top of page


የአዲስ ቄራዎች ድርጅት አካባቢውን መበከል ካላቆመ ካለበት ቄራ አካባቢ እንዲነሳ የሚል የፍርድ ውሳኔ አፈፃፀም እንደተከፈተበት ተሰምቷል
ህዳር 5 2018 አካባቢን በመበከል በነዋሪው ላይ የጤና ጉዳት እያደረሰ ነው በሚል ክስ ቀርቦበት የነበረው የአዲስ ቄራዎች ድርጅት አካባቢውን መበከል ካላቆመ ካለበት የቄራ አካባቢ እንዲነሳ የሚል የፍርድ ውሳኔ አፈፃፀም እንደተከፈተበት ተሰምቷል፡፡ ቄራዎች ከአካባቢው ይነሳል አይነሳም የሚለውን ለመወሰን ለፊታችን ህዳር 15 በፍርድ ቤት ቀጠሮ ተሰጥቷል ተብሏል፡፡ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ከ30 ዓመታት በላይ አጥንት፣ደም፣ ቁርጥራጭ ስጋና መሰል የእርድ ተረፈ ምርቶችን በመልቀቅ አካባቢውን ሲበክል ቆይቷል በሚል ቁም ለአካባቢህ በተባለው ሃገር በቀል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት በፍርድ ቤት ክስ ቀርቦበት እንደነበር ይታወሳል፡፡ ፍርድ ቤቱም ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ በሰጠው ውሳኔ የቄራዎች ድርጅት በሚለቅቀው በካይ ፈሳሽ፣ጠጣርና ጋዝ የነዋሪ
32 minutes ago2 min read


ሬፍሌክስሎጂ (Reflexology) ምንድነው?
ሬፍሌክስሎጂ (Reflexology) ምንድነው? በጥንታዊ ግብጻውያን ፣ ቻይና እና ህንድ ውስጥ በባህላዊ መንገድ እንደተጀመረ የሚነገርለት ሬፍሌክስሎጂ በ1900 በተደረገ ጥናት መሰረት የውስጥ እግር ላይ እያንዳንዱን የሰውነትን ክፍልን የሚወክል ነርቭ እንዳለ በሳይንስ ተረጋግጧል ይላሉ። ሬፍሌክስሎጂ (Reflexology) በእግር ፣ በእጅ መዳፍ እና በጆሮ አከባቢ የሚገኙ የነርቭ ጫፎችን በማሸት የተለያዩ የሰውነት ክፍሎች ጋር የሚደርስ በሳይንስ የተረጋገጠ አጋዥ ህክምና እንደሆነ የሬፍሌክስሎጂ ባለሙያ የሆኑት ብርሃኑ ጣሰው ይናገራሉ። ሳይንሱ እንደ ደም ግፊት ፣ ካንሰር ፣ ስኳር የመሳሰሉ ክሮኒክ ካልሆኑ በሽታዎች በስተቀር ሬፍሌክስሎጂ ከ8 እስከ 12 ዙር ቢታሹ እንደሚመክር አስረድተው ደም ግፊት ያለበት ሰው ግን አንገቱ አከባቢ ጫና ፣ ራስ
54 minutes ago2 min read


ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ስምምነት ምክንያት የውጪ ባለሃብቶች ለኢንቨስትመንት እየመረጧት ነው ተባለ
ህዳር 5 2018 ኢትዮጵያ ከወር ግድም በፊት በይፋ በተቀላቀለችው የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ስምምነት ምክንያት የውጪ ባለሃብቶች ለኢንቨስትመንት እየመረጧት ነው ተባለ። በስምምነቱ መሰረት ወደ ተለያዩ ሀገራት የሚላኩ ምርቶች ጥራታቸውን የጠበቁ ስለመሆናቸው ጥብቅ የማረጋገጥ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ነግሮናል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠናን ባለፈው መስከረም ወር መጨረሻ በይፋ መቀላቀሏ ይታወሳል። ወደ አራት የአፍሪካ ሀገራት ምርቶችን በአየር እና በየብስ ትራንስፖርት በመላክ ነው የንግድ ቀጠናውን የተቀላቀለችው። በአየር ትራንስፖርት የተላኩት ስጋ እንዲሁም የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች ሲሆኑ ፤በየብስ ትራንስፖርት ደግሞ የተላኩት ቡና፣ የጥራጥሬ ምርቶችና የቅባት እህሎች ናቸው። ኬንያ
2 hours ago2 min read


የኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚገኙ ሠራተኞች መብታቸው ለማረጋገጥ የሚደረገው ክትትል እንደሚጠናከር የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ተናገረ
ህዳር 5 2018 በተለያዩ የኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች የሚገኙ ሠራተኞች መብታቸው ተከብሮ እየሰሩ ስለመሆናቸው ለማረጋገጥ የሚደረገው ክትትል እንደሚጠናከር የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ተናገረ። ከሠሞኑ በሃዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በአንድ ኢትዮጵያዊ ሠራተኛ ላይ ድብደባ የፈጸመ አንድ የውጪ ዜጋ እና የቅርብ ሃላፊው የስራ ውላቸው ተቋርጦ ከሀገር እንዲወጡ መደረጉን ኮርፖሬሽኑ ጨምሮ ተናግሯል። በኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች መብታቸው ተከብሮ እየሰሩ ስለመሆናቸው ለማረጋገጥ ፤ የሚደረገው ክትትል በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ተናግሯል። ኮርፖሬሽኑ ከሠሞኑ በሃዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በአንድ ኢትዮጵያዊ ሠራተኛ ላይ የተፈጸመውን ጥቃት መ
2 hours ago1 min read


በኢትዮጵያ ከሚወለዱ 10,000 ህጻናት 83 ቱን የሚያጠቃው የነርቭ ዘንግ የአፈጣጠር ችግር
ህዳር 5 2018 በኢትዮጵያ ከሚወለዱ 10,000 ህጻናት 83 ቱን የሚያጠቃው የነርቭ ዘንግ የአፈጣጠር ችግር በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ30,000 - 50,000 ህጻናት ከነርቨ ዘንግ የአፈጣጠር ችግር (Spina Bifida) ጋር ይወለዳሉ፡፡ በዚህም ምክንያት አብዛኞቹ ሕጻናት ለዕድሜ ልክ የአካል ጉዳት አለፍ ሲልም ለሞት ይዳረጋሉ፡፡ የነርቭ ዘንግ የአፈጣጠር ችግር ምንድነው? ስፓይና ቢፊዳ (Spina bifida) ማለት ከነርቨ ዘንግ የአፈጣጠር ችግሮች ውስጥ አንዱ ሲሆን የአከርካሪ አጥንትና የህብለሰረሰር በአግባቡ አለመዘጋት(ክፍተት) ነው። በአብዛኛው ጊዜ ስፓይና በፊዳ ያለባቸው ሕጻናት ፈሳሽ በአጎላቸው ወስጥ ስለሚከማች ሃይደሮ ሴፋለስም ያጋጥማቸዋል። ሃይድሮ ሴፋለስ ምንድነው? ሃይድሮ ሴፋለስ ማለት በጭንቅላት ውስጥ ከመጠን በላይ የፈሳሽ ክምችት ሲ
2 hours ago3 min read


በመምህርነት ሞያ ለሚሰለጥኑ ሁሉም መምህራን የምልክት ቋንቋ፣ የብሬል ማንበብና መጻፍ እንዲሁም የልዩ ፍላጎት ትምህርትን እንዲሰለጥኑ የሚያስገድድ ረቂቅ መመሪያ ተዘጋጀ፡፡
ህዳር 5 2018 በመምህርነት ሞያ ለሚሰለጥኑ ሁሉም መምህራን የምልክት ቋንቋ፣ የብሬል ማንበብና መጻፍ እንዲሁም የልዩ ፍላጎት ትምህርትን እንዲሰለጥኑ የሚያስገድድ ረቂቅ መመሪያ ተዘጋጀ፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀው ይኸው መመሪያ የልዩ ፍላጎት ( #አካቶ ) ትምህርት ማስፈጸሚያ መመሪያ ይሰኛል፡፡ በዚህ ባለ 25 ገጽ ረቂቅ መመሪያ መሰረት ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰጠው የትኩረት መስክና የስልጠና ፕሮግራም ድልድልን መሰረት ያደረገ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ የምልክት ቋንቋ፣ የንግግር ወጌሻ እና የፊዚዮቴራፒ ስልጠና እንደሚሰጥ ተደንግጓል፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በተመለከተ ደግሞ በመምህርነት ሞያ ለሚሰለጥኑ ሁሉም መምህራን የምልክት ቋንቋ፣ የብሬል ማንበብና መጻፍ እንዲሁም የልዩ ፍላጎት ትምህርት ማስተዋወቂያ
5 hours ago2 min read


የአንደኛው እምነት ተግባር የሌላኛው መብት እንዳይጥስ መንግስት ምን ማድረግ አለበት?
ህዳር 4 2018 ሀይማኖትን መሰረት ያደረጉ ግድያዎች በተደጋጋሚ እየተፈፀሙ መሆኑን የሀይማኖቱ ተቋማት በሚያወጧቸው መግለጫዎች ይናገራሉ። የአንድ ሃይማኖት ተከታይ የሌላውን እንዳይጎዳ የአንደኛው እምነት ተግባር የሌላኛው መብት እንዳይጥስ መንግስት ምን ማድረግ አለበት? በጉዳዩ ላይ የህግ ባለሞያን ጠይቀናል። ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ማርታ በቀለ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s 🐦X
1 day ago1 min read


ባለፈው ዓመት ብቻ ከ700 በላይ ሰዎች ከህልፈት በኋላ፤ ብሌናቸውን ለመለገስ ቃል መግባታቸው ተነገረ፡፡
ህዳር 4 2018 ባለፈው ዓመት ብቻ ከ700 በላይ ሰዎች ከህልፈት በኋላ ብሌናቸውን ለመለገስ ቃል መግባታቸውን የኢትዮጵያ ደምና ህብረ ህዋስ ባንክ ተናገረ፡፡ የዓይን ብርሃናቸውን ላጡ ሰዎች ዳግም ብርሃን ለመለገስ ከበጎ ፈቃደኛ ለጋሾች የሚሰበሰብ የዓይን ብሌን ቁጥር ለመጨመር በህዳር ወር ጥረት ይደረጋል ተብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ምህረት ስዩም የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm 💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s 🐦
1 day ago1 min read


የሚበዙት ባንኮች ከመደበኛ ስራቸው ውጪ በሆኑ ሌሎች ተግባራት መሰማራታቸው
ህዳር 4 2018 የባንኮች በአቅምም፣ በአገልግሎት ጥራትም ልቀው የመገኘት ሀሳብ በየጊዜው ይነሳል። ባንኮች ወደፊት ለሚመጣው ፉክክር ዝግጁ መሆን አለባቸው ይባላል። በሌላ በኩል የሚበዙት ባንኮች ከመደበኛ ስራቸው ውጪ በሆኑ ሌሎች ተግባራት ሲሰማሩ ይታያል። በኢ-ኮሜርስ፣ በትምህርት ዘርፍ፣ በሎጅስቲክስና በሌላው መፎካከራቸው በዝቶ እየታየ ነው። የክፍያ ሥርዓትን ማገዝ የሚጠበቅባቸው ባንኮች፣ ሶፍትዌር አበልፅገው በተለያየ ንግድና አገልግሎት ውስጥ ሲሳተፉ ይታያል። ይህም የተቋቋሙበት ዓላማ ይህ ነው ወይ? የሚል ጥያቄን ያስነሳል። ባንኮች ከድንችና ሽንኩርት ሽያጭ እስከ ሎጅስቲክ ዘርፍ ገብተው ሲሰሩ ይታያል፡፡ የባንክ ስራውን ከማሳደግና ማቀላጠፍ ወደዚህ ዓይነት ስራ ውስጥ መግባታቸው ምን ይዞ ይመጣል? ባለሙያ ጠይቀናል። ሙሉ
1 day ago1 min read


በኢትዮጵያ በትራፊክ አደጋ ምክንያት የሚደርሰው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር አሁንም ከፍተኛ ሆኗል ተባለ።
ህዳር 4 2018 በኢትዮጵያ በትራፊክ አደጋ ምክንያት የሚደርሰው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር አሁንም ከፍተኛ ሆኗል ተባለ። ላለፋት 15 አመታት በኢትዮጵያ በተለይም በአዲስ አበባ የመንገድ ትራፊክ አደጋ ተጋላጭነትን ለመቀነስና መንስኤዎቹን ለመለየት እየሰራ መሆኑን ብሉምበርግ ፊላንትሮፒስ የተባለው አለም አቀፍ ተቋም ተናግሯል። ተቋሙ ከጆን ሆፕኪንስ ዩንቨርስቲና ከአዲሰ አበባ ዩኒቨርስቲ የህብረተሰብ ጤና ትምህርት ቤት ጋር በመሆን በመንገድ ትራፊክ አደጋ መንስኤዎች እና መፍትኤ ላይ ባሰናዱት አውደ ጥናት ነው ይህን የሰማነው። የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህብረተሰብ ጤና ትምህርት ቤት ከተቋማቱ በሚያገኘው ድጋፍ በፍጥነት፣ የደህንነት ቀበቶ አጠቃቀም፣ የሞተር ብስክሌት ቆብ አጠቃቀምና ጠጥቶ ማሽከርከር ላይ ችግሮችን በመለየት የመንገድ ትራፊክ አ
1 day ago2 min read


ህግ አውጪ ተቋማት በጥናትና ምርምር ለመደገፍ ይሰራል የተባለለት ተቋም ስራ መጀመሩን ተነግሯል
ህዳር 4 2018 እንደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያሉ ህግ አውጪ ተቋማት በጥናትና ምርምር ለመደገፍ ይሰራል፣ ለሰላምና ዲሞክራሲ ግንባታ እገዛ ያደርጋል የተባለለት ተቋም ስራ መጀመሩን ተነግሯል፡፡ እንደራሴዎች በተገኙበት ስራ መጀመሩን የተናገረው ብሪጅ ሪሰርችና ኢኖቬሽን የተባለ ድርጅት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ 18 የህግ አውጪ ምክር ቤቶችን በገለልተኝነት ሙያዊ የሆነ የአቅም ግንባታ ስራዎችን እሰራለሁ ብሏል፡፡፡ ህግ አውጪዎች ያሉባቸው ክፍተቶች ምንድናቸው? የሚለውን በመለየት በጥናትና ምርምር ለማገዝ መቋቋሙን የነገሩን የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ቃለ አብ ታደሰ(ዶ/ር) ናቸው፡፡ ተቋሙ ወደ ስራ ከገባ የመጀመሪያ የሆነውን ጥናት ቢያደርግም ወደፊት ሌሎች ምርምርና ጥናት የሚደረግባቸው ስራዎችን ከምክር ቤቱ ጋር እንደሚያደርግም አስረድተዋ
1 day ago1 min read


‘’የአዕምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ህፃናት ለማሰልጠን በልገሳ ከውጪ የገባ ኮምፒውተር በጉምሩክ ተይዞብኝ 6 ዓመት ሆነው’’ ራዕይ የህፃናት መርጃ
ህዳር 4 2018 የአዕምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ህፃናት ለማሰልጠን ሊውል የነበረ እና በልገሳ ከውጪ ሀገር የገባ ኮምፒውተር በጉምሩክ ተይዞብኝ 6 ዓመት ሆነው ሲል ራዕይ የህፃናት መርጃ ድርጅት ተናገረ፡፡ ጉምሩክ ኮሚሽን በጉዳዩ ላይ እስካሁን ምላሽ አልሰጠም፡፡ ከ300 በላይ በአዕምሮ እድገት ውስንነት እንዲሁም በኦቲዝምና በሌላም ምክንያት ልዩ ድጋፍ የሚሹ ህፃናትን እየደገፈ እንደሆነ የሚናገረው ድርጅቱ፤ የሚደግፋቸው ልጆች በአዲስ አበባ ከተማ ባሉ 7 የመንግስት ትምህርት ቤቶች ውስጥ የአካቶ ትምህርት እየተማሩ ጎን ለጎን የእደጥበብ ሙያንና ሌላውንም ተሰጧቸውን እንዲያዳብሩ ማድረጉን ተናግሯል፡፡ የድርጅቱ መስራችና ዳይሬክተር ፅጌ ጥበቡ(ዶ/ር) የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችን ጠርተው ስለ ስራው ባብራሩበት ወቅት ልጆቹ እንዲሰለጥኑበ
1 day ago2 min read


በጅንካ ከተማ ምንነቱ በመረጋገጥ ላይ ያለ የሄሞራጂክ ፊቨር በሚባል በሽታ 8 ሰዎች መጠርጠራቸውን ተነገረ።
ህዳር 3 2018 በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጅንካ ከተማ ምንነቱ በመረጋገጥ ላይ ያለ የሄሞራጂክ ፊቨር (Hemorrhagic Fever) በሚባል በሽታ 8 ሰዎች መጠርጠራቸውን ጤና ሚኒስቴር ተናገረ። የጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና ከክልሉ ጤና ቢሮ ጋር በመሆን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተመዘገበውን ይህንን የበሽታ መንስኤ ለማወቅ እና ተጨማሪ ስርጭትን ለመግታት እንዲሁም ለመቆጣጠር ፈጣን ምላሽ ሰጪ ቡድን ወደቦታው በመላክ የመስክ ግምገማዎች እና የላብራቶሪ ምርመራዎችን እያከናወነ መሆኑ ተነግሯል። በተጨማሪም የማህበረሰብ ቅኝት፣ የንከኪ ልየታ፣የቤት ለቤት ልየታ እንዲሁም የህከምና አገልግሎት አሰጣጥን እያጠናከረ ይገኛል ብሏል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሌላ ተጨማሪ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ፤ ለመከላከል የሚከተሉትን ምከረ-ሃሳቦች እና
1 day ago1 min read


ቁጥሩ ከግማሽ በላይ ቀንሶ እየተመናመነ ያለው ዋልያ አሁንም ማገገም አላሳየም ተባለ
ህዳር 3 2018 በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ የሚገኘውና ቁጥሩ ከግማሽ በላይ ቀንሶ እየተመናመነ ያለው ዋልያ አሁንም ማገገም አላሳየም ተባለ። ከቅርብ ወራት በፊት የተደረገ ድጋሚ ቆጠራ በፓርኩ የሚገኙ ዋልያዎች ብዛት አሁንም 306 መሆኑን አሳይቷል ተብሏል። ለዋልያ ቁጥር መመናመን አንዱ ምክንያት የሰሜኑ ጦርነት ነበር ተብሏል፡፡ በኢትዮጵያ ብቻ ከሚገኙ ብርቅዬ የዱር እንስሳት አንዱ የሆነው ዋልያ ቁጥሩ ከግማሽ በላይ ቀንሶ እየተመናመነ እንደሚገኝ ከዚህ ቀደም መነገሩ ይታወሳል፡፡ ከወራት በፊት በተደረገ የድጋሚ ቆጠራ በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ያሉ ዋልያዎች ብዛት አሁንም 306 እንደሆነ መረጋገጡን፤ በባለስልጣኑ የብሄራዊ ፓርኮች አስተዳደር መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶክተር አዳነ ፀጋዬ ነግረውናል። የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ባለበት አካባቢ የሚኖሩ
2 days ago1 min read


በኢትዮጵያ የተፈቀደላቸው የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች 89 መሆናቸውን ብሔራዊ ባንክ ተናገረ፡፡
ህዳር 3 2018 በኢትዮጵያ የገንዘብ ማስተላለፍ አገልግሎት እንዲሰጡ የተፈቀደላቸው የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች 89 መሆናቸውን ብሔራዊ ባንክ ተናገረ፡፡ ቀደም ሲል የገንዘብ ማስተላለፍ አገልግሎት እንዳይሰጥ ታግዶ የነበረውና ዋና መስሪያ ቤቱ በአሜሪካ ቨርጂኒያ ግዛት በፎልስ ቸርች የሚገኘው ራማዳ ፔይ(ካህ) በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ አጠቃላይ ግምገማ ከተካሄደ በኋላ በሕጋዊ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች ስም ዝርዝር ውስጥ ዳግም እንዲካተት መደረጉን ባንኩ በመግለጫው ጠቅሷል። ራማዳ ፔይ በሕጋዊ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች ስም ዝርዝር ውስጥ ዳግም እንዲካተት የተደረገው አስፈላጊው የቁጥጥርና የክትትል ሂደት ከተጠናቀቀ በኋላ መሆኑን ተነግሯል። በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ አገልግሎት እንዳይሰጡ ታግደው የሚገኙ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች በሙሉ የሀገሪቱ
2 days ago1 min read


ከተማሪዎች ንቅናቄ ጀምሮ የተፈጠሩ የማያግባቡ ትርክቶች
ህዳር 3 2018 የህዝብን ስሜት ለመሳብ እና የፖለቲካ ቅቡልነት ለማግኘት ተብለው ከተማሪዎች ንቅናቄ ጀምሮ የተፈጠሩ የማያግባቡ ትርክቶች መፍትሔ እንዲፈለግላቸው ተጠየቀ። ትርክቱን የፈጠሩት አንዳንድ የብሄር ፖለቲካ አራማጆች እና የፖለቲካ ድርጅት መስራቾች በሰሩት ስህትት ቢፀፀቱም ትርክቱ ከእነሱ ቁጥጥር ውጪ ስለሆነ ችግሩን መፍታት እና የተከሰተውን ቀውስ ማረም እንዳልተቻለም ተነግሯል፡፡ ይህ የተጠየቀው የኢትዮጵያ ሞያ ማህበራት ባለፈው ቅዳሜ ጥቅምት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ታሪክ እና ትርክትን መሰረት አድርጎ ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ነው። በውይይቱ ላይ መነሻ ሀሳብ ያቀረቡት የታሪክ አጥኚው እና የኢትዮጵያ ታሪክ ባለሞያዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ባህሩ ዘውዴ(ፕ/ር) ትርክት ማለት ለጥሩም ሆነ ለመጥፎ ዓላማ ታሪክን ለውስን ወይም ለራስ
2 days ago3 min read


በወሊድ ወቅት የሚከሰት ፌስቱላ !
በወሊድ ወቅት በተገቢው ሰዓት አስፈላጊውን ህክምና አለማግኘት ብዙ ችግር ያስከትላል፡፡ እንደ መንገድ፣ ገንዘብ፣ የባህል ተጽዕኖ እና በተዛቡ የአመለካከት ችግሮች ምክንያት ወደ ጤና ተቋማት ባለመሄድ አሊያም ወደ ጤና ተቋማት ከሄዱ በኋላ ተገቢውን ህክምና አለማግኘት ፣ ጥራት በጎደለው ህክምና ፣ የአቅርቦት እጥረት ፣ ተፈላጊው ክህሎት ያለው ባለሙያ ባለመኖር እና ሙያው በሚጠይቀው ሙያዊ የሥነምግባር ጉድለት ምክንያት ሽንት መቆጣጠር አለመቻል ወይም ፌስቱላ ሊከሰት ይችላል፡፡ በወሊድ ወቅት የሚከሰት ፌስቱላ ቁርጠኝነቱ ካለ እና ከህክምና ባለሙያዎች ጋር የተቀናጀ ጥረት ከተደረገ ሙሉ በሙሉ መከላከል እንደሚቻል ባለሙያዎች የሚያምኑ ቢሆንም አንዴ ከተፈጠረ በኋላ ግን አስቸጋሪ አንዳንዴም የማይቻል ነው ይላሉ። ምክንያቱም ለፌስቱላ የሚያደርሰው ከባድ በሆነው ምጥ
3 days ago2 min read


የኢኮኖሚ ድርጅቶችን እንዲቆጥሩ 40,000 ወጣቶች ተሰማርተዋል ተባለ፡፡
ህዳር 2 2018 በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የኢኮኖሚ ድርጅቶችን እንዲቆጥሩ 40,000 ወጣቶች ተሰማርተዋል ተባለ፡፡ ይህንን ያለው የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ነው፡፡ አገልግሎቱ ድርጅቶቹን እንዲቆጥሩልኝ ያሰማራኋቸው ወጣቶች ሁሉም የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ናቸው ብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት ከጥቅምት 1 ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 2018 ዓ.ም ድረስ በኢትዮጵያ የሚገኙ ሁሉም አይነት የኢኮኖሚ ድርጅቶች መረጃ የመቁጠር ስራ እየከወነ እንደሆነ ተናግሯል፡፡ በዚህ ቆጠራ በኢትዮጵያ የሚገኙ የኢኮኖሚ ድርጅቶ ብዛት፣ በምን ዘርፍ እንደተሰማሩ፣ ያላቸው የሰው ሀይል፣ የሚገኙበት ቦታ፣ የሚጠቀሙት የግብዓት ዓይነት መጠንና ምንጭ፣ የምርት ሽያጮቻቸውና ምን ያህል ኤክስፖርት እንደሚያደርጉ እንዲሁም በስራቸው የሚገጥሟቸው ችግሮች ይመዘገባል
3 days ago2 min read


የጤና ሚኒስቴር የህክምና ተቋማት የሚሰጧቸውን የተለያዩ የህክምና አይነቶች ያካተተ መተግበሪያ አስመርቋል
ህዳር 2 2018 በሀኪም የታዘዙ መድሀኒቶችን በቀላሉ ፈልጎ ማግኘት ብዙ ጊዜ ለተጠቃሚዎች ፈታኝ ይሆናል፤ አንዳንዶቹ መድሃኒቶች በተወሰኑ የመድኃኒት መደብሮች ወይም ፋርማሲዎች የሚገኙ አልፎ አልፎም በደላላ ዋጋ ተጨምሮባቸው የሚሸጡ መሆኑን ታካሚዎች ቅሬታ ያቀርባሉ፡፡ ይህንን ያስቀራል በሚል በተጨማሪም የህክምና ተቋማት የሚሰጧቸውን የተለዩ የህክምና አይነቶች ያካተተ መተግበሪያ የጤና ሚኒስቴር ትናንት አስመርቋል፡፡ መተግበሪያው የኢትዮጵያን የጤና ስርዓት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለመደገፍና በተለይ ብዙ ችግር የሚታይበትን የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓት ለማገዝ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡ ኢንጂነር ውብአየሁ ማሞ መተግበሪያውን ካለሙት ባለሙያዎች አንዱ ናቸው አሁን ዲጂታል ጤናን በእንደዚህ አይነት መልኩ መጀመሩ የመድኃኒቶችን ዋጋ እና ቦታውን በቀላሉ ለማ
3 days ago1 min read
በሴቶች ተይዘው የነበሩ የከፍተኛ ስልጣን ቦታዎች ተመልሰው በወንዶች እየተያዙ መሆኑን ጥናት አሳየ፡፡
ህዳር 2 2018 ሴቶች በሰላምና ደህንነት ጉዳዮች እንዲወያዩ፣ መፍትሄም እንዲሰጡ የማድረግ ጅምሮች ቢኖሩም አሁንም ብዙ እንደሚቀር ጥናት አሳየ፡፡ በሴቶች ተይዘው የነበሩ የከፍተኛ ስልጣን ቦታዎች ተመልሰው በወንዶች እየተያዙ መሆኑን በጥናቱ ተጠቅሷል፡፡ ላለፉት 25 ዓመታት ሴቶች በሰላምና ደህንነት ላይ የነበራቸው ተሳትፎና ሚና ምን ይመስላል የሚለው ጥናት ያደረጉት በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህርና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሦስተኛ ዲግሪያቸውን በመስራት ላይ የሚገኙት አቶ መብራቱ ጌርጌሶ ናቸው፡፡ አሁን ላይ ሴቶች በፖለቲካው በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ በሌሎችም ጉዳዮች ላይ እየተሳተፉ ቢሆንም በቂ እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ መምህርት የሆኑት ሙሉእመቤት ማጆሮ(ዶ/ር) ሴቶች በባህላዊ የሰላም ግንባታ ላይ ተሳትፎቸው ምን ይመስላል የሚለ
3 days ago1 min read


ህዳር 2 2018 - የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር አለም አቀፍ ወድድሮችን በተመለከተ እቅዱን ሙሉ በሙሉ ፈጽሜያለሁ ማለቱ በፓርላማ ጥያቄ አስነሳ።
በ20ኛው አለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ኢትዮጵያ ያመጣችው ውጤት ከ33 ዓመታት ወዲህ ዝቅተኛ ቢሆንም፤ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር አለም አቀፍ ወድድሮችን በተመለከተ እቅዱን ሙሉ በሙሉ ፈጽሜያለሁ ማለቱ በፓርላማ ጥያቄ አስነሳ። ኢትዮጵያ ባለፈው ጃፓን ቶኪዮ ላይ በተደረገው 20ኛው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ያስመዘገበችው ውጤት ከ33 ዓመታት ወዲህ ዝቅተኛው መሆኑን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህል እና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተናግሯል። ቋሚ ኮሚቴው ይህን የተናገረው የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴርን የ2018 ሩብ ዓመት የስራ ክንውን ሪፖርቱን ትናንት ከስዓት በኋላ በገመገመበት ወቅት ነው። የቋሚ ኮሚቴውን ጥያቄ ያቀረቡት የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ተህቦ ምህረት ናቸው። አቶ ተህቦ የባህል እና
3 days ago2 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page








