ለማስተማመር ማቀዳቸውን ነግረውናል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….
በረከት አካሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7

