top of page

በጋሞ ዞን ሰሞኑን በተከሰተው የመሬት መንሸራተት እና የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 64 መድረሱ ተነገረ።

  • 1 hour ago
  • 1 min read

መጋቢት 3/2018


በጋሞ ዞን ሰሞኑን በተከሰተው የመሬት መንሸራተት እና የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 64 መድረሱ ተነገረ።


የተጎዱትን በህይወት የማትረፉ ስራ ከዚህ በውሃላ ብዙም ተስፋ የለውም፣ቀሪ የአስከሬን ፍለጋ ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ ነው ተብሏል።


የሟቾቹ ቁጥር 52 ስለመድረሱ አስቀድመን ነግረናችሁ የነበረ ሲሆን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የተጨማሪ ሰዎች አስክሬን መገኘቱን ተናግሯል።


እስካሁን አስከሬናቸው የተገኘ የሟቾች ቁጥርም 64 ደርሷል ብሏል።


የዞኑ ፖሊስ መምሪያ በአካባቢው ነዋሪ የነበሩና በአደጋው የጠፉ ሰዎች ቁጥር 128 መሆኑን ተናግሯል።



እስካሁን ባለው መረጃ ከዚህ ውስጥ የ64ቱ ሰዎች አስክሬን መገኘቱን የጋሞ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር አብረሀም ቡሔ ተናግረዋል።


ኢንስፔክተሩ በሶስት ወረዳዎች አደጋ ተመዝጋቧል ያሉ ሲሆን ከሁሉም ከባድ አደጋ ያስተናገደው ዳጮ ባባ የተባለው ወረዳ ነው ብለዋል።


ከዚሁ ወረዳ ብቻ የ59 ሰዎች አስክሬን መገኘቱን ገልጸው የሌሎች አምስት ሰዎች አስከሬን ደግሞ በቦንኬና ከምባ ዙሪያ ወረዳ መገኘቱ ተነግሯል።


በማህበራዊ ሚዲያዎች የሟቾችን ቁጥር በተመለከተ የተለያየ መረጃ እየቀረበ ሲሆን ይህም የተሳሳተና የተዛባ መረጃ ነው ብለዋል።


ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች በህይወት የማግኘቱ ተስፋም እየተመናመነ መጥቷል ተብሏል።


ከዚህ በኋላ ቀሪ የጠፉ ሰዎችን አስክሬን ፍለጋ ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራም የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ተናግሯል።

Recent Posts

See All
በኢትዮጵያ የንግዱን ማህበረሰብ እየገጠሙ ካሉ ችግሮች 40 በመቶ ያህሉ ከገንዘብ አቅርቦት ጋር የተገናኙ ናቸው ተባለ ።

መጋቢት 3/2018 በኢትዮጵያ የንግዱን ማህበረሰብ እየገጠሙ ካሉ ችግሮች 40 በመቶ ያህሉ ከገንዘብ አቅርቦት ጋር የተገናኙ ናቸው ተባለ ። በአጠቃላይ በኢትዮጵያ 2 ሚሊየን የሚጠጉ ጥቃቅን ፣ አነስተኛና መካከለኛ የንግድ ኢንዱስትሪ ተቋማት እንዳሉ ተነግሯል። የእነዚህ ኢንዱስትሪ ባለቤቶችና ኢ-መደበኛ በሆኑ ሌሎች ንግ

 
 
 
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page