የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከፍተኛ የተባለ የግማሽ ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ልዩ ጨረታ ሊያካሂድ ነው፡፡
- sheger1021fm
- 3 hours ago
- 1 min read
ጥር 18/2018
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከፍተኛ የተባለ የግማሽ ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ልዩ ጨረታ ሊያካሂድ ነው፡፡
ነገ አካሂደዋለሁ ብሎ ባወጣው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ 500 ሚሊዮን ዶላር ለባንኮች አቀርባለሁ ብሏል፡፡
የዛሬ ሳምንት ባካሄደው የ70 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ 15 ባንኮች አንድን ዶላር በአማካይ 154.9 ብር በሆነ ዋጋ ገዝተዋል፡፡
በዚህ ጨረታ የባንኮች ፍላጎት 94.7 ሚሊዮን ዶላር ማግኘት የነበረ ሲሆን በጊዜው ብሔራዊ ባንክ ካቀረበው 70 ሚሊዮን ዶላር ጋር ሲነፃፀር ከ24 ሚሊዮን ዶላር በላይ ክፍተት እንዳለው ያሳያል፡፡
ይህም በባንኮች ዘንድ ከፍ ያለ የውጭ ምንዛሬ ፍላጎት መኖሩን ያሳያል፡፡

በጥቁር ገበያው እና በመደበኛው የምንዛሬ ገበያ መካከል ያለው ልዩነትም እንደታሰበው መጥበብ አልቻለም፡፡
የተጠቀሱትን ክፍተቶች ከግምት በማስገባት እና የምንዛሬ ገበያውን ለማረጋጋትም ይመስላል ብሔራዊ ባንክ ነገ ግማሽ ቢሊዮን ዶላር ለባንኮች በጨረታ አቀርባለሁ ብሏል፡፡
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገበያውን ለማረጋጋት ያለበትን ሀላፊነት ለመወጣት የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ማካሄድ ከጀመረ ወዲህ በልዩ ጨረታ ከፍተኛ መጠን ያለው ዶላር ሲያቀርብ የነገው ሁለተኛው ነው፡፡
ባለፈው ታህሳስ ወር መጨረሻ በወጣው የ150 ሚልዮን ዶላር ጨረታ ብር ከዶላር አንጻር በስሱም ቢሆን በ40 ሳንቲም የመጠንከር አዝማሚያ አሳይቶ እንደነበር አይዘነጋም፡፡
ለነገ የተሰናዳው ሁለተኛው ልዩ ጨረታ ከታህሳሱ በ350 ሚልዮን ዶላር ከፍ ያለ ነው፡፡
ትዕግስት ዘሪሁን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…..
YouTube : https://url-shortener.me/2DTR
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://url-shortener.me/2DTY
WhatsApp :https://url-shortener.me/2DU0
X : https://x.com/shegerfm?s=2
Website፡ https://www.shegerfm.com/
LinkedIn :https://url-shortener.me/2DU8
Tiktok : https://url-shortener.me/2DUB
Instagram : https://url-shortener.me/2DUD












Comments