top of page

በኢትዮጵያ ተላላፊ ባለሆኑ እንደ ልብ ያሉ ሕመሞች ምክንያት የሚመጣ የጤና ችግር ለሀገሪቱ የጤና ሥርዓት ተጨማሪ ሥጋት ሆኗል ተባለ።

  • 1 day ago
  • 2 min read

ሐምሌ 28 2018


በኢትዮጵያ ተላላፊ ባለሆኑ እንደ ልብ ያሉ ሕመሞች ምክንያት የሚመጣ የጤና ችግር ለሀገሪቱ የጤና ሥርዓት ተጨማሪ ሥጋት ሆኗል ተባለ።


ከልብ ሕመም ጋር በተያያዘ የሚደርስ የጤና ቀውስን ለመቀነስ ሕክምናው እንዲሁም ቅድመ - መከላከሉ ላይ በስፋት መሠራት አለበት ተብሏል።


ከልብ ሕክምና ተደራሽነት፣ የጤና ፖሊሲን ማሻሻል እና ምርምር ላይ የሚሠራው የፓን አፍሪካን የልብ ሕክምና ማኅበር ሰሞኑን በአዲስ አበባ ባካሄደው ዓመታዊ ጉባኤ ከልብ ሕመም ጋር የተገናኙ የጤና ችግሮች የአፍሪካ ከፍተኛ የጤና ሥጋት እየሆኑ ነው ብሏል።


ኢትዮጵያን ጨምሮ በአህጉሪቱ ከልብ ሕክምና ጋር በተገናኘ ያሉ ፈተናዎችን በመለየት፣ ሰፊ የጥናትና ምርምር ሥራዎች እና የፖሊሲ ማሻሻያ እንዲደረግ ለመንግሥታት ግብዓት የሚያቀብል ውይይት እንደሆነ የነገሩን የኮንፈረንሱ ሊቀመንበር እንዲሁም ከፍተኛ የልብ ሕክምና ስፔሻሊስት የሆኑት ፕሮፌሰር ከበደ ኦሊ ናቸው።


ከልብ ሕመም ጋር ተያይዘው የሚከሰቱ ሌሎች ተላላፊ ያልሆኑ ሕመሞች በቂ የሕክምና አገልግሎት አለመኖር ተጨማሪ ችግር እየሆነ መምጣቱንም ፕሮፌሰር ከበደ ተናግረዋል።


የኢትዮጵያ የልብ ሕክምና ማኅበር ፕሬዝዳንት እና የውስጥ ደዌ እና የልብ ሕክምና ሰብስፔሻሊስት የሆኑት ዶክተር ናትናኤል ታዬ በበኩላቸው፣ የልብ ሕመምን ጨምሮ ሌሎች ተላላፊ ያልሆኑ ሕመሞች እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ታዳጊ ሀገራት ለሕክምና የሚጠይቁት ወጪ ከፍተኛ በመሆኑ ቀድሞ መከላከሉ ላይ መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል።


ከጊዜ ወደ ጊዜ ጫናው እየጨመረ የመጣውን የልብ እንዲሁም ተያያዥ ሕመሞች ለመከላከልና የሕክምና ሥራውን ለማስፋፋት ምን እየተሠራ ነው? ስንል የጠየቅናቸው በጤና ሚኒስቴር የሚኒስትር ዴኤታ ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ስለሺ ጋሮማ፣ ዓለም አቀፍ እንዲሁም በኢትዮጵያ ደረጃ የልብ ሕመም ጫና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረና ብዙ ችግር ያደረሰ መሆኑን ጠቅሰዋል።


ለዚህም በሽታውን ለመከላከል በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች አሉ፤ ፖሊሲዎችን በመቅረጽ፣ በአመጋገብ እና በአካላዊ እንቅስቃሴ ዙሪያ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ቀድሞ ለመከላከል በፌደራል ደረጃ የወጡ የአፈጻጸም መመሪያዎችን ወደ ክልል በማውረድ በጤና ሚኒስቴር በኩል እየተሠራ ነው ብለዋል።


በኢትዮጵያ እንደ ካንሰር፣ ልብ፣ ስኳር እና ሌሎች ተላላፊ ባልሆኑ ሕመሞች ምክንያት የሚመጣው የጤና ችግር በከፍተኛ ፍጥነት መጨመሩንና ከሚከሰቱ ሞቶች በእነዚህ ሕመሞች የሚመጣው ከ40 በመቶ በላይ የሚሆነውን እንደሚያዝ ተገልጿል።


ከነዚህ ውስጥ ደግሞ የልብና ደም ሥር በሽታዎች ለብቻቸው ከፍተኛውን ቁጥር እንደሚይዙ የዓለም ጤና ድርጅት ጥናት ያሳያል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ...



ምህረት ስዩም

Recent Posts

See All
እንደ ጣና ያሉ ሀይቆችና የውሃ አካላት ላይ ተንሰራፍቶ ከሚገኘው የእምቦጭ አረም የነዳጅ ምርቶችን ለማምረት ይሰራል ከተባለ ከአምስት አመት በላይ ሆኖታል።

ሐምሌ 29 2018 እንደ ጣና ያሉ ሀይቆችና የውሃ አካላት ላይ ተንሰራፍቶ ከሚገኘው የእምቦጭ አረም የነዳጅ ምርቶችን ለማምረት ይሰራል ከተባለ ከአምስት አመት በላይ ሆኖታል። ይተገበራል በተባለው ፕሮጀክትም ነጭ ጋዝ፣ ቤንዚን ፣ኪሮሲን፣ የአውሮፕላን ነዳጅ እና ሚቴን ማምረት የሚለው ይገኝበታል ። ተረፈ ምርቱ ከነዳጅ

 
 
 
ኢትዮጵያ ሁለት ዓይነት የመሬት አስተዳደር ሥርዓትን እንደምትከተል ይነገራል::

ሐምሌ 29 2018 ኢትዮጵያ ሁለት ዓይነት የመሬት አስተዳደር ሥርዓትን እንደምትከተል ይነገራል:: ይህም የከተማ የመሬት አስተዳደር ሥርዓትና የገጠር የመሬት አስተዳደር ሥርዓት ተብሎ እንደሚጠራም ሰምተናል:: በዚህም የከተማው በአንድ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት የገጠሩም እንዲሁ በሌላ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት እየተመራ ይገኛል

 
 
 
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page