ነሀሴ 28 2017 - የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ከዚህ በኋላ ለባቡር ሾፌርነትና ቴክኒሺያኖች ስልጠና ማረጋገጫ ወደ ቻይና አልሄድም አለ
- sheger1021fm
- Sep 3
- 1 min read
ምድር ባቡሩ ከዚህ ቀደም ለቻይና የባቡር ቴክንሺያኖችና የሰው ሀይል ስልጠና በ6 ዓመት ውስጥ ብቻ 357 ሚሊዮን ዶላር አውጥቻለሁ ፤ አሁን ግን በሀገር ቤት የብቃት ማረጋገጫ መስጠት የሚያስችለኝን አሰራር ጀምሬያለሁ ብሏል፡፡
ተቋሙ ከዚህ ቀደም ለባቡር ሾፌሮ ፤ ኦፕሬሽን ፤ ስልጠና እና ጥገና እንዲሁም አጠቃላይ ባቡሩ ውሎ እስኪያድርበት ላለው ጉዞ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚቀረጥፍብኝን አሰራርን አስቀርቻለሁ ብሏል።
ምድር ባቡሩ ይህን አገልግሎት መጀመሬ ከዚህ ቀደም ከቻይና ለሚመጡና ይህንኑ ተግባር ላከናወኑ ቡድኖች ከ350 ሚሊየን ዶላር በላይ ማውጣቴን ያስቀርልኛል ብሏል።
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. https://www.mixcloud.com/ShegerFM/680/
ተህቦ ንጉሴ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
Comments