top of page

ጥብቅ እንደሆነ የሚነገርለት የኢትዮጵያ የባንኮች ብድር አሰጣጥ ሥርዓት አሁንም ሊሻሻሉ የሚገቡ ጉዳዮች ያሉበት ነው ተባለ።

  • 5 hours ago
  • 1 min read

ሐምሌ 27 2018


ጥብቅ እንደሆነ የሚነገርለት የኢትዮጵያ የባንኮች ብድር አሰጣጥ ሥርዓት አሁንም ሊሻሻሉ የሚገቡ ጉዳዮች ያሉበት ነው ተባለ።


ሰዎች ከዚህ በፊት የወሰዷቸውን ብድሮች የከፈሉበት መልካም ታሪክ እየታየ ከባንኮች ገንዘብ የሚያገኙበት ሥርዓት በኢትዮጵያም ሊለመድ እንደሚገባ የዘርፉ ባለሙያዎች ተናግረዋል።


በኢትዮጵያ የባንኮች ብድር መመርያና ፖሊሲ ከባንክ ባንክ የተለያየ በመሆኑ የብድር አሰጣጥ ሂደቱም በተወሰነ መልኩ ከተቋም ተቋም እንደሚለያይ ተነግሯል፡፡


ከብድር ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ ያሉ ባንኮች ዋና ዋና የብድር መስፈርቶችን ያስቀምጣሉ፡፡


ከእነዚህ መካከል የብድር መያዣ ፣ ካፒታል፣ የስራ ዕቅድ፣ የገንዘብ አቅም ፣ የብድር ስጋት ደረጃ እንዲሁም አስፈላጊ የሰነዶችና ቅድመ ሁኔታዎችን ማሟላት የሚሉት እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡


ሆኖም እነዚህን ነገሮች በዘመናዊ መልክ ማረጋገጥ የሚቻልበት መንገድ ቢዘረጋ ሲሉ በጉዳዩ ላይ ያነጋገር ናቸው የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡


ከጥብቅ መስፈርቶቹ መካከል አንዱ የብድር ታሪክ ሲሆን እነዚህን እና የተበዳሪው አቅም ምን ድረስ ነው የሚለውን ሌሎች ሀገራት እንዴት እንደሚያስኬዱት የምጣኔ ሃብት ባለሙያው ዘሪሁን ጴጥሮስ ነግረውናል፡፡


በሌሎች ሃገራት እያንዳንዱ ሰራተኛ በቀጥታ በበይነ መረብ አማካኝነት እንደሚመዘገብና የተበዳሪው የገንዘብ አጠቃቀሙ፣ የውጪ አጠቃቀም ፣ ገቢው ምን ያህል ነው፣ የሚለው እያንዳንዱ እንቅስቃሴው በካሜራ በመታገዝ እንደሚጠና አስረድተዋል፡፡


ከዚህ በመነሳት እንደ ሀገር ቢሰራበት ያሉትንም ሀሳብ አክለዋል፡፡


ይህ ሁሉ የሚሆነውና መዘመን ያስፈልገዋል የሚባለው ሊመጣ የሚችለውን አደጋ ለመለየትና ቀድሞ ለመከላከል እንደሆነ ባለሙያው ዘሪሁን ጴጥሮስ ተናግረዋል፡፡


በቅርቡ በቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ጥናታቸውን ያቀርቡት በዩንቨርስቲው የአካውንቲንግ እና ፋይናንስ መምህርና ተመራማሪ ነዋይ አያሌው ትልልቅ የሚባሉ ባንኮች ኪሳራ ሊያስከትል የሚችል የብድር አሰጣጥ አሰራር እንደሚከተሉ በጥናታቸው ማረጋገጫቸውን ነግረውናል፡፡


ሌላኛው የምጣኔ ሃብት ባለሙያና በባንኩ ዘርፍ ልምድ ያላቸው ሲሳይ ክፍሉ በበኩላቸው ባንኮች ራሳቸው ለኪሳራ አያጋልጡም ለትርፍ እንደመቋቋማቸው ምን ላይ መስራት እንዳለባቸው ያውቃሉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡


ለሚሰጡ ብድሮች ባንኩንም በማይጎዳ መልኩ ተበዳሪውም ተጠቃሚ እንዲሆን ይህንን የተመለከቱ ፖሊሲዎች በሚውጡበት ጊዜ ከሚደረጉ ጥናቶችና የምርምር ውጤቶች በመነሳት መዘመንና መሻሻል ያለባቸውን በመለየት ቢሰራበት ሲሉ ባለሙያዎቹ ምክር ሃሳባቸውን አስቀምጠዋል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ....



ማርታ በቀለ

Recent Posts

See All
ታሪክን_የኋሊት

ባለ ብዙ ገድሉ አፍሪካ አሜሪካዊ ስፖርተኛ ጄሲ ኦውንስ በዘመኑ ድንቅነቱን አስመስክሯል፡፡ በተለይም ከ90 አመታት በፊት በጀርመን በተካሄደው የበርሊን ኦሎምፒክ ታላቁን ታሪክ የሰራበት ነበር፡፡ በዚያ ኦሎምፒክ ኦውንስ በተለያዩ ስፖርታዊ ክንውኖች አራት የወርቅ ሜሊያዎችን አጥልቋል፡፡ በዚህ ኦሎምፒክ በመቶ ሜትር ሩጫ

 
 
 
በኤሌክትሪክ እጦት ምክንያት የእለት ተእለት ተግባራቸውን መከወን ዳገት እንደሆነባቸው የምዕራብ ጎጃም ዞን ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡

ሐምሌ 27 2018 በኤሌክትሪክ እጦት ምክንያት የእለት ተእለት ተግባራቸውን መከወን ዳገት እንደሆነባቸው የምዕራብ ጎጃም ዞን ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትክ አገልግሎት በበኩሉ ማህበረሰቡ የሚያነሳው ችግር ተገቢ ነው እሱን ለማስተካከልም እየሰራሁ ነው ብሏል፡፡ ከ1.3 ሚሊየን በላይ ህዝብ ያለበት የምዕራብ ጎ

 
 
 
የመኖሪያ ቤት ችግር በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ የብዙዎች ራስ ምታት ሆኖ ቀጥሏል።

ሐምሌ 27 2018 የመኖሪያ ቤት ችግር በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ የብዙዎች ራስ ምታት ሆኖ ቀጥሏል። በሪል እስቴት ዘርፍ ከተሰማሩ አልሚዎች መካከል አንዱ የሆነውና የቤት ችግርን ለመፍታት እሰራለሁ የሚለው አባይ ሆምስ ሪል እስቴት፤ ከሰሞኑ በ2 ቢሊዮን ብር የግንባታ ወጪ አዲስ የመኖሪያ ህንፃ ፕሮጀክት ይፋ አድርጓ

 
 
 
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page