በየሳምንቱ 1 ሚሊዮን ሰዎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እየተመዘገቡ ነው ተባለ።
- 2 hours ago
- 1 min read
መጋቢት 1/2018
በየሳምንቱ 1 ሚሊዮን ሰዎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እየተመዘገቡ ነው ተባለ።
በአሁኑ ሰዓት በአጠቃላይ የፋይዳ መታወቂያ የተመዘገቡ ሰዎች ቁጥር 37.5 ሚሊዮን መድረሱን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ፅ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ዮዳሄ አርአያስላሴ ተናግረዋል።
ዋና ዳሬክተሩ ይህን ያሉት ፅ/ቤታቸው ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ጋር በመተባበር ለግል መገናኛ ብዙኀን ፋይዳ መታወቂያ በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።
እስከ መጪው ሰኔ ወር ድረስ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተመዝጋቢዎችን ብዛት 90 ሚሊዮን ለማድረስ ታቅዶ እየተሰራ እንደሆነ አቶ ዮዳሄ አስረድተዋል።
የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ለመልካም አስተዳደር፣ ለማህበራዊ እና ደህንነት ጉዳዮች ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው በፕሮግራሙ ላይ ሲነገር ሰምተናል።

በዚህም በጥቅል ሀገራዊ ምርት ወይንም GDP 6 በመቶ እንደሚያበረክትም ተጠቅሷል።
የባንክ አገልግሎቶችን ለማግኘት አና በመደበኛ አኮኖሚ ውስጥ ለመሳተፍ፣የቴሌኮም አገልግሎቶችን ለማግኘት፣የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ለማግኘት አንደ ቅድመ ሁኔታ በመሆን የማንነት ማጭበርበርን በመከላከል ዲጂታላይዝድ አግልግሎቶችን ለማቀላጠፍ መታወቂያው እንደሚጠቅም ሲነገር ሰምተናል።
ከዚህ በተጨማሪም በሰነዶች ምዝገባ እና ማረጋገጫ አገልግሎት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማግኘት፣ ተማሪዎች አንድ ዋና የተማሪ መታወቂያ፣ የሀገር አቀፍ ፈተና መለያ አንዲሁም እንደ ቤተ-መጻህፍት አገልግሎት ያሉ የትምህርት አገልግሎቶችን ለማግኘት ያስችላል ተብሏል።
ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ ማንኛውም ስደተኞች ፋይዳ መታወቀያን በመጠቀም ሁሉንም በሀገሪቱ የሚገኙ አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ሌላኛው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጠቀሜታ መሆኑ ተጠቅሷል።
ይህ የፋይዳ መታወቂያ እነዚህንና ሌሎች በርካታ ጥቅሞች ቢሰጥም ምዝገባውን በጥርጣሬ የሚያዩት ፣ እንደ CCTV ካሜራ የሚመለከቱ አሉ ተብሏል።
ይህንንን የግንዛቤ ችግር ለመፍታትና በመጪው ሰኔ 90 ሚሊዮን ሰዎች ለመመዝገብ ሚዲያዎች ግንዛቤ በመፍጠር አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ተጠይቋል።
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments