የዱር እንስሳት አደንና ሽያጭ ፣ የፓርኮች መራቆት፣ ግጭት እና የፋይናንስ እጥረት የዱር እንስሳትና የፓርኮች ጥበቃ ስራ ፈተና ሆኗል ተባለ።
- 2 hours ago
- 1 min read
መጋቢት 3/2018
የዱር እንስሳት አደንና ሽያጭ ፣ የፓርኮች መራቆት፣ ግጭት እና የፋይናንስ እጥረት የዱር እንስሳትና የፓርኮች ጥበቃ ስራ ፈተና ሆኗል ተባለ።
ይህ የተባለው የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን የተመሰረተበትን 60ኛ ዓመት ዛሬ ሲያከብር ነው።
የቱሪዝም ሚኒስትር ድኤታው አቶ ስለሺ ግርማ የኢኮ ቱሪዝምና የብርቅዬ እንስሳት ቱሪዝም ኢትዮጵያ ውስጥ እየሰፋ መጥቷል ብለዋል።
ላለፉት 60 ዓመታት ህገወጥ የዱር እንስሳት አደንና ሽያጭ፣ የፓርኮች መራቆት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የፋይናንስ እጥረት ዘርፉን ሲገጥሙት የነበሩ ችግሮች ናቸው ተብሏል።

የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኩመራ ዋቅጅራ በኢትዮጵያ 30 ፓርኮች፣ ከ90 በላይ ጥብቅ ስፍራዎች ስለመኖራቸው ተናግረዋል።
ከነዚህ ውስጥ የባሌ ብሔርራዊ ፓርክና ሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የአለም ቅርስ ተብለው በተባበሩት መንግስታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) የተመዘገቡ መሆናቸውን አስታውሰዋል።
ፓርኮቹና የዱር እንስሳቱ እየገጠማቸው ስላለው ችግር ያነሱት ሀላፊው የዱር እንስሳቱና ፓርኮቹ የበለጠ እንዲጠበቁ የአካባቢው ማህበረሰብ ከዚያ ተጠቃሚ መሆን አለበት ተብሏል።
በረከት አካሉ




Comments