top of page

 ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚካሄደው የግብርና ስራ በየዓመቱ የሚያስፈልገው አጠቃላይ ብድር 2.5 ትሪሊዮን ነው፡፡

  • sheger1021fm
  • 1 hour ago
  • 1 min read

ጥር 18/2018

 

ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚካሄደው የግብርና ስራ በየዓመቱ የሚያስፈልገው አጠቃላይ ብድር 2.5 ትሪሊዮን ነው፡፡

 

አሁን ላይ በዓመት እየቀረበ ያለው 52 ቢሊዮን ብር ነው፡፡

 

ለማዳበርያ ከንግድ ባንክ እየቀረበ ያለውን ብድር ሳይካተት፡፡

 

ይህም ማለት ግብርናው ከሚፈልገው ብድር አኳያ እየቀረበ ያለው እዚህ ግባ የሚባል አለመሆኑ ነው፡፡

 

መንግስት በቅርቡ ይፋ ያደረገው ሀገር አቀፍ የግብርና ፍኖተ ካርታ ከ4 ዓመት በኋላ ለግብርናው ዘርፍ በየአመቱ መቅረብ የሚገባው ብድር መጠን 880 ቢሊዮን ብር ለማድረስ አቅዷል፡፡

 

በግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የዲጂታል ፋይናሻል ሰርቪስ ፕሮግራም ቡድን መሪው አቶ አወት ተኬኤ የፋይናንስ ዘርፉ ለግብርናው በቂ ብድር የማያቀርበው ዘርፉን በቅጡ ባለመረዳት ነው፡፡

 

በተለይም የግል ፋይናስ ተቋማት ለግብርናው የሚሆን ምርት በሚገባ እያስተዋወቁ አይደለም የሚነሳው የፖሊሲ ክፍተት እንደተጠበቀ ሆኖ ብለዋል፡፡

 

በሀገር አቀፍ የግብርና ፍኖተ ካርታው መረጃ መሰረት አነስተኛ ማሳ ያለው አንድ ኢትዮጵያዊ ገበሬ የሚያገኘው ብድር መጠን 10 ሺ ብር ብቻ ነው፡፡

 

በዚህ ብድር ብቻ ገበሬው እርሻው መከወን አይቻልም ብድሩን በተለያየ አማራጭ ማስፋት አለብን ሲሉም አክለዋል፡፡

 

መንግስት የግብርና ፋይናንስ ችግርን ለመቅረፍ በማሰብ በተጠናቀቀው 2025 የግብርና ፍኖተ ካርታ ይፋ ማድረግ ዘርፉን ለመለወጥ ያለው ፍላጎት ያሳያል ብለዋል፡፡

 

ብድር ሲቀርብ ከገበሬው ጀምሮ እስከ ምርት ማቀነባበር ስራ ላይ ለተሰማራው የግብርና ተዋናይ ነው ይበልጡኑ ለገበሬው ሲሉም ነግረውናል፡፡

 

ከ2017 ዓመት በፊት በነበሩት 3 ተከታታይ አመታት በነበሩት ጊዜያት 591 ቢሊዮን ብር ብድር ከባንኮች መሰራጨቱን የግብርና ሚኒስቴርና ብሄራዊ ባንክ የወጡት መረጃ የሚያሳይ ሲሆን ግብርናው የ122 ቢሊዮን ብር አግኝቷል፡፡

 

ከዚህ ውስጥ 52 ቢሊዮን ብሩ ብቻ ነው ከማዳበርያ ውጪ ላለው የግብርና ስራ የቀረበው ብድር፡፡

 

ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ

 

በረከት አካሉ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…..

 

X : https://x.com/shegerfm?s=2                 

Website፡ https://www.shegerfm.com/                          

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page