top of page

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት 9 ወራት የስነ ምግባር ጥሰት በፈፀሙ 1,139 የአገልግሎቱ ሠራተኞች ላይ የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃዎች መውሰዱን ተናገረ፡፡

  • 10 hours ago
  • 1 min read

ግንቦት 4/2018


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት 9 ወራት የስነ ምግባር ጥሰት በፈፀሙ 1,139 የአገልግሎቱ ሠራተኞች ላይ የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃዎች መውሰዱን ተናገረ፡፡


እርምጃ ከተወሰደባቸው ኃላፊዎችና ሠራተኞች መካከል 16ቱ ከስራቸው ሲሰናበቱ፤ 721ዱ የደመወዝ ቅጣት እንዲሁም 402 የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ናቸው ተብሏል፡፡


አገልግሎቱ በሠራተኞች ላይ ከወሰዳቸው አስተዳደራዊ እርምጃዎች መካከል 103 ሠራተኞች ላይ በደንበኞች የቀረበን ጥቆማ በመመርመር የወሰደው መሆኑንና ቀሪ 1,036ቱ ተቋሙ በራሱ ግኝት አጣርቶ የወሰዳቸው እርምጃዎች መሆናቸውን ተናግሯል፡፡



ባለፉት 9 ወራት አገልግሎቱ በሙስና መጠቆሚያ ዘመናዊ መተግበሪያ እና በሌሎች አማራጮች ከደንበኞቹ የደረሱትን 427 ጥቆማዎችን መርምሮ በ103 ኃላፊዎችና ሠራተኞች ላይ የተለያዩ እርምጃዎችን ወስዷል ተብሏል፡፡


በደንበኞቹ በቀረቡት ጥቆማዎች መሰረት 14 የፅሁፍ፣ 80 የደሞዝ ቅጣት፣ 2 ከቦታ የማንሳትና 7 ስንብት በድምሩ 103 እርምጃዎች መወሰዳቸውን ጠቅሷል፡፡


የሙስና ጥቆማ ከቀረበባቸው ጉዳዮች መካከል የአዲስ ቆጣሪ ጥያቄ፣ የኃይል መቆራረጥና አስቸኳይ ጥገና፣ የቆጣሪ ንባብና የቢል ስብሰባ እንዲሁም ንብረት አያያዝና አጠቃቀም ይገኙበታል፡ እንደሚገኙበት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በላከን መግለጫ ተናግሯል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page