top of page

ከመጋቢት አጋማሽ ጀምሮ በ16 ጉዳዮች ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ ማካሄድ እንደሚጀምር ምርጫ ቦርድ ተናገረ።

  • 12 minutes ago
  • 1 min read

የካቲት 30/2018  

 

ከመጋቢት አጋማሽ ጀምሮ  በ16 ጉዳዮች ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ ማካሄድ እንደሚጀምር ምርጫ ቦርድ ተናገረ።

 

ቦርዱ ይህን ያለው ባለፈው ቅዳሜ በኢዲስ ኢንትርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር የሲቪል ማህበረሰብ ደርጅቶች ለዲሞክራሲያዊ ምርጫ ያላቸው ድርሻ በሚል ርዕስ በተሰናዳ የወይይት መድረክ ላይ ነው።

 

ነጻ፣ ፍትሐዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ አካታች እና ታዓማኒ ምርጫ ለማካሄድ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምን እያሰራ ነው? የሚል ጥያቄ በወይይቱ ላይ ለምርጫ ቦርድ ቀርቧል።

 

ቦርዱን ወክለው በውይይቱ ላይ የታደሙት የምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ነዋይ የመራጮች ምዝገባ በአንዳንድ ክልሎች መጀምሩን እና የዕጩዎች መዝገባ መጠናቀቁን ተናግረዋል።

 

አቶ ተስፋዬ ነዋይ ዘንድሮ ቦርዱ እሰራለሁ ያለው ትልቁ ስራ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚከራከሩት መድረክ ማዘጋጀት እንደሆነ ጠቁመዋል።

 


አሁን በቴሌቪዥኖች የሚተላለፍ የተለያዩ የክርክር መድረኮች መኖራቸውን ያስታወሱት ምክትል ሰብሳቢው እነዚህ መድረኮች ሚዲያዎቹ በራሳቸው ተነሳሽነት የሚያደርጓቸው ክርክሮች ናቸው፤ የራሳቸው ደካማ እና ጠንካራ ጎን አላቸው ሲሉ አስረድተዋል።

 

በዚህም ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ 47 የሚሆኑ ፓርቲዎች የሚከራከሩበት "በጣም የተደራጃ መድረክ" ለህዝቡም በቂ መረጃ የሚሰጥ "ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዳቀረቡትም እጩ ብዛት የክርክር የሚያደርጉበት መድረክ እያዘጋጀን ነው ሲሉ አቶ ተስፋዬ ተናግረዋል።

 

ቦርዱ ከመጋቢት አጋማሽ ጀምሮ በ16 ርዕስ ጉዳዬች ላይ የሚዘጋጁ የክርክር መድረኮችን ለህዝቡ መገናኛ ብዙሃን ጨምሮ በተለያዩ ቋንቋዎች እና  ዘዴዎች ለህብረተሰቡ ተደራሽ ይደረጋል ብሏል።

 

ይህም መራጩ ስለ ፓርቲዎቹ "በቂ ግንዛቤ" ኖሮት እንዲመርጥ ለማድረግ ያግዛል ሲል ምርጫ ቦርድ አክሏል።

 

ያሬድ እንዳሻው

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

YouTube : https://shorturl.at/18TS1                   

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page