በኢትዮጵያ የንግዱን ማህበረሰብ እየገጠሙ ካሉ ችግሮች 40 በመቶ ያህሉ ከገንዘብ አቅርቦት ጋር የተገናኙ ናቸው ተባለ ።
- 2 hours ago
- 1 min read
መጋቢት 3/2018
በኢትዮጵያ የንግዱን ማህበረሰብ እየገጠሙ ካሉ ችግሮች 40 በመቶ ያህሉ ከገንዘብ አቅርቦት ጋር የተገናኙ ናቸው ተባለ ።
በአጠቃላይ በኢትዮጵያ 2 ሚሊየን የሚጠጉ ጥቃቅን ፣ አነስተኛና መካከለኛ የንግድ ኢንዱስትሪ ተቋማት እንዳሉ ተነግሯል።
የእነዚህ ኢንዱስትሪ ባለቤቶችና ኢ-መደበኛ በሆኑ ሌሎች ንግዶች የተሠማሩ ሰዎች በአጠቃላይ የብድር ፍላጎታቸው በአገሪቱ ባሉ ሁሉም ባንኮችና የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ተቆጥቦ ከሚገኘው ገንዘብ ግማሽ ያህሉን ይሆናል ተብሏል።
በኢትዮጵያ ባሉ ባንኮችና የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ተቆጥቦ ያለ አጠቃላይ ገንዘብ 3.7 ትሪሊዮን ብር እንደሆነ የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት በካፒታል ሆቴል እያካሄደው ባለው ውይይት ላይ ሲነገር ሠምተናል።
በውይይቱ ላይ የንግዱ ማህበረሰብ ስለሚገጥመው የመስሪያ ቦታ አቅርቦት ችግርም ተነስቷል።
የመስሪያ ቦታ ማግኘት ብዙ ሂደትን ማለፍ የሚጠይቅ ተግባር እንደሆነ ተነግሯል።
አንድን ቦታ ህጋዊ በሆነ መንገድ በሊዝ የገዛ ግለሰብ በሚቀጥለው ቀን መልሶ መሸጥ ቢፈልግ 24 ሂደቶችን ወይም መስፈርቶችን ማለፍ ይጠበቅበታል ተብሏል።
ምክር ቤቱ "ቀልጣፋና አስተማማኝ የፋይናንስና የመስሪያ ቦታ አቅርቦት ለፈጣን ኢንቨስትመንትና ልማት" በሚል ባዘጋጀው መድረክ ላይ በተለያዩ ባለሞያዎች የመነሻ ፅሁፎች ቀርበዋል።
ታሳታፊዎችም ከብድር እና ከቦታ አቅርቦት ጋር በተገኘ ይታያሉ ያሏቸውን ጥያቄዎችም አንስተዋል።
ንጋቱ ረጋሳ





Comments