top of page


ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰናዳ ነው የተባለ ሀገር አቀፍ የሰብል ጥበቃና የአፈር የማዳበሪያ ኤክስፖ በኤግዚቢሽን ማዕከል ተከፈተ።
ግንቦት 14/2018 ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰናዳ ነው የተባለ ሀገር አቀፍ የሰብል ጥበቃና የአፈር የማዳበሪያ ኤክስፖ በኤግዚቢሽን ማዕከል ተከፈተ። ኤክስፖው አስመጭዎችን፣ አከፋፋዮችን፣ ተጠቃሚዎችን በቀጥታ የሚያገናኝ እና የገበያ ትስስርን የሚፈጥር ይሆናል ተብሎ ታምኖበታል። የኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሰብል በሽታ፣ ተባይ፣ የአፈር ለምነት ችግር፣ የቴክኖሎጂ እጥረቶች እና ሌሎች ችግሮችን እያስተናገደ መሆኑ ተነግሯል። ይህንን ችግር ለመቋቋም የሚያስችል እና ዘርፉ ያሉበትን ችግሮችን ለመፍታት ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት የሚቆየው ኤክስፖ የራሱ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎ ታምኖበታል። ዝግጅቱን ዊ ሊንክ የተባለ ድርጅት ከግብርና ሚኒስቴር እና ከሌሎች የመንግስት እና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በመተባበር እንዳሰናዳው ተነግሯል። የሰብል በሽታ
26 minutes ago1 min read


የኤም ኤስ አይ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ቁጥር የነበረውን የእናቶችና ጨቅላ ህፃናት ሞት እንዲቀንስ ከፍተኛ አስተዋፆ ማድረጉን ተናገረ፡፡
ግንቦት 14/2018 በኢትዮጵያ ከ35 ዓመታት በፊት ጀምሮ የስነ ተዋለዶ፣የ እናቶችና ህጻናት ጤና አግልጎሎቶችን ሲሰጥ የቆየው የኤም ኤስ አይ ኢትዮጵያ (MSI) ከፍተኛ ቁጥር የነበረውን የእናቶችና ጨቅላ ህፃናት ሞት እንዲቀንስ ከፍተኛ አስተዋፆ ማድረጉን ተናገረ፡፡ ድርጅቱ ባለፉት 10 ዓመታት በተለይ በዓመት በአማካይ ለ2,000 ሰዎች አገልግሎቱን ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሷል፡፡ በሰጣቸው የስነ ተዋለዶ፣ የእናቶችና ህጻናት ጤና አገልግሎቶች የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር አንዲያድግ አንዲሁም የእናቶችና የጨቅላ ህጻናት ሞት አንዲቀንስ ከፍተኛ አስተዋጾ ማበርከቱን የኤም ኤስ አይ ኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተሩ አበበ ሽብሩ (ዶ/ር) ነግረውናል፡፡ በዚህም ለምሳሌ ባለፈው ዓመት ብቻ ከወሊድ ጋር በተያያዘ 1000 እናቶችን ከሞት ታድገናል ብለዋል፡፡ 30
2 hours ago2 min read


የደቡብ አፍሪካ መንግስት በኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰውን ጉዳት መርምሮ ውጤቱን በቅርብ ይፋ እንደሚደረግ ቃል መግባቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ።
ግንቦት 13/2018 የደቡብ አፍሪካ መንግስት በኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰውን ጉዳት መርምሮ ውጤቱን በቅርብ ይፋ እንደሚደረግ ቃል መግባቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ። ለተፈጠረው ችግር መፍትሄ የሚያፈላልግ ልዑክ ወደ ስፍራው በቅርብ እንደሚያቀና ሚኒስቴሩ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ተናግሯል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው በሳምንቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን አካቷል፡፡ መግለጫውን የሰጡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ናቸው። ቃል አቀባዩ በቅርቡ የተከናወኑ ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ እንቅስቃሴን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በቅርቡ በህንድ በተካሄደው የብሪክስ አባላት የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ በደቡብ አፍሪካ ጥቃት ስለደረሰባቸው ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ ከአቻችው ጋር መወያ
24 hours ago1 min read


የፖለቲካ ፓርቲዎች የህዝቡን ሰላም ከሚያውኩ ቅስቀሳዎች እንዲርቁ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አሳሰበ።
ግንቦት 13/2018 የፖለቲካ ፓርቲዎች የህዝቡን ሰላም ከሚያውኩ ቅስቀሳዎች እንዲርቁ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አሳሰበ። ከ10 ቀናት በኋላ የሚካሄደው ሃገር አቀፍ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ እንዲሁም ሃገራዊ ሰላምን ለማፅናት በሚል የፊታችን እሁድ የአደባባይ የፀሎት እንደሚደረግ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ተናግሯል። የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ጠባቂ አባቶች በወሰኑት መሰረት የፊታችን እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ፒያሳ አካባቢ በሚገኘው አራዳ ፓርክ ሃገር አቀፍ የፀሎት መርሃ ግብር መሰናዳቱን የጉባኤው ጠቅላይ ፀሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ በጉዳዩ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ዛሬ በሰጡት መግለጫ ጠቅሰዋል። ቀሲስ ታጋይ የፀሎት መርሃ ግብሩን አላማዎች ሲጠቅሱም በሃገር ውስጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ለማገዝ ምዕመናን ሃላፊነ
24 hours ago1 min read


አቢሲንያ ባንክ የ5ተኛ ዙር የ“እችላለሁ” እና የ“ይጀምሩ፣ ያድሱ፣ ይደጉ-2” የሽያጭ ዘመቻ የሽልማትና መዝጊያ ሥነ-ሥርዓት አከናወነ።
ግንቦት 13/2018 አቢሲንያ ባንክ የ5ተኛ ዙር የ“እችላለሁ” እና የ“ይጀምሩ፣ ያድሱ፣ ይደጉ-2” የሽያጭ ዘመቻ የሽልማትና መዝጊያ ሥነ-ሥርዓት አከናወነ። ባንኩ አዘጋጅቶ የነበረው የሽያጭ ዘመቻ አዳዲስ ደንበኞች ከባንኩ ጋር ሥራ እንዲጀምሩ እና ነባር አነስተኛ ተቀማጭ ያላቸውና በንቃት የማያንቀሳቀሱ ደንበኞች ግንኙነታቸውን እንዲያድሱ እንዲሁም ሁሉም ደንበኞች ከባንኩ ጋር አብረው ይደጉ በሚል መሪ ቃል ለሁለተኛ ጊዜ ያካሄድኩት ነው ብሏል። በዚህም አንድ ዕድለኛን የመኪና ባለቤት ያደረገ ሲሆን በየሁለት ሳምንቱ ደግሞ ሌሎች በርካታ የሽልማት ዓይነቶችን በመሸለም አጠናቋል። በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8)ን በማስመልከት ባንኩ ለ5ኛ ጊዜ “እችላለሁ" በሚል ከመጋቢት 8 እስከ ሚያዝያ 23 ቀን 2026 ዓ/ም የቆየ ልዩ ሴቶችን የሚያበረታታ መ
24 hours ago1 min read


በኤልኒኖ ምክንያት ሊከሰት ይችላል የተባለውን የድርቅ ስጋት
ግንቦት 13/2018 መጪው ክረምት በኤልኒኖ ምክንያት ሊከሰት ይችላል የተባለውን የድርቅ ስጋት የሚመለከታቸው ተቋማት ለገበሬው እና ሌላም ጉዳዩ ለሚያገባቸው መረጃውን እንዲያደርሱ ማሳሰቢያ ተሰጥቷቸዋል፡፡ መረጃውን ከማድረስ ባሻገር አስፈላጊው ቅድመ ጥንቃቄ ሳያደርጉ ቀርተው ጉዳት ከተከሰተ ተጠያቂ የሚሆኑበት አሰራር መዘርጋቱን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (IGAD) ተናግሯል፡፡ የዘንድሮው የክረምት ዝናብ ጥሩ አጀማመር ቢኖረውም በነሃሴ እና መስከረም ወራቶች ግን ደረቅ ሰሞናት ሊበዙ ፤ የዝናብ መዋዠቅ እና መቆራረጥም ሊታይ እንደሚችል የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሊጂ ኢንስቲትዩት ከሠሞኑ ይፋ ባደረገው ትንበያው ማሳወቁ ይታወሳል። ይኖራል ተብሎ የተተነበየው ደከም ያለ የኤልኒኖ ክስተት በነሃሴ እና መስከረም ወራቶች ደረቅ ሰሞናት እንዲበዙ ፤ ብሎም የዝ
1 day ago1 min read


ባህላዊው ህክምና በሚፈለገው ልክ ከዘመናዊው ጋር ተስማምቶ መቀጠል የማይችለው ለምንድን ነው?
ግንቦት 13/2018 እንደነ ቻይና እና ህንድ ባሉት ሀገሮች ፈዋሽነት ያላቸው እፅዋትን በመድሃኒትነት መጠቀም የተለመደ ነው፡፡ በኢትዮጵያ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተለያዩ እፅዋትን በመድሃኒትነት ፈጭታችሁ አፍልታችሁ ተጠቀሙ የሚሉ መልክቶች በተለይ በማህበራዊ ሚዲያ በስፋት ይታያል፡፡ ግን አወሳሰድን የጎንዮሽ ጉዳትና ሌላውንም እንዴት ማወቅ ይቻላል? ጠቃሚውን ከጎጂው መለየት የሚቻለውስ እንዴት ነው? ባህላዊው ህክምና በሚፈለገው ልክ ከዘመናዊው ጋር ተስማምቶ መቀጠል የማይችለው ለምንድን ነው? ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ፍቅሩ አምባቸው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68a
1 day ago1 min read
ፋሽስት ኢጣሊያ ፣ በደብረ ሊባኖስ ገዳም የሚገኙ 300 መነኮሳትና ዲያቆናት በመደዳ በጥይት ያስደበደባቸው፣ በ1929 ዓ.ም በዛሬው ቀን ነበር፡፡
#ታሪክን_የኋሊት ፋሽስት ኢጣሊያ ፣ በደብረ ሊባኖስ ገዳም የሚገኙ 300 መነኮሳትና ዲያቆናት በመደዳ በጥይት ያስደበደባቸው፣ በ1929 ዓ.ም በዛሬው ቀን ነበር፡፡ መነኮሳቱና ዲያቆናቱ እንዲገደሉ ትዕዛዝ የሰጠው ጀኔራል ሮዶልፎ ግራዚያኒ ነበር፡፡ ጀኔራል ግራዚያኒ የኢጣሊያ የምስራቅ ዕዝ አዛዥና በኋላም የኢትዮጵያ የቅኝ ግዛት ገዥ በነበረበት ጊዜ ሁሉ፣ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና መነኮሳት ላይ የተለየ ጥላቻ ነበረው፡፡ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናት፣ ኢትዮጵያ እንዳትገዛልን የሚያወግዙ፣ ስለነፃነት የሚሰብኩ፣ አርበኞችን የሚደግፉ ናቸው ፤ የሚል እምነት ስለነበረው ቤተ ክርስቲያኗን ለመበተን ይመኝ ነበር፡፡ የካቲት 12፣ አብርሃም ደቦጭ በቦምብ ካቆሰለው በኋላ ፣ሚስቱን ደብረ ሊባኖስ ገዳም መደበቁን ሰማ፡፡ ይኽም በካህናት መ
2 days ago2 min read


በምርጫ ወቅት "በታንዛኒያ እና በዩጋንዳ "ላይ የተስተዋለው የኢንተርኔት ገደብ ወይም እቀባ በኢትዮጵያ እንዳይኖር የአፍሪካ ህብረትን ጨምሮ ሌሎች ተቋማት ምክረ ሃሳብ ማቅረባቸውን ተናገሩ።
ግንቦት 12/2018 በምርጫ ወቅት "በታንዛኒያ እና በዩጋንዳ "ላይ የተስተዋለው የኢንተርኔት ገደብ ወይም እቀባ በኢትዮጵያ እንዳይኖር የአፍሪካ ህብረትን ጨምሮ ሌሎች ተቋማት ምክረ ሃሳብ ማቅረባቸውን ተናገሩ። የአፍሪካ ህብረት ምርጫውን ለመታዘብ በቂ ዝግጅት ማድረጉን እና የምርጮ ቦርድ ውሳኔን በመጠበቅ ላይ እንደሚገኝ አስረድቷል። ይህ የተነገረው ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ህብረት ፓራዳይም ኢንሼቲቭ ከተሰኘ መንግስታዊ ካለሆነ ተቋም ጋር በመሆን በዲጂታል መብት ላይ ባሰናዳው ወይይት ላይ ነው። በራዲሰን ብሉ (Radison blue) ሆቴል በተካሄደው ውይይቱ ላይ የአፍሪካ ህብረት፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት የሳይንስ የባህል ተቋም ዩኔስኮ ፣ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ፣ የኢትዮ ቴሌኮም
2 days ago2 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

