top of page

ነሀሴ 30 2017 - ሁለተኛው የአፍሪካ የወጣቶች የአየር ንብረት ጉባኤ በአድዋ ሙዝየም እየተካሄደ ነው።

  • sheger1021fm
  • 3 days ago
  • 1 min read

አፍሪካዊያን ወጣቶች በአየር ንብረት ለውጥና በሌሎች ምክንያቶች ለስደት እየተዳረጉባት መሆኑን በጉባኤው ተነስቷል።


ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አፍሪካ ወደ ከባቢ አየር የምትለቅቀው በካይ ጋዝ ከአጠቃላዩ ድርሻው ከ4 በመቶ ዝቅ ያለ መሆኑን ተናግረዋል።


ነገር ግን አፍሪካ በድርቅ፣ ጎርፍ፣ በምግብ ዋስትና አለመረጋገጥ፣ በዝናብ እጦት እና ሌሎችም ችግሮች ወጣቶቿ የስደትና ሌሎችም ችግሮች ተጋፋጭ እየሆኑ ነው ተብሏል።

ree

አፍሪካውያን ወጣቶች ላይ በስራ ፈጠራ በወጣቶች የነገ መሪነት ላይ በስፋት መስራት ይገባል ያሉት አቶ ተመስገን የአዲስ አበባ የአፍሪካ ወጣቶች ዲክላሬሽን ይዘጋጃልም ብለዋል።


የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ አፍሪካውያን ወጣቶች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ለስደትና ለሌሎች ችግሮች እየተጋለጡ ቢሆንም የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችን እየሰሩ የሚገኙ ወጣቶችም አሉን በማለት ተናግረዋል።


በውይይቱ እየተሳተፉ ያሉ ወጣቶች በአየር ንብረት ለውጥ ፍትህ እንፈልጋለን ፍትህም ዛሬ ይሰጥ ሲሉ በተደጋጋሚ ሲናገሩ አድምጠናል።


ኢትዮጵያ በአድዋ ጦርነት የውጪ ወራሪን ተባብራ ድል እንዳደረገች አፍሪካውያንም በህብረት የአየር ንብረት ለውጥን በመተባበር ክንድ መፋለም አለባት ፣ የአየር ንብረት ለውጥ በዚሁ ከቀጠለ ከአሁኑ በባሰ መንገድ አፍሪካውያን ለስደት ይዳረጋሉ ተብሏል።


በረከት አካሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page