top of page


‘’የበጋው መብረቅ’’ ሌተና ጀነራል ጃገማ ኬሎ
#ታሪክን_የኋሊት ‘’የበጋው መብረቅ’’ በሚል ቅፅል ስማቸው የሚታወቁት ሌተና ጀነራል ጃገማ ኬሎ ከዚህ አለም በሞት የተለዩት በ2009 ዓ.ም በዛሬዋ ዕለት ነበር፡፡ አርበኛው ጃገማ ኬሎ ጣሊያን ኢትዮጵያ በወረረችበት ወቅት ከፍተኛ ተጋድሎ በማድረጋቸው ይታወቃሉ፡፡ ጃጋማ ኬሎ የተወለዱት በጅባትና ሜጫ አውራጃ በደንቢ ዮብዲ ወረዳ ውስጥ በ1913 ዓ.ም ነው፡፡ ጃገማ ለቤተሰቦቻቸው የመጨረሻ ልጅ ናቸው፡፡ በልጅነታቸው ወላጅ አባታቸውን በሞት በማጣታቸው ያደጉት ከአጎታቸው ጋር ነው፡፡ አደን ይወዱ የነበሩት ጃገማ የ15 ዓመት ወጣት እያሉ ጣሊያን ኢትዮጵያን ወረረች፡፡ ታዳጊው አዳኝ ከሌሎች የኢትዮጵያ አርበኞቸ ጋር ሆነው ጫካ ገቡ፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥ በርካታ አርበኞችን በማስተባበር ታዋቂ የጦር መሪና አስተባባሪ መሆን ቻሉ፡፡ በተለያዩ የጦር ሜዳዎች የኢጣሊያ
2 hours ago2 min read


ኢትዮጵያ ከወጪ ንግድ ከምታገኘው ገቢ ግብርና በአማካይ ከሶስት ቢሊየን ዶላር በላይ የሚሆነውን እንደሚያመጣ ይነገራል።
መጋቢት 29/2018 ኢትዮጵያ ከወጪ ንግድ ከምታገኘው ገቢ ግብርና በአማካይ ከሶስት ቢሊየን ዶላር በላይ የሚሆነውን እንደሚያመጣ ይነገራል። መንግስት ደግሞ የዘርፉን ምርታማነት በማሳደግ ገቢውን ይበልጥ ከፍ ለማድረግ እየሰራሁ ነው ብሏል። ምርታማነትን ከማሳደግ ጎን ለጎን ጥራት ማረጋገጡም እኩል ትኩረት የሚሰጠው ነው የሚለው የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ወደ ውጪ የሚላኩትም ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡትም በጠንካራ የፍተሻ ስርአት ውስጥ እንደሚያልፉ ተናግሯል። ግብርና በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ድርሻው ከፍ ያለ እንደሆነ ከግብርና ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ ያመለክታል። እንደ መረጃው ዘርፉ ለጥቅል ሀገራዊ ምርት ( #GDP ) 32 በመቶ ድርሻ ያበረክታል። ከአጠቃላይ የሀገሪቱ ህዝብም እስከ 75 በመቶ የሚሆነው በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋዋሪ በግብርና ተሰማርቶ የሚ
3 hours ago2 min read


አንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ-ጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
መጋቢት 29/2018 አንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ-ጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። አምባሳደር ቆንጂት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከ1950ዎቹ አንስቶ ከዴስክ ኦፊሰርነት እስከ ከፍተኛ ሀላፊነት ማገልገላቸው ተነግሯል። አምባሳደር ቆንጂት የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት ከመመስረቱ አንድ ዓመት አስቀድመው ወደ ዲፕሎማትነት ህይወት መግባታቸው ይነገራል። በዲፕሎማትነት ሀገራቸውን በማገልገል ቀዳሚ ከሆኑ ሴት አፍሪካዊ ዲፕሎማቶች ውስጥ አንዷ ተደርገውም ስማቸው ይነሳል። ለዚሁ የረጅም ጊዜ አገልግሎታቸውን ከዚህ ቀደም በሀገር ደረጃ እውቅና ተሰጥቷቸዋል። #አምባሳደር_ቆንጂት ከዮዲት እምሩ በመቀጠል፤ በኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሴት አምባሳደርም ናቸው። አምባሳደሯ በኦቶዋ፣ ካይሮ፣ ቴል አቪቭና ቬይና በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች
3 hours ago1 min read


የኢራን የደህንነት መስሪያ ቤት የበላይ መጂድ ካዴሚ በአሜሪካ እና በእስራኤል ጣምራ ጥቃት ተገደሉ ተባለ፡፡
መጋቢት 28/2018 የኢራን የደህንነት መስሪያ ቤት የበላይ መጂድ ካዴሚ በአሜሪካ እና በእስራኤል ጣምራ ጥቃት ተገደሉ ተባለ፡፡ ካዴሚ የተገደሉት አሜሪካ እና ኢራን ዛቻቸውን ከፍ ባደረጉበት አጋጣሚ እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡ የኢራን ሹሞችም ካዴሚ በአሜሪካ እና በእስራኤል ጣምራ ጥቃት መገደላቸውን አረጋግጠዋል ተብሏል፡፡ ጦርነቱ ከተጀመረ አንስቶ የቀድሞው የአገሪቱን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ ዓሊ ሐሚኒን ጨምሮ በርካታ ኢራናውያን የጦር እና የሲቪል ሹሞች ተገድለዋል፡፡ በኢራን ፣ በእስራኤል በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ እና በሳውዲ አረቢያ አዳዲስ ጥቃቶች መፈፀማቸው ተሰምቷል፡፡ ኢራን የጦርነት መቆሚያ መደራደሪያ ረቂቋን ማቅረቧ ታውቋል፡፡ ፓኪስታን በድርድሩ አስተናጋጅነት ስሟ ሲነሳ ሰምብቷል፡፡ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡.
1 day ago1 min read


መጋቢት 28/2018 - ዓለም አቀፍ ወሬዎች
#ፍልስጤም የፍልስጤማውያኑ የጦር እና የፖለቲካ ድርጅት (ሐማስ) የእስራኤል ጦር በጋዛ የሚፈፀመውን ጥቃት አቁሞ ጠቅልሎ ካልወጣ በስተቀር በጭራሽ ትጥቅ አልፈታም አለ፡፡ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለጋዛ ሰርጥ የወደፊት ሰላም ቀደም ሲል ያቀረቡት ባለ 20 ነጥቦች የሰላም እቅድ ሐማስ ሙሉ በሙሉ ትጥቅ እንዲፈታ የሚጠይቅ መሆኑን ሬውተርስ አስታውሷል፡፡ የሐማስ የበላዮች በዚህ ጉዳይ ትናንት ከአደራዳሪዎቹ ጋር መመካከራቸው ተሰምቷል፡፡ ይሄን ተከትሎም የሀማስ ወታደራዊ ክንፍ ቃል አቀባይ አቡ ኦባይዳ የእስራኤል ጦር ከመንፈቅ በፊት በተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት መሰረት የጋዛ ሰርጥን ለቅቆ ካልወጣ በስተቀር በጭራሽ ትጥቅ አንፈታም ብለዋል፡፡ በጋዛ የወደፊት ዘላቂ ስለማለቱ የሐማስ ትጥቅ መፍታት ነገር በጣሙን አስቸጋሪው ጉዳይ እንደሆነ ይነገራል
1 day ago2 min read


በቀን እስከ 50 ሺህ ስኩዌር ሜትር ወይም ከ40 እስከ 45 ኮንቴነር ሴራሚክ ማምረት የሚችል ፋብሪካ ከ3 ሳምንት በኋላ ምርት ይጀምራል ተባለ።
መጋቢት 28/2018 በቀን እስከ 50 ሺህ ስኩዌር ሜትር ወይም ከ40 እስከ 45 ኮንቴነር ሴራሚክ ማምረት የሚችል ፋብሪካ ከ3 ሳምንት በኋላ ምርት ይጀምራል ተባለ። በ50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ኢንቨስትመንት ከአዲስ አበባ 65 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው በቱለፋ ከተማ የተገነባው ይህን ፋብሪካ የገነባው ባይጂያ ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ የተባለ ድርጅት ነው። በ30 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ የሴራሚክ እና የፖርስሊን ምርቶች ፋብሪካ ምርት ሲጀምር ብቻውን አሁን ካለው የሴራሚክ ፍላጎት እስከ 70 በመቶ ድረስ የማቅረብ አቅም አለው ተብሎለታል። በባይጂያ ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ የሚመረቱን ምርቶች ለገበያ የሚያቀርበው ማንሰን ኢንቨስትመንትስ ነው። የማንሰን ኢንቨስትመንትስ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳዊት እርገቱ እና የባይጂያ ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ ዋና
1 day ago1 min read


የአካቶ ትምህርት ስርዓት ለአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች
መጋቢት 25/2018 በአካቶ ትምህርት ስርዓት አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች እንዳለባቸው ችግር ተለይተው እንደማንኛውም ሰው የትምህርት እድል እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ቢባልም ልዩ ፍላጎት የሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች ግን ጎዶሎዎች እንዳሉባቸው ይናገራሉ፡፡ በልዩ ፍላጎት የሰለጠነ በቂ መምህራን አለመኖር፣ የትምህርት ቁሳቁስ እጥረት፣ የመሰረተ ልማት ምቹ አለመሆንን ጨምሮ ሌሎች ችግሮች እንዳሉባቸው ያነሳሉ፡፡ ትምህርት ሚኒስቴርም በበኩሉ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች የሚያነሱት ቅሬታ ትክክል ነው ለዚህ ደግሞ እንደ እኩዮቻቸው የትምህርት እድል እንዲያገኙ የአካቶ ትምህርት ሥርዓትን ዘርግቼ እየሰራሁ ነው ብሏል፡፡ በተለይ የአካቶ ትምህርት ትግበራ ሲታሰብ የቁሳቁስ እጥረት፣ የሰለጠኑ መምህራን አለመኖር፣ የመሰረተ ልማት ምቹ አለመሆን በዋናነት የሚነሱ ጥያቄዎች
4 days ago1 min read


የተፈጠረውን የነዳጅ እጥረት ተከትሎ የጭነት መኪኖች ምልልስ በመቀነሱ የወጪ ንግዱ የሚላክበት ኮንቴይነር እጥረት ማጋጠሙ ተሰምቷል፡፡
መጋቢት 25/2018 በሀገር ውስጥ የተፈጠረውን የነዳጅ እጥረት ተከትሎ የጭነት መኪኖች ምልልስ በመቀነሱ የወጪ ንግዱ የሚላክበት ኮንቴይነር እጥረት ማጋጠሙ ተሰምቷል፡፡ በጅቡቲ የባዶ ኮንቴይነሮች ክምችት ቢጨምርም መኪኖች ወደ ሀገር ቤት በበቂ ሁኔታ ሊያመጧቸው ስላልቻሉ የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ድርጅት ባዶ ኮንቴነሮችን ወደ ሀገር እያስገባ እንደሚገኝ ነግሮናል። የኢትዮ ጁቡቲ ምድር ባቡር ድርጅት የቢዝነስ ደቨሎፕመንት እና የማርኬቲንግ ክፍል ሃላፊ ኤደን ተስፋዬ በተለይ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ለተሰማሩ ድርጅቶች ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል። ላኪዎች ከድርጅቱ ጋር እንዲሰሩ እና በተፈጠረው ችግር ምክንያት መስተጓጎል እንዳይኖር እንዳያደርጉም ሃላፊዋ ጥሪ አቅርበዋል። ድርጅቱ ለወጪ ንግዱ ቅድሚያ በመስጠት ጭነቶችን ለማመላለስ ዝግጅት እንደጨረሰም ተ
4 days ago1 min read


የመካከለኛ ምስራቅ ጦርነት ያስከተለው የነዳጅ እጥረት አምራች ፋብሪካዎች ላይም ተፅዕኖ እያሳደረ ነው፡፡
መጋቢት 25/2018 የመካከለኛ ምስራቅ ጦርነት ያስከተለው የነዳጅ እጥረት አምራች ፋብሪካዎች ላይም ተፅዕኖ እያሳደረ ነው፡፡ የተለያዩ ምርቶችን ለገበያ የሚያቀርቡ ፋብሪካዎች በነዳጅ እጥረት ምክንያት ጥሬ እቃ ተወዶብናል ፣ ተፅዕኖዎቹን ተቋቁመን የምርት ሂደቱ እንዳይስተጓጎል ጥረት እያደረግን ነው ብለዋል፡፡ በመካከለኛው ምስራቅ ኢራን ከአሜሪካና እስራኤል ጋር እያካሄደችው ያለው ጦርነት በእኛም ሀገር እንቅስቃሴዎች ላይ ተፅዕኖውን እያሳረፈ ነው። የትራንስፖርት ዘርፉ ተጠቃሽ ሲሆን አሁን ያለውን ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ የነዳጅ ግብይት መከተል እንደሚገባ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከሠሞኑ ማሳሰቡ ይታወሳል። የተፈጠረውን የነዳጅ አቅርቦት ችግር ተከትሎ በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ላይ መስተጓጎል እንዳይፈጠር ፤ መንግስት ነዳጅን ከተጓዳኝ
4 days ago2 min read


የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በድጋሚ የአብረን እንስራ ጥሪ አቀረበ።
መጋቢት 25/2018 የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በድጋሚ የአብረን እንስራ ጥሪ አቀረበ። ላለፉት 3 ቀናት በአዲስ አበባ ከትግራይ ክልል ተወላጆች ጋር ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያ ዙር የአጀንዳ ማሰባሰብ ምክክር ዛሬ ተጠናቅቋል። በማጠናቀቂያው መርሃ ግብር መልዕክት ያስተላለፉት ፤ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ የመከርነው ለትግራይ ሰላም እንጂ ትግራይን ለመጉዳት አይደለም፤ ከዚህም በኋላ አብሮ ለመስራት በራችን ክፍት ነው ሲሉ ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ጥሪ አቅርበዋል። በምክክሩ የተነሱት ጉዳዮች ደረጃቸው ሊለያይ ይችል ይሆናል እንጂ፤ አብዛኞቹ በሁሉም ክልሎችና የከተማ መስተዳድር ከተነሱት ጋር ተቀራራቢ ናቸው ብለዋል። ይሁንና አንዳንዶቹ ጉዳዮች የትግራይ ብቻ የሆኑ መሆናቸውን አስተው
4 days ago1 min read


ዳሸን ባንክ ልዩ የሱፐር አፕ ማስተዋወቅ ውድድር ሽልማትን ጨምሮ አራት አዳዲስ አገልግሎቶችን ዛሬ አስጀመረ።
መጋቢት 24/2018 ዳሸን ባንክ ልዩ የሱፐር አፕ ማስተዋወቅ ውድድር ሽልማትን ጨምሮ አራት አዳዲስ አገልግሎቶችን ዛሬ አስጀመረ። ባንኩ የሱፐር አፕ ተጠቃሚዎችን ለማበረታት እንዲሁም የአገልግሎቱን ተደራሽነት ለማስፋት የቲክቶክ ይዘት ፈጠራ ውድድር ማዘጋጀቱን ይፋ አድርጓል። በዚህ ውድድር ለሚያሸንፉ የይዘት ፈጣሪዎች በድምሩ ስድስት ሚሊዮን ብር የገንዘብ ሽልማት እንዳዘጋጀ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የንግድ ሥራ ትምህርት ቤት (ኮሜርስ) በተዘጋጀ ስነ ስርአት ላይ ተነግሯል። በዳሸን ሱፐር አፕ ቲክቶክ ቻሌንጅ አሸናፊ ለመሆን ይዘት ፈጣሪዎች ስለ ዳሸን ባንክ ሱፐር አገልግሎቶች የሚገልፅ የቲክቶክ ቪዲዮ በመስራት ማጋራት ይጠበቅባቸዋል ተብሏል። የሰሩት ቪዲዮ በቲክቶክ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዕይታ ሲያገኝ፣ በዳሸን ሱፐር አፕ ውስጥ በሚገኘው የዳሸን ክሬቲቭ አ
5 days ago1 min read


ከቴምር ፕሮፐርቲ መኖሪያ ቤት የሚገዙ ደንበኞች ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ልዩ የሼባ ማይልስ ስጦታ የሚያገኙበት ዕድል መዘጋጀቱ ተነገረ።
መጋቢት 24/2018 ከቴምር ፕሮፐርቲ መኖሪያ ቤት የሚገዙ ደንበኞች ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ልዩ የሼባ ማይልስ ስጦታ የሚያገኙበት ዕድል መዘጋጀቱ ተነገረ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የደንበኞች ሎያሊቲ ክፍል ማናጀር አቶ ሰለሞን መኮንን እና የቴምር ፕሮፐርቲ የኢቨንት እና ፕሮሞሽን ዳይሬክተር አቶ ዑስማን መሀመድ ስምምነቱን በሰጡት መግለጫ ይፋ አድርገዋል። በዚህ ስምምነት መሰረት የቴምር ሪል ስቴት ደንበኞች የሚገዙትን የቤት ወይም የሱቅ አይነት መሰረት ያደረገና የከፈሉትን መጠን ያማከለ የዓለም አቀፍ በረራ የማይልስ ዕድል ያገኛሉ ተብሏል። የቴምር ደንበኞች በዚህ ስምምነት መነሻነት የሼባማይልስ ደረጃቸው እንደ ክፍያቸው ሁኔታ እያደገ የሚሄድ ሲሆን፤ ከብሉ ወደ ሲልቨር፣ ከሲልቨር ወደ ጎልድ ወይም ከብሉ ወደ ጎልድ የማሳደግ ዕድልንም ይሰጣል መባሉን ሰም
5 days ago1 min read


ቪዛ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለ ቪዛ ካርድ ደንበኞች የ2026 የዓለም ዋንጫን በአካል ተገኝተው የሚመለከቱበትን ዕድል ይዘው መቅረባቸውን ተናገሩ።
መጋቢት 24/2018 ቪዛ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለ ቪዛ ካርድ ደንበኞች የ2026 የዓለም ዋንጫን በአካል ተገኝተው የሚመለከቱበትን ዕድል ይዘው መቅረባቸውን ተናገሩ። ዕድሉ የምድብ ጨዋታዎችን በአካል ለመመልከት የሚያስችል መሆኑ ተነግሯል። ይህ ከመጋቢት 5 እስከ ሚያዝያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ንቅናቄ፣ በመላው ኢትዮጵያ ለሚገኙ የባንኩ የዴቢትም ሆነ የቅድመ ክፍያ ቪዛ ካርድ ተጠቃሚዎች በሙሉ ክፍት ነው ተብሏል። ደንበኞቹ በቪዛ ካርዳቸው የሚፈጽሙት እያንዳንዱ ግብይት እንደ አንድ ዕጣ ይቆጠራል የተባለ ሲሆን ለዚህ ምዝገባ አይጠየቅም ተብሏል። በቪዛ የምሥራቅ አፍሪካ ክላስተር ሓላፊ የሆኑት ያሬድ እንዳለ፣ የካርድ ተጠቃሚዎችን በየቀኑ እየፈጸሟቸው ለሚገኙ ግብይቶች ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ተባብረን በመሸለማችን ደስተኞች ነን'' ብለዋል።
5 days ago1 min read


አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ከሌሎች ተማሪዎች እኩል የማይማሯቸው ትምህርቶች በመኖራቸው ተወዳዳሪነታችንን ይቀንስብናል ብለዋል።
መጋቢት 24/2018 በኢትዮጵያ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ቀላል የማይባል ችግር እንደሚያጋጥማቸው በተደጋጋሚ ይናገራሉ፡፡ የመሰረተ ልማት አለመሟላት፣ እነሱን ተቀብሎ የሚያስተምር ትምህርት ቤት አለማግኘት፣ የቁሳቁስ አለመሟላት፣ በስራ ቅጥር ወቅት እድል አለማግኘት እና በሌሎች ፈተናዎች እንደሚያልፉ ይነገራል፡፡ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ከሌሎች ተማሪዎች እኩል የማይማሯቸው ትምህርቶች በመኖራቸው ተወዳዳሪነታችንን ይቀንስብናል ብለዋል። በዚህም ምክንያት አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ገበያ ሲቀላቀሉ ከሌሎች ተማሪዎች ጋር እኩል ተወዳዳሪ ለመሆን እንደሚቸገሩ አንስተዋል። ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ እስከ ሁለተኛ ደረጃ የትምህርት ክፍል ድረስ አካል ጉዳተኞች የማይማሯቸው የትምህርት ዓይነቶች በመኖራቸው ተወዳዳሪነታቸው ላይ ችግር እየፈጠረባቸው
5 days ago1 min read


ታሪክን የኋሊት - ንግስተ ነገስታት ንግስት ዘውዲቱ
በኢትዮጵያ የመሪዎች ታሪክ ፣ ባለፉት 1000 ዓመታት ውስጥ የመጀመሪያዋ ሴት ንግስተ ነገስታት የነበሩት ንግስት ዘውዲቱ ፣ ያረፉት በ1922 ዓ.ም በዛሬው ቀን ነበር፡፡ ንግስተ ነገስታት ዘውዲቱ፣ በ10ኛ ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ መሪ እንደነበረች ከሚነገርላት ዮዲት ጉዲት ወዲህ ፣ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሴት መሪ ነበሩ፡፡ ንግስት ዘውዲቱ ፣ የኢትዮጵያን ንግስና ያገኙት ፣ በጊዜው የነበሩት የጦር አለቆች ፣ አገረ ገዥዎች ፣ መኳንንት የቤተ መንግስቱ የጥበቃ ወታደሮች ምርጫ እንጂ እንደቀደምቶቻቸው በውርስና በውጊያ አልነበረም፡፡ ከአዲስ አበባ ቤተ መንግስት የተላኩ የጦር መኮንኖች ፣ መሳፍንቱ መኳንንቱ ሕዝብና ሰራዊት፣ በአንድነት ተስማምተው ፣ ነግስተ ነገስታት ዘውዲቱ ተብለው ፣ በአባትዋ በአፄ ምኒልክ ዙፋን እንዲቀመጡ “መርጦዎታል” ተብለው የተነገሩት
5 days ago2 min read


የእሳት እራት ተብሎ የሚጠራው ነፍሳት በኢትዮጵያ በአፅዋት ላይ ምንም ጉዳት የማያስከትል ቢሆንም አውሮፓ ከገባ ግን ከ100 በላይ የእፅዋት ዓይነቶችን ቀርጥፎ የሚበላ ሌላ ባህሪ ያለው ተባይ ይሆናል፡፡
መጋቢት 24/2018 የእሳት እራት ተብሎ የሚጠራው ነፍሳት በኢትዮጵያ በአፅዋት ላይ ምንም ጉዳት የማያስከትል ቢሆንም አውሮፓ ከገባ ግን ከ100 በላይ የእፅዋት ዓይነቶችን ቀርጥፎ የሚበላ ሌላ ባህሪ ያለው ተባይ ይሆናል፡፡ በዚህም ምክንያት ከአመታት በፊት በኢትዮጵያ የአበባ እርሻዎች ውስጥ መገኘቱን ተከትሎ የአውሮፓ ህብረት ተባዩ ከምርቱ ጋር ወደኛ እንዳይመጣብን የሚል ማሳሰቢያ ሰትቶ ነበር፡፡ የአበባ ምርት ወደ ህብረቱ እንዳይገባ ከመታገዱ በፊት ምን እርምጃ ተወሰደ፡፡ በእንግሊዝኛው ምህጻረ ቃል F C M የሚሰኘው ተባይ የቢራቢሮ ዝርያ ሲሆን በእኛ አገር የእሳት እራት በመባል ይታወቃል ። በሀገራችንአብዛኞቹ ዕፅዋት የዚህ ተባይ መኖሪያ ሆነው እንደሚያገለግሉ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ወንዳለ ሃብታሙ ነግረውናል፡፡
5 days ago1 min read


በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በከፍተኛ ት/ት ተቋማት የሚገኙ ወጣቶች ለኤችአይቪ ተጋላጭነትን ለመቀነስ የኮንዶም አቅርቦትና ግንዛቤው ላይ መሰራት አለበት ተባለ፡፡
መጋቢት 24/2018 በኢንዱስትሪ ፓርኮች እንዲሁም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ የሚገኙ ወጣቶች ለኤች አይ ቪ ተጋላጭነትን ለመቀነስ የኮንዶም አቅርቦትና ግንዛቤው ላይ መሰራት አለበት ተባለ፡፡ በስራቸው እና ዕድሜያቸው ምክንያት ለኤች አይ ቪ እጅግ ተጋላጭ ከሆኑት ውስጥ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያሉ ወጣቶች በተለይ ሴቶች ይገኙበታል ተብሏል፡፡ ለዚህም የጤና ሚኒስቴር ከለጋሽ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመሆን ኮንዶም በነፃ እያቀረበ መሆኑን ነገር ግን ይህም ቢሆን በቂ አለመሆኑን ተናግሯል፡፡ በጤና ሚኒስቴር የኤች አይቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ፍቃዱ ያደታ እንደሚናገሩት በተለይ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ላይ ተቀጥረው ከሚሰሩት ውስጥ አብዛኛዎቹ ወጣቶች በመሆናቸው የኤች አይ ቪ ተጋላጭነታቸውን መቀነስ ላይ ይበልጥ መስራት ያ
5 days ago2 min read


የአቪዬሽን ዘርፍ ባለሙያዎች በሚፈለገው ልክ ማሰልጠን እና ያሉትንም የማቆየቱ ፈተና እንዴት እየሆነ ይሆን?
መጋቢት 24/2018 በአቪዬሽን ዘርፍ የሚሰማሩ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች፣ ኦዲት ኢንስፔክተሮች እና ሌሎች ባለሞያዎችን መቅጠር፣ ያሉትንም ማቆየት የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ዘርፍ ያልተፈታ ፈተና ነው። በክፍያ ምክንያት የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን እነዚህን የአቪዬሽን ዘርፍ የጀርባ አጥንት የሆኑትን ባለሙያዎች በሚፈለገው ልክ ለማግኘትና፣ የገቡትንም ለማቆየት እንደሚቸገር በየጊዜው ይነሳል። ኢትዮጵያ ከዓለም ተወዳዳሪ፣ ከአፍሪካ ቀዳሚ የሆነ ግዙፍ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ እየገነባች ነው፣ የአቪዬሽኑ ዘርፍ በፍጥነት እያደገ ነው፣ የሀገር ውስጥ በረራን የሚሰጡ አዳዲስ አውሮፕላን ማረፊያዎችም በየክልሉ እየተገነቡ ነው። ለመሆኑ ለዚህ ሁሉ ስራ የግድ የሆኑትን፣ የአቪዬሽኑን ዘርፍ ከጀርባ ሆነው የሚደግፉትን፣ የበረራ ደህንነትን የሚያረጋግጡትን ባለሙያዎች
5 days ago1 min read
የኤሌክትሪክ ኬብሎችን የዘረፉ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ።
መጋቢት 23/2018 የኤሌክትሪክ ኬብሎችን የዘረፉ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ። ከ3.8 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኤሌክትሪክ ኬብሎችን የዘረፉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አገልግሎቱ ተናግሯል። የየካ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የደረሰውን ጥቆማ መሰረት በማድረግ ከምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ህግ ቢሮ ጋር ባደረገው ኦፕሬሽን ተጠርጣሪዎቹን ካከማቹት በርካታ የኤሌክትሪክ ኬብልና ገመድ ጋር በቁጥጥር ሥር ማዋል ችለዋል ተብሏል። ኮተቤ ኪዳነ-ምህረት አካባቢ ተከማችተው የተገኙት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች 4 ሺ 895 ሜትር ኤቢሲና ዩጂ የኤሌክትሪክ ኬብሎች፣ 350 ኪ.ግ የሚመዝኑ የተለያዩ አልሙኒየምና መዳቦች ናቸው ተብሏል። አጠቃላይ የዋጋ ግምታቸውም 3 ሚሊየን 895 ሺህ 81
6 days ago1 min read


ሀገራዊ ምክክሩ የትግራይ ነገ የተረጋጋ እንዲሆን የክልሉ ህዝብ የድርሻውን የሚወጣበት መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተናገረ።
መጋቢት 23/2018 ሀገራዊ ምክክሩ የትግራይ ነገ የተረጋጋ እንዲሆን የክልሉ ህዝብ የድርሻውን የሚወጣበት መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተናገረ። ለበርካታ ጊዜያት ሊከናወን ቀጠሮ ሲያዝ ሲራዘም የነበረው የትግራይ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብ ምክክር ዛሬ በአዲስ አበባ ተጀምሯል። ከዛሬ መጋቢት 23 እስከ አርብ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ በሚካሄደው የመጀመሪያውን ዙር የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረክ ከክልሉ የመጡና በአዲስ አበባ ያሉ የትግራይ ተወላጆች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራት፣ የሃይማኖት ተወካዮች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻዎች እየተሳተፉ ነው። በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ትግራይ የሌለችበት ምክክር ግቡን የማይመታ በመሆኑ ከብዙ ጥረቶች በኋላ በአዲስ አበባ እንድ
6 days ago1 min read


መጋቢት 22/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ጀርመን በጀርመን ከሚኖሩ ስደተኞች 80 በመቶዎቹ ወደ አገራቸው እንደሚሸኙ መራሄ መንግስት ፍሬድሪክ ሜርዝ ተናገሩ፡፡ ሶሪያውያኑ ስደተኞች በመጪዎቹ 3 አመታት ከጀርመን ወደ አገራቸው ይሸኛሉ መባሉን ቢቢሲ ፅፏል፡፡ መራሄ መንግስት ሜርዝ 80 በመቶዎቹ ሶሪያውያን ስደተኞች በ3 አመታት ጊዜ ወደ አገራቸው እንደሚሸኙ እወቁልን ያሉት ከሶሪያው ጊዜያዊ ርዕሰ ብሔር አህመድ አልሻራ ጋር በበርሊን ከተነጋገሩ በኋላ ነው ተብሏል፡፡ ብዙዎቹ ሶሪያውያን ስደተኞች ጀርመን የገቡት በአገራቸው ተቀስቅሶ የነበረው ውስብስብ የእርስ በርስ ጦርነት በተፋፋመበት ወቅት ነበር፡፡ አሁን ስደተኞቹን ከጀርመን መመለስ ይጀመራል ቢባልም ዝርዝሩ ገና አልታወቀም፡፡ ሶሪያ በአሁኑ ወቅት ከ10 ዓመት በፊት ከነበረው በእጅጉ የተሻለ ፀጥታ እንደሚስተዋልባት መረጃው አስታውሷል፡፡ #አሜሪካ አ
7 days ago2 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

