top of page


በሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ የተቋቋመው አጣሪ ቡድን በምስራቅ አርሲ ዞን ስላለው ሁኔታ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት ይፋ አደረገ፡፡
ህዳር 1 2018 በኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ የተቋቋመው አጣሪ ቡድን በምስራቅ አርሲ ዞን ስላለው ሁኔታ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት ይፋ አደረገ፡፡ ከየቤተ እምነቱ የተውጣጣው አጣሪ ኮሚቴ ግድያው እምነትን፣ ዘርን፣ ፆታንና እድሜን ያልለየ መሆኑን ማረጋገጡን ተናግሯል፡፡ የማጣራት ስራው የተከወነባቸው በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ጉና ወረዳ፣ ሲርካ ወረዳ፣ ቁልቁሉ አቤ ወረዳና መርቲ ወረዳዎች ናቸው ተብሏል፡፡ የአጣሪ ኮሚቴው ዋና ሰብሳቢ መላከ ሰላም ዳዊት ያሬድ በሪፖርታቸው በእነዚህ ወረዳዎች በንጹሃን ሰዎች ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ ግድያና እገታ መፈፀሙን ማረጋገጣቸውን ጠቅሰው፤ ከአካባቢው ነዋሪዎች በተገኘው መረጃ የድርጊቱ ፈፃሚዎች በምሽት የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ብድኖች ናቸው ብለዋል፡፡ ኮሚቴው ከሄደባቸው ወረዳዎች መካከል አንዱ በሆነው በአርሲ ዞን ጉና
11 minutes ago1 min read


በ4 ዓመታት በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ይኖሩ የነበሩ ከ500,000 በላይ ኢትዮጵያዊያን መመለሳቸውን ተነገረ
ህዳር 1 2018 ባለፉት 4 ዓመታት በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ከ500,000 በላይ ኢትዮጵያዊያን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ፡፡ ኢትዮጵያዊያኑ በተለያዩ የመካከለኛ ምሥራቅ፣ የአፍሪካ እና እንደ በምይማር ያሉ የእስያ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ መሆናቸወን ሚኒስቴር መ/ቤቱ ጠቅሷል፡፡ ይህ ሥራ መቀጠሉ የተነገረ ሲሆን በሳውዲ አረቢያ በተለያዩ እስር ቤቶችና ማቆያ ማዕከላት የሚገኙ ሰዎች ከመስከረም 05 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከ17,000 በላይ ኢትዮጵያዊያን መመለስ ተችላል ተብሏል። በአሁኑ ወቅትም ከሳውዲ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን የመመለሱ ሥራ ቀጥሏል ሲልም አስረድቷል። በተመሳሳይ በየመን በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ 36 ሰዎች ወደ ሀገራ
1 hour ago1 min read


ህዳር 1 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ስሎቫኪያ በአውሮፓ አገሮች ታግዶ የሚገኘው የሩሲያ ገንዘብ ለዩክሬይን በብድር የመሰጠቱ ሀሳብ ከስሎቫኪያ በኩል ጠንካራ ተቃውሞ ገጠመው፡፡ በአውሮፓ ህብረት ዘንድ ታግዶ ከሚገኘው የሩሲያ ገንዘብ 140 ቢሊዮን ዩሮው ለዩክሬይን የጦር መደገፊያ በብድር እንዲሰጣት ምክር ከተያዘ መቆየቱን አናዶሉ አስታውሷል፡፡ የስሎቫኪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሮበርት ፊኮ ግን እኛ የዚህ ውጥን አካል አይደለንም ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ ከዚህ ይልቅ ለዩክሬይኑ ጦርነት ማብቃት ጥረቱ ቢበረታ ይሻላል ብለዋል ፊኮ፡፡ የታገደው የሩሲያ ገንዘብ ለዩክሬይን የጦር መደገፊያነት በብድር በሚሰጥበት መላ በአውሮፓ ህብረት መድረክ በመጪው ወር በታላቁ እንደሚመከርበት ታውቋል፡፡ ገንዘቡ ለዩክሬይን በብድር እንዲፈቀድላት የሁሉንም የህብረቱ አባል አገሮች ሙሉ ስምምነት እንደሚሻ ተ
2 hours ago2 min read


ዲጂታል ስርዓት እና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት)
ህዳር 1 2018 #ጉዳያችን - ዲጂታል ስርዓት እና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት) ሀገራት ወደ ዲጂታል መንገድ በሚያደርጉት ጉዞ የዛሬውን ብቻ ሳይሆን እንዳስፈላጊነቱ የቀደሙ በወረቀት ያሉ መረጃዎችንም ወደ ዲጂታል ስርዓት ያስገባሉ። ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ ምን ማድረግ ይኖርባታል? የኤ.አይ.ቲ ቴክኖሎጂ ስራ አስኪያጅና የቴክኖሎጂ ባለሙያው አቶ እስራኤል ብሩክ በጉዳዩ ላይ የሰጡንን ማብራሪያ ያድምጡ….. የቀደመው ተያያዥ ዘገባን ለማድመጥ …. https://tinyurl.com/uernphkz ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Fa
2 hours ago1 min read


ምርቶች በወጣላቸው ደረጃ መሰረት ተዘጋጅተው ለገበያ መዋላቸውን ለማረጋገጥ የሚደረገው የቁጥጥር የላላ ሆኖ ቀጥሏል፡፡
ህዳር 1 2018 ምርቶች በወጣላቸው ደረጃ መሰረት ተዘጋጅተው ለገበያ መዋላቸውን ለማረጋገጥ የሚደረገው የቁጥጥር የላላ ሆኖ ቀጥሏል፡፡ መረጃዎችን የሚያጸድቀው ቦርድ የሚወጡ ደረጃዎችን አተገባበር በየጊዜው እንዲከታተል የሚያስችል አዲስ አሰራር ሊከተል እንደሆነም ሠምተናል፡፡ በሌላ በኩል ለሁለት ተጨማሪ ሀገር በቀል ምግብ ነክ ምርቶች በኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንስቲትዩት ደረጃ መዘጋጀቱ ተነግሯል፡፡ የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንስቲትዩት ምግብ ነክ ለሆኑ ስድስት አገር በቀል ምርቶች ደረጃ ማዘጋጀቱ ይታወሳል፡፡ ሽሮ፣ በርበሬ፣ ቆሎ፣ በሶ፣ አረቄ እና ጠጅ ደረጃው የተዘጋጀላቸው ምርቶች ናቸው፡፡ ለምርቶቹ የወጣውን ደረጃ ህብረተሰቡ እንዲያውቀው እንዲሁም የተመረጡ የጥቃቅን እና አነስተኛ ተቋማት ደረጃውን መሰረት አድርገው ምርቱን እንዲያዘጋጁ መደረጉን በኢንስቲት
3 hours ago1 min read


ህዳር 1 2018 - በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው መታየት የነበረባቸው አዎንታዊ ለውጦች ለምን መታየት አልቻሉም?
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ሙሉ በሙሉ ስራ ላይ የዋለው ካለፈው መስከረም ወር ጀምሮ ነው፡፡ ይህን ተከትሎም ከመስከረም በኋላ የብር የመግዛት አቅም ይጠናከራል የውጪ ምንዛሪ ግኝቱ ከፍ ይላል የሚሉ እና ሌሎችም የተጠበቁ ለውጦች ነበሩ፡፡ መሬት ላይ ሲታይ ግን በተቃራኒ ሆነው የተገኙም አሉ፡፡ ምክንያቱ ምንድን ነው? የብር የመግዛት አቅም መጠናከር ሲኖርበት ከዕለት ዕለት አሳሳቢ በሚባል ደረጃ እያሽቆለቆለ መሆኑን በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው የዘርፉ ባለሞያ ጠቅሰዋል፡፡ ለዚህም አንደኛው ምክንያት የውጪ ምንዛሪ ገበያው ላይ ያለው ችግር መሆኑን አንስተዋል፡፡ የውጪ ምንዛሪውን ገበያ ከሚያውኩት መካከል የባንኮች አሰራር ግልፅ አለመሆን፣ የጥቁር ገበያው ጠንካራ ሆኖ መቀጠልና ሌሎችም ይገኙበታል ብለዋል፡፡ በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው መታየት የነበረባቸው፤ አዎንታዊ
3 hours ago1 min read


ጥቅምት 29 2018 - ጥቅምት 29 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#አሜሪካ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን በደቡብ አፍሪካ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የቡድን 20 አባል አገሮች ጉባኤ አይገኝም አሉ፡፡ የአሜሪካውፕሬዘዳንት አፍሪካ ነርስ በተሰኙት ነጭ ደቡብ አፍሪካዊያን ላይ እልቂት እና ማሳደዱ በርትቶባቸዋል የሚል ክሳቸውን እየደጋገሙት መሆኑን አናዶሉ አስታውሷል፡፡ የፕሬዘዳንት ሲሪል ራማፎሳ መንግስት በትራምፕ የሚቀርበውን ውንጀላ በተደጋጋሚ እያስተባበለ ነው፡፡ ትራምፕ ግን የደቡብ አፍሪካን መንግስት ጥምድ አድርገው እንደያዙት ነው፡፡ እንደውም ደቡብ አፍሪካ ከቡድን 20 አባል አገርነቷ ልትባረር ይገባል ያሉት ሰሞኑን ነው፡፡ የቡድን 20 አባል አገሮች ስብሰባ በደቡብ አፍሪካ ቢካሄድም ያለ አሜሪካ ተሳትፎ ይሆናል ተብሏል፡፡ #ማሊ በምዕራብ አፍሪካዊቱ ሀገር ማሊ
2 days ago1 min read


የሀይማኖት ምልክቶችን የሚያንቋሽሹ ሰዎች በህግ እንዲጠየቁ ካልተደረገ ለግጭት መንስኤ ሊሆኑ እንደሚችሉ ተነገረ
ጥቅምት 28 2018 የሀይማኖት ምልክቶችን የሚያንቋሽሹ እና ንፁሀን የሚገድሉ ሰዎች በህግ እንዲጠየቁ ካልተደረገ ለከፋ ግጭት መንስኤ ሊሆኑ እንደሚችሉ ተነገረ። በአደባባይ፣ በጎዳናዎች የሚደረጉ ስብከቶችን ጨምሮ የሀይማኖት ዶግማዎችን የሚያንቋሽሹ እና የሚያነውሩ አካላትን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ የሚረዳ ስርዓት ለማበጀት ወይይት ተጀምሯል ተብሏል። የአዲስ አበባ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ፣ የከተማዋ ኮሚኒኬሽን ጉዳይዎች ቢሮ፣ የሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ከሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን የስራ ሃላፊዎች ጋር በመሆን በሰላም ጉዳይ ላይ በትናንትናው እለት ተወያይተዋል። አንድ የውይይቱ ተሳታፊ ህጻናትን ጨምሮ ንጹሃን እየተገደሉ ነው፡፡ ይህን ወንጅል የሚፈጽሙ አካላት ለምንድነው በህግ የማይጠየቁት፣ መቼስ ነው የሚቆመው ሲሉ ጠይቀዋል። ንጹሃን እየተገደሉ እስከመቼ
3 days ago3 min read


ጥቅምት 28 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ካሜሮን የካሜሮኑ አረጋዊ ፕሬዘዳንት ፖል ቢያ ለ8ኛ ጊዜ ቃለ መሐላ በመፈፀም አዲሱን ሀላፊነታቸውን ተረከቡ፡፡ ፖል ቢያ ለ8ኛ ጊዜ ቃለ መሐላ በመፈፀም ሀላፊነታቸው የተረከቡት በቅርብ ጊዜው የካሜሩን ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ አሸንፈዋል ከተባለ በኋላ እንደሆነ አልጀዚራ ፅፏል፡፡ የ92 አመቱ አረጋዊ ፖል ቢያ እስካሁን ካሜሮንን ከ40 አመታት በላይ መርተዋታል፡፡ በአሁኑ ጊዜም ከአገር መሪዎቹ መካከል በእድሜ አንጋፋው እሳቸው ናቸው፡፡ ፖል ቢያ በምርጫው አሸንፈዋል የተባለው ሁነኛ ተፎካካሪዎች ከምርጫ በታገዱበት አጋጣሚ ነው ተብሏል፡፡ ተቃዋሚዎች ፖል ቢያ አሸናፊ የተደረጉበትን ምርጫ ህገ መንግስታዊ ጠለፋ ነው ሲሉ እየጠሩት መሆኑን መረጃው አስታውሷል፡፡ #ሩሲያ ሩሲያ የአሜሪካ የወረራ ስጋት ተጋርጦብኛል ለትምትለው የደቡብ አሜሪካዋ አገ
3 days ago2 min read


አዋሽ ባንክ የመስመር ዲጂታል የብድር አገልግሎት ይፋ ማድረጉን ተናገረ።
ጥቅምት 28 2018 አዋሽ ባንክ የመስመር ዲጂታል የብድር አገልግሎት ይፋ ማድረጉን ተናገረ። ባንኩ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በዲጂታል መተግበሪያ በኩል የብድር አገልግሎት ማቅረብ የሚያስችል '"መስመር ዲጂታል የብድር አገልግሎት" በአዋሽ ብር ፕሮ መተግበሪያ በኩል አቅርቧል ተብሏል። ባንኩ ይህንን መተግበሪያ ይፋ ያደረገው ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን እና ከፈርስት ኮንሰልት ጋር በመተባበር እንደሆነ ተናግሯል። አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በሙሉ አቅማቸው እንዳይወጡ እና ስራዎችን እንዳይከውኑ ከሚያደርጓቸው ችግሮች መካከል የብድር አገልግሎት አለማግኘት አንዱ መሆኑን የአዋሽ ባንክ ሲኒየር ችፍ ማርኬቲንግ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ዮሀንስ መርጋ አንስተዋል። ለዚህ ችግር መፍትሄ ለመስጠት ደግሞ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የብድር አገልግ
3 days ago1 min read


ጥቅምት 27 2018 - ''በሀይማኖት ሽፋን ግጭት ለመቀስቀስ የሚንቀሳቀሱ አካላትን ከድርጊታችሁ ታቀቡ ልንላቸው ይገባል'' የአዲስ አበባ ከተማ የኮሙኒኬሽን ቢሮ
በሀይማኖት ሽፋን ስም ግጭት ለመቀስቀስ የሚንቀሳቀሱ አካላትን "ከድርጊታችሁ ታቀቡ" ልንላቸው ይገባል ሲል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮሙኒኬሽን ቢሮ ተናገረ፡፡ የአዲስ አበባ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ፣ የከተማዋ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ከሃይማኖት ሚዲያዎች የስራ ሃላፊዎች ጋር በመሆን በሰላም ጉዳይ ላይ ተወያይተዋል። በውይይቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የከተማዋ የኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ዘውዱ ከበደ ሚዲያ ሰላምን ለመስበክ፣ የእርስ በእርስ ግንኙነትን ለማጠናከር ድርሻው ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡ ይሁንና አንዳንድ ግለሰቦች ሃይማኖትን ሽፋን በማድረግ በማህበረሰብ መካከል ግጭት እና ቅራኔ ለመፍጠር እንደሚሰሩ ተናግረው እነዚህን አካላት በቃ ልንላቸው ይገባል ሲሉ አስረድተዋል፡፡ የአዲስ አበባ ሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጻሀፊ መጋቢ ታምራት አበ
4 days ago1 min read


ገበያው ልቅ ነፃነት ሳይሆን የመንግስትን ጥብቅ ቁጥጥር ያሻል ተብሏል
ጥቅምት 27 2018 የአንዳንድ ምርቶች ዋጋ ባልታወቀ ምክንያት ሁለትና ሶስት እጥፍ ሲያድግ ሌላ ጊዜ ደግሞ በዛው ልክ ሲወርድ ይታያል፡፡ የደላሎች ጣልቃ ግብነት እና የመንግስት የቁጥጥር ማነስ እንዲህ ላለው ያልተረጋጋ ዋጋ ምክንያቶች መካከል እንደሆኑ ባለሙያዎች ይነገራሉ፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገራትም ገበያው ልቅ ነፃነት ሳይሆን የመንግስትን ጥብቅ ቁጥጥር ያሻል ተብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… ንጋቱ ረጋሣ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬Wh
4 days ago1 min read


ጥቅምት 27 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ፊሊፒንስ ፊሊፒንስን ሰሞኑን በመታት ከባድ አውሎ ነፋስ የሟቾቹ ብዛት ከ140 በላይ መድረሱ ተሰማ፡፡ አውሎ ነፋሱ በከባድ ጎርፍ እና በመሬት መንሸራተት ጭምር የታገዘ እንደነበር AFP አስታውሷል፡፡ በአደጋው ከሞቱት እና አካላዊ ጉዳት ከገጠማቸው ሌላ 127 ሰዎች ደግሞ እስካሁን የደረሱበት አልታወቀም ተብሏል፡፡ ይህም የሟቾቹ ብዛት ከተጠቀሰውም በላይ ሊጨምር ይችላል የሚል ስጋት አሳድሯል፡፡ ሴቡ የተባለችዋ ግዛት ዋነኛዋ የአደጋው ሰለባ ነች፡፡ በግዛቲቱ የደረሰው ጎርፍ እና የመሬት መንሸራተት ከዚህ ቀደም ከደረሱት ሁሉ በእጅጉ ከባድ ነበር ተብሏል፡፡ ጎርፉ መኪኖችን እና ትልልቅ ኮንቴይነሮችን ጭምር አንከብክቦ መጋለቡ ታውቋል፡፡ ለፊሊፒንሱ አውሎ ነፋስ ፣ ጎርፍ እና የመሬት መንሸራተት አደጋ የአየር ለውጡ በዋና ምክንያትነት እየቀረ
4 days ago2 min read


በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በተከሰቱ ግጭቶች ምክንያት መስተጓጎል ከሚገጥማቸው አንዱ የህክምና አገልግሎትን በአግባቡ አለማዳረስ ነው፡፡
ጥቅምት 27 2018 በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በተከሰቱ ግጭቶች ምክንያት መስተጓጎል ከሚገጥማቸው አንዱ የህክምና አገልግሎትን በአግባቡ አለማዳረስ ነው፡፡ በእነዚህ አካባቢዎች እንዲሁም በግጭት ባለፉት ውስጥ ደግሞ የአዕምሮ ጤና ችግር እየተባባሰ የሚሄድ በመሆኑ ህክምናው እንዲሁም የመድኃኒት አቅርቦቱ ላይ እንዴት እየተሰራ ነው? ስንል የጤና ሚኒስቴርን ጠይቀናል፡፡ በጤና ሚኒስቴር የአዕምሮ ጤና ፕሮግራም ባለሙያ የሆኑት አቶ ጀማል ተሾመ እንደነገሩን በተለያዩ ግጭት በነበረባቸው እንዲሁም አሁንም ድረስ ግጭቱ በቀጠለባቸው አካባቢዎች ላይ ከመንግስት በተጨማሪ በአለም አቀፍ ተቋማት ጭምር የአዕምሮ ጤና ህክምናና የመድኃኒት አቅርቦት እንዲኖር ጥረት እያደረግን ነው ብለዋል፡፡ የአዕምሮ ጤና ህክምና አንዴ ከተቋረጠ እየተባባሰ የሚሄድና ለነገ ቢባ
4 days ago1 min read


የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥርዓተ ትምህርት ክለሳ እየተደረገበት መሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር ተናገረ፡፡
ጥቅምት 26 2018 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥርዓተ ትምህርት ክለሳ እየተደረገበት መሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር ተናገረ፡፡ የሚከለሰው ሥርዓተ ትምህርትም በ2018 የትምህርት ዘመን ዩኒቨርስቲ የገቡ ተማሪዎች የአንደኛ ዓመት ትምህርታቸውን ሲጨርሱ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል። በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ተልዕኮ መሰረት ባደረገ መልኩ ስርዓተ ትምህርቱን የመከለስ ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። ክለሳው ያስፈለገው የቀድሞዎቹ ሥርዓተ ትምህርቶች ዘመኑን ያልዋጁና ከ21ኛው ክፍለ ዘመን ጋር በአግባቡ ያልተቃኙ በመሆናቸው ነው ብለዋል። አዲሱ እየተከለሰ ነው የተባለው የከፍተኛ ትምህርት፣ ሥርዓተ ትምህርት ተመራቂዎች በትምህርት ፕሮግራሞቹ ከተማሩ በኋላ ሊኖራቸው የሚ
5 days ago1 min read


ምርት ለማጓጓዝ ከፍተኛ ቢሮክራሲና የተጠላለፈ አንደኛው ፈተና
ጥቅምት 26 2018 #ምጣኔ_ሀብት ለዘመናት የኢትዮጵያን ወጪ ንግድ ሲረብሽ የነበረው ጉዳይ የኮንቴይነር እጥረት፣ የአስተሻሸግ ችግር እና ቅሸባ እንደሆነ ተደጋግሞ ይነሳል። ይኸው ችግር ኢትዮጵያ በዓለም ገበያ የምታቀርባቸውን ምርቶች እንዲወድቁ ወይም እንዲመለሱ አድርጓል። ከዚህም ባለፈ ምርት ለማጓጓዝ ከፍተኛ ቢሮክራሲና የተጠላለፈ የሎጅስቲክስ ስራም አንደኛው ፈተና ነው። በአየር፣ በየብስ፣ በባህር፣ በባቡር፣ የሎጅስቲክስ ስራዋን ማቀላጠፍ ያላወቀችበት ኢትዮዽያ አሁንም ከዚህ መዓዘን ብዙ ስራ ይጠብቃታል። ይህ በመሆኑም ከወጪ ንግድ የታሰበውን ያህል የውጪ ምንዛሪ ለመለቃቀም ፈትኖ ቆይቷል። በተለይ በወጪ ንግድና ሌላውም ንግድ የሚሳተፉ በሙሉ የሎጀስቲክስ መደነቃቀፍን አሁንም ያነሳሉ፡፡ ከዚህም በላይ የኢትዮዽያ ወጭ ንግድ የውድድር
5 days ago1 min read


''ከማህበረሰቡ ከሚቀርቡለት የተበደልን አቤቱታዎች 35 በመቶዎቹ እኔን የሚመለከቱ አይደሉም'' እምባ ጠባቂ ተቋም
ጥቅምት 26 2018 የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ከማህበረሰቡ ከሚቀርቡለት የተበደልን አቤቱታዎች 35 በመቶዎቹ እኔን የሚመለከቱ አይደሉም አለ፡፡ በህግ የተሰጠኝ ሃላፊነት የግልም ሆነ የመንግስት ድርጅቶች ማህበረሰቡ ላይ የሚፈፅሟቸውን አስተዳደራዊ በደሎች የተመለከቱ አቤቱታዎችን ተቀብሎ በመመርመር የተበዳዮችን እምባ ማበስ ነው የሚለው ተቋሙ፤ ነገር ግን ብዙ ጊዜ የሚቸገርበት ጉዳይ ማህበረሰቡ ወደ እምባ ጠባቂ ተቋም ማምጣት ያለበትን ጉዳይ አለማወቅ እንደሆነ ነግሮናል፡፡ በዚህ ምክንያት አጠቃላይ አቤቱታዎች 35 በመቶዎቹ አይመለከቱንም ብለን የምንመልሳቸው ናቸው ያሉን የተቋሙ ምክትል እምባ ጠባቂ ዶክተር የኔነህ ስመኝ ናቸው፡፡ በህዝብ ምርጫ የተቋቋሙ ምክር ቤቶች በህግ አውጪነታቸው የሚሰጧቸው ውሳኔዎችን፤ በፍርድ ቤት በመታየት ላይ ያሉና ውሳኔ
5 days ago1 min read


የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን እስካሁን ወደ ማህበረሰቡ ለተቀላቀሉ የቀድሞ ተዋጊዎች ከ7.2 ቢሊዮን ብር በላይ መክፈሉን ተናግሯል፡፡
ጥቅምት 26 2018 የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን እስካሁን ወደ ማህበረሰቡ ለተቀላቀሉ ከ80,000 በላይ የቀድሞ ተዋጊዎች ከ7.2 ቢሊዮን ብር በላይ መክፈሉን ተናግሯል፡፡ ከባለፈው ዓመት ህዳር ወር ጀምሮ በአጠቃላይ ከ80,000 በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች በትግራይ፣ በአፋር፣ በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች የታሃድሶ ስልጠና ወስደው ማህበረሰቡ መቀላቀላቸውን የኮሚሽኑ ኮሚኒሽን እና አለም አቀፍ ግንኙት ዳይሬክተር ሃብታሙ መሰለ ተናግረዋል፡፡ ዳይሬክተሩ በዚህም ለእያንዳንዱ የቀድሞ ተዋጊ ከስልጠናው በኋላ ስራ ለመጀመሪያ 90,400 ብር እንደተሰጣቸው ነግረውናል፡፡ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ወደ ስራ ሲገባ 371,971 የቀድሞ ተዋጊዎች አሉ ብሎ ሲሆን እስካሁን 80,000 በላይ የሚሆኑትን ወደ ማህበረሰቡ መቀላቀል ችሏል፡፡ ከዚህ ውስጥ 63,000 የሚሆኑ
5 days ago1 min read


ጥቅምት 26 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#እስራኤል የእስራኤሉ የኢነርጂ እና የመሰረተ ልማት ሚኒስትር ኤሊ ኮኸን ወደ ጋዛው ጦርነት መመለሳችን አይቀርም አሉ፡፡ ዔሊ ኮኸን በጋዛ ወደ ጠንካራው ድብደባችን ለመመለስ የምንጠብቀው የሟች ታጋቾችን አስከሬን በሙሉ መረከብ ብቻ ነው ሲሉ ለአገራቸው ቻናል 7 ቴሌቪዥን መናገራቸውን ሚድል ኢስት ሞኒተር ፅፏል፡፡ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቀደም ሲል ባቀረቡት ባለ 20 ነጥቦች የሰላም እቅድ በጋዛ አልፎ አልፎ ቢጣስም የተኩስ አቁም ስራ ላይ ውሏል፡፡ እቅዱ የተኩስ አቁሙን መዝለቅ የሚከታተል አለም አቀፍ አረጋጊ ሀይል በጋዛ እንዲሰፍር ይጠይቃል፡፡ ዔሊ ኮኸን ግን አለም አቀፍ ሀይል ቢሰፍር እንኳ ሐማስን ትጥቅ ማስፈታቱ አይሆንለትም ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ የአገራቸው ጦር ግን ወደ ጋዛው ዘመቻ ተመልሶ ሐማስን ትጥቅ ማስፈታቱን በብቃት ማሳካት ይችላ
5 days ago2 min read


ጨው፣ ስኳር፣ ስብ በብዛት የሚገባባቸው በፋብሪካ የተቀነባበሩ፣ የታሸጉ ምግቦችን ለመቆጣጠር ይረዳል የተባለ ህግ እየተሰናዳ ነው፡፡
ጥቅምት 25 2018 ጨው፣ ስኳር፣ ስብ በብዛት የሚገባባቸው በፋብሪካ የተቀነባበሩ፣ የታሸጉ ምግቦችን ለመቆጣጠር ይረዳል የተባለ ህግ እየተሰናዳ ነው፡፡ ገና በረቂቅ ደረጃ ላይ ያለው ህጉ በፋብሪካ የሚቀነባበሩ ምግቦች በውስጣቸው የያዟቸውን ንጥረ ነገሮችና መጠን በግልፅ እንዲፅፉ፣ ያስገድዳል፡፡ ምርቱን ማስተዋወቅ ይከለክላል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… ምህረት ስዩም የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxj
5 days ago1 min read


በአዲስ አበባ በ3 ወራት ውስጥ ከ25,000 በላይ ህፃናት ተወልደው፣ የልደት ምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል፡፡
ጥቅምት 26 2018 በአዲስ አበባ በ3ወራት ውስጥ ከ25,000 በላይ ህፃናት ተወልደው፣ የልደት ምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ በወቅቱ የልደት ምዝገባ ያደረጉ ህጻናት ቁጥር ከ25,000 በላይ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጥጋቡ ሹመይ ነግረውናል፡፡ ጋብቻ ከ2,500 በላይ፣ ፍቺ 853 ፣ ሞት 1,258 ፣ ጉዲፈቻ ደግሞ 58 በአጠቃላይ 30,500 ኩነቶች ባጋጠሙ በወቅታቸው መመዝገባቸውን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡ በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ 3 ወራት በወቅቱ በዘገየና ጊዜ ገደቡ ባለፈ 172,011 ወሳኝ ኩነቶች መመዝገባቸውን ከኤጀንሲው ሰምተናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… ማርታ በቀለ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇�
5 days ago1 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page








