top of page


10 ቢሊዮን ዶላር ወጪ የሚጠይቀው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ተጀመረ።
ጥር 2/2018 10 ቢሊዮን ዶላር ወጪ የሚጠይቀው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ተጀመረ። ግንባታውን ያስጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ናቸው፡፡ የቢሾፍቱ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ፕሮጀክት ይሆናል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስረድተዋል። ይኽም ከኢትዮጵያ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ሪፎርም፣ የኢንደስትሪ ማስፋፊያ አጀንዳ እና የረጅም ዘመን የአቪየሽን ስትራቴጂ ጋር የተናበበ ነውም ሲሉም አክለዋል። ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድን አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያጠናክራል። በAfCFTA ማህቀፍ የአፍሪካን የማገናኘት አቅም ይጨምራል ተብሏል። ከአዲስ አበባ ደቡብ ምስራቅ 40 ኪሎሜትር አካባቢ የምትገኘውና 1910 ሜትር ከፍታ ያላት ቢሾፍቱ ለአውሮፕላኖች ሥራ የተመቸ ከባቢ ያላት ሲሆን
3 days ago1 min read


በአዲስ አበባ አንዳንድ የወረዳ አመራሮች ተገልጋዩን ያመነጫጭቃሉ፣ ለጥያቄም ምላሽ አይሰጡም የሚል ቅሬታ ቀረበባቸው።
ጥር 2/2018 በአዲስ አበባ አንዳንድ የወረዳ አመራሮች ተገልጋዩን ያመነጫጭቃሉ፣ ለጥያቄም ምላሽ አይሰጡም የሚል ቅሬታ ቀረበባቸው። የከተማ አስተዳደሩ በበኩሉ በአግባባቡ ስራቸውን መስራት ያልቻሉ ሃላፊዎች ላይ እርምጃ እንደተወሰደባቸው አንደሆነ አስረድቷል፡፡ ቅሬታው የቀረበባቸው የከተማው የሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ በስድስት ወራት የስራ ክንውን ዙሪያ ትናንት ቅዳሜ ጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ከሚመለከታቸው የከተማው ባለድርሻ አካላት ጋር ወይይት ባካሄደበት ወቅት ነው። የወይይቱ ተሳታፊዎች አገልግሎት ለማግኘት ወደ ወረዳ ሲያቀኑ በሁሉም ባይሆንም በአንዳንድ አመራሮች ማመነጫጨቅ እና ማንገላታት እንደሚያጋጥማቸው እንዲሁም ለጥያቄያቸው ምላሽ እንደሚነፍጓቸው ተናግረዋል። ወይይቱን የመሩት የአዲስ አበባ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ አማካሪ
3 days ago1 min read


የታህሳስ ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 9.7 በመቶ ሆኗል ሲል የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ተናገረ።
ጥር 1/2018 የታህሳስ ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 9.7 በመቶ ሆኗል ሲል የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ተናገረ። የታህሳስ 2018 ዓ.ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት መጠን 9.7 በመቶ ደርሷል፤ ይህም በታህሳስ 2017 ዓ.ም ከተመዘገበው 17.0 በመቶ ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ ቅናሽ አሳይቷል ሲል ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል። የወር ከወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በታህሳስ 2018 ዓ.ም በ0.3 በመቶ የቀነሰ ሲሆን፤ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ጋር ሲነጻጸር የ0.8 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች የዋጋ ግሽበት 9.8 በመቶ የደረሰው በዋናነት የአትክልት፣ የሥጋ፣ የስኳር እና የጣፋጭ ምግቦች፣ የወተት ተዋጽኦዎች፣ የፍራፍሬ፣ የዘይትና የቅባት እንዲሁም የሌሎች የምግብ ሸቀጦች ዋጋ በመጨመሩ ነው። በሌላ በኩል የዳቦ እና የጥራጥ
4 days ago1 min read
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ኢንተርፕራይዝ እንዲያቋቁሙ መፈቀዱ እራሳቸውን በገንዘብ እንዲችሉ ያግዛል ተባለ፡፡
ጥር 1/2018 የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ኢንተርፕራይዝ እንዲያቋቁሙ መፈቀዱ እራሳቸውን በገንዘብ እንዲችሉ ያግዛል ተባለ፡፡ ይህም የሚሰጡት ስልጠና ጥራት እንዲኖረው ይረዳል ሲሉ ያነጋገርናቸው የዘርፉ ባለሙያ ጠቅሰዋል፡፡ ባለፈው አመት የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ ወጥቶ ወደ ስራ ገብቷል፡፡ ፖሊሲው ውስጥ ከተካተቱ ጉዳዮች አንዱ ቴክኒክና ሙያ ተቋማት እራሳቸውን በፋይናንስ እንዲችሉ ማድረግ ነው፡፡ ለዚህም የተለያዩ አማራጮችን ያስቀመጠ ሲሆን ኢንተርፕራይዝ አቋቁመው በሚያሰለጥኑበት ዘርፍ የንግድ አገልግሎት እንዲሰጡ ይፈቅዳል፡፡ በሚዛን የግብርና ኮሌጅ የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠሪ አቶ ካሳሁን አይከን ይሄ ለተቋማቱ ምን ይዞላቸው ይመጣል? ስንል ጠይቀናቸዋል። አቶ ካሳሁን የስልጠና ጥራት እንዲኖር ፣ በፋይናንስ እራሱን የቻለ
4 days ago1 min read


የኮሎምቢያው ፕሬዘዳንት ጉስታቮ ፔትሮ የአሜሪካ ጦር ጥቃት ያሰኛጋል አሉ፡፡
ጥር 1/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #ኮሎምቢያ የኮሎምቢያው ፕሬዘዳንት ጉስታቮ ፔትሮ የአሜሪካ ጦር ጥቃት ያሰኛጋል አሉ፡፡ ጉስታቮ ፔትሮ በአሜሪካ የጦር ጣልቃ ገብነት ስጋት ገብቶኛል ያሉት ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ነው፡፡ ባለፈው ሳምንት አሜሪካ በቬኔዙዌላ ላይ ወታደራዊ እርምጃ በመውሰድ የአገሪቱን ፕሬዘዳንት ኒኮላስ ማዱሮን አሳግታ ወደ ኒውዮርክ ማስወሰዷ ይታወቃል፡፡ ከዚያ ወዲህ በርካታ አገሮች በአሜሪካ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት ክፉኛ ስጋት እንደገባቸው ይነገራል፡፡ በአሜሪካ ወታደራዊ እርምጃ ስጋት ገብቶኛል የሚሉት የኮሎምቢያው ፕሬዘዳንት ጉስታቮ ፔትሮ የዋይት ሐውስን አስተዳደር በግላጭ በመንቀር ይታወቃሉ፡፡ ትራምፕ እንደ ቬኔዙዌላ ሁሉ በኮሎምቢያም ላይ ሲዝቱ መቆየታቸው መረጃው አስታውሷል፡፡ #ሶማሊያ የሶማሊያ ፌዴራል መንግስት ሹሞቹ
4 days ago2 min read


የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለተጠቃሚዎች እራሱ ስጋ ለማቅረብ ሚያስችለውን ጥናት እያደረገ መሆኑን ተናገረ፡፡
ታህሳስ 30/2018 የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለተጠቃሚዎች እራሱ ስጋ ለማቅረብ ሚያስችለውን ጥናት እያደረገ መሆኑን ተናገረ፡፡ ድርጅቱ ለገና በዓል 5,164 የቁም እንስሳት እርድ መፈፀሙን ነግሮናል፡፡ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አታክልቲ ገብረሚካኤል አስካሁን ድረስ ከደንበኞች ከበዓል እርድ ጋር በተያያዘ ቅሬታ እንዳልቀረበ ይናገራሉ፡፡ ከበዓሉ ቀደም ባለው ጊዜ ድርጁቱ በቂ ዝግጅት አድርጎ ነበር ያሉት አቶ አታክልቲ ስጋውን ለደንበኞች ለማቅረብ የሚገለገሉባቸው መኪኖችንም እንቅስቃሴ በካሜራ እና በጂፒኤስ ሲከታተሉ እንደነበር ያስረዳሉ፡፡ የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳር ፕሮጀክቶች ህገወጥ የቁም እንስሳት እርድ ከተማ ውስጥ እንዲቀንስ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው በሌላ በኩል ደግሞ አንዳንዶች ወደ ሸገር ከተማ በመሄድ ህገወጥ
5 days ago1 min read


በአዲስ አበባ በመንገድ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚደርሰው ጉዳት ስራው ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ነው ተባለ
ታህሳስ 30/2018 በአዲስ አበባ በየጊዜው የመንገድ ግንባታዎች እንዲሁም ጥገናዎች ቢደረጉም በመንገድ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚደርሰው ጉዳት ግን ስራው ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ነው ተባለ፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… ምህረት ስዩም የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1 WhatsApp : https://whatsapp.com/channel/0029VaAOnG9J3juypE0M4G1O X : https://x.com/shegerfm?s=2
5 days ago1 min read


ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በጤና፣ በግብርና፣ ኢንዱስትሪና በሌሎችም ዘርፎች ምርምር ለማድረግ የኒውክሊየር ቴክኖሎጂን ስትጠቀም ነበረ ተባለ፡፡
ታህሳስ 30 2018 ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በጤና፣ በግብርና፣ ኢንዱስትሪ እና በሌሎችም ዘርፎች ምርምር ለማድረግ የኒውክሊየር ቴክኖሎጂን ስትጠቀም ነበረ ተባለ፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… ቴዎድሮስ ወርቁ
5 days ago1 min read


በዓለም አቀፍ ገንዘብ ድርጅት 32 ዓመት በተለያየ የስራ ሀላፊነት ያገለገሉት ኢትዮዽያዊው አበበ አዕምሮ ሥላሴ በጡረታ ሊገለሉ እንደሆነ ተሰማ
ታህሳስ 30/2018 በከፍተኛ ደረጃ በኢኮኖሚ ባለሞያነት፣ በዓለም አቀፍ ገንዘብ ድርጅት (IMF) 32 ዓመት በተለያየ የስራ ሀላፊነት ያገለገሉት ኢትዮዽያዊው አበበ አዕምሮ ሥላሴ፤ ከ3 ወር በኋላ በጡረታ ሊገለሉ እንደሆነ ተሰማ። አቶ አበበ በዓለም አቀፍ ገንዘብ ድርጅት IMF ከ 30 ዓመት በላይ በተለያየ ኃላፊነት ፣ የባለፉትን 10 ዓመታት ደግሞ የአፍሪካ ዳይሬክተር ሆነው እያገለገሉ ነው። በማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲዎች ቀረፃ እና ትንተና፣ በፋይናንስና በገንዘብ ነክ ፖሊሲ ጉዳዮች፣ በዕዳ ሽግሽግ፣ አጠቃላይ በገንዘብ ቁጥጥር እና ፊስካል ፖሊሲ ሰርተዋል። የ IMF ዋና ዳይሬክተር፣ ክሪስታሊና ጆርጂየቫ፣ አበበ አዕምሮ ስላሴ ከአፍሪካ ዲፓርትመንት ዳይሬክተርነት ከ3 ወር በኋላ ይገለላሉ ብለዋል። ከ2008 ጀምሮ በIMF አፍሪካ ክፍል ዳይሬክተር ሆነው ያገ
5 days ago1 min read


ወ/ሮ ሐይማኖት ዘለቀ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተርነት ሹመት በህዝብ እንደራሴዎች ም/ቤት ፀደቀ።
ታህሳስ 28/2018 ወ/ሮ ሐይማኖት ዘለቀ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተርነት ሹመት በህዝብ እንደራሴዎች ም/ቤት ፀደቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሹመቱን ያጸደቀው 8ኛ መደበኛ ስብሰባውን ዛሬ ባካሄደበት ወቅት ነው። ዛሬ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣንን እንዲመሩ የተሾሙት ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ ያለፈውን አንድ ዓመት ያህል ተቋሙን በዋና ዳይሬክተርነት ሲመሩ የነበሩት ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር )ይተካሉ። ሳምሶን መኮንን(ዶ/ር) በገዛ ፍቃዳቸው ስልጣናቸውን መልቀቃቸው ተነግሯል። ዛሬ ሹመታቸው የጸደቀላቸው ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ ከ20 ዓመታት በላይ በመገናኛ ብዙሃን እና ተያያዥ ሞያ ላይ የቆዩ መሆናቸው ተነግሯል። አዲሷ ተሿሚ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በውጪ ቋንቋ እና ስነ ፁሁፍ እንዲሁም ሁለተኛ ዲግሪያ
Jan 61 min read


በሀገር ውስጥ ላቦራቶሪዎች ጥራታቸው መፈተሽ የማይችሉ ምርቶች ከመነሻ ሀገር የጥራት ማረጋገጫ ይዘው እንደመጡ ከውሳኔ ተደርሷል፡፡
ታህሳስ 27/2018 በሀገር ውስጥ ላቦራቶሪዎች ጥራታቸው መፈተሽ የማይችሉ ምርቶች ከመነሻ ሀገር የጥራት ማረጋገጫ ይዘው እንደመጡ ከውሳኔ ተደርሷል፡፡ ጀነሬተሩ፣ የልብስ ማጠቢያ ማሽን እና ሌላውም በዚህ የፍተሻ ሥርዓት እንዲያልፍ ተወስኗል፡፡ ይህ ደግሞ ተከልሶ የመጣ ፣ ሥርዓት ፣ ከአስመጪዎች በኩል ግን የሚነሳበት ጥያቄ አለ፡፡ ለመሆኑ አሰራሩ ተግባራዊ የሚሆነው እንዴት ነው? ያስፈለገውስ ለምን ይሆን? ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….. ንጋቱ ረጋሣ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Jan 51 min read


የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች 6 ወራት ለቀሩት ሀገራዊ ምርጫ እንዴት እየተሰናዱ ይሆን?
ታህሳስ 27/2018 ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን ለሚካሄደው ቀን ቆርጣለች፡፡ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን መገንቢያ አንዱ መንገድ ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ በዚህ የምርጫ ወቅት የዜጎች ሰብአዊ መብት እንዳይታፈን ተፎካካሪዎችም ሀሳባቸውን በነፃነት እንዲያስረዱ ማድረግ መቻል ሥርዓቱን ነፃ መሆን አንዱ ማሳያ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ሰብአዊ መብት ለማስከበር የቆምን ነን የሚሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች 6 ወራት ለቀሩት ሀገራዊ ምርጫ እንዴት እየተሰናዱ ይሆን? ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….. ምህረት ስዩም የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw
Jan 51 min read


''በገና በዓል ወቅት የሀይል መቆራረጥ እንዳይፈጠር የቅድመ ዝግጅት ስራዬን አጠናቅቄአለሁ'' የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
ታህሳስ 27/2018 በገና በዓል ወቅት የሀይል መቆራረጥ እንዳይፈጠር የቅድመ ዝግጅት ስራዬን አጠናቅቄአለሁ ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ። በበዓሉ እለት እና በዋዜማው የሀይል መቆራረጥ አንዳይኖርም አስቀድሞ የጥገና ስራ እየተሰራ ነው ብሏል፡፡ ከዚህ ቀደም በበዓሉት ወቅት ይፈጠሩ የነበሩ የሀይል መቆራረጦች ለማስቀረት እየሰራ መሆኑን የተናገረው አገልግሎቱ ረቡዕ ታህሳስ 29 ቀን በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በሚከበረው የገና በዓልም ተመሳሳይ ችግር እንዳይፈጠር አስቀድሜ ስራዎችን ሰርቻለሁ ብሏል። አገልግሎቱ ይህንን ያለው የገና እና የጥምቀት በዓላትን በማስመልከት በተከናወኑ የቅድመ ዝግጅት ስራዎቹ ላይ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው። የገና በዓል ከሌሎች በዓላት በበለጠ በደንበኞች ዘንድ የሀይል አጠቃቀሙ ክፍተኛ በመሆኑ የኢትዮጵያ
Jan 52 min read
በኢትዮጵያ አብዛኛው የፋይናንስ ተቋም አሰራሩ አንድ ዓይነት ነው።
ታህሳስ 27/2018 በኢትዮጵያ አብዛኛው የፋይናንስ ተቋም አሰራሩ አንድ ዓይነት ነው። በተለይ በዓል በመጣ ግዜ ፤ በዓሉን ታሳቢ በማድረግ የብድር አገልግሎት የሚሰጡ የፋይናንስ ተቋም ቁጥራቸው ቢጨምር ፤ አንዛኛውን ሰው በፋይናንስ ለማካተት አንደኛው መንገድ ይሆናል ይባላል። በበዓል ወቅት እና የማህበራዊ አገልግሎት ጊዜ ለአንድ ቀንም ቢሆን አስቸኳይ የፋይናንስ አቅርቦት ለማግኘት አብዛኛው የፋይናንስ ተቋም ብድር ሲሰጥ አይታይም፡፡ ይሁንና የማህበራዊ እና የበዓል ሰሞን ወጭዎችን ለመሸፈን የሚያስፈልግ የፋይናንስ አስቸኳይ ብድር አገልግሎት ስራ መጀመሩን ሰምተናል፡፡ ይህ የፋይናንሰ አቀባይ ምንዳ የገንዘብ ቁጠባና ህብረት ስራ ማህበር ይባላል። ደንበኞች ይህን አገልግሎት በአጭሩ እንዴት ያገኙታል? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ተህቦ ንጉ
Jan 51 min read


የይዞታ ማረጋገጫ ሳይኖር፤ የንብረት ታክስ እንዲከፈል የሚያስገድደው ረቂቅ አዋጅ
ታህሳስ 27/2018 መንግስት የባለቤትነት መብት የሌላቸው ሰዎች የይዞታ ማረጋገጫ ባይኖራቸውም የንብረት ታክስ እንዲከፍሉ የሚያስገድድ ረቂቅ አዋጅ እያሰናዳ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ ለመሆኑ የባለቤትነት መብት በሌለበት ሁኔታ ለይዞታ የንብረት ታክስ እንዲከፈል ማድረግ ምን ያክል ትክክለኛ አካሄድ ይሆናል? የንብረት ታክስ የሚከፍለው ግለሰብስ በሂደት መብት እንዲፈጠርለት አያደርግም ወይ? የሚል ጥያቄም ይነሳል፡፡ የህግ ባለሞያ አነጋግረናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….. ንጋቱ ረጋሣ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://youtube.com/@shegerfm1021radio?si=MIGhci0wINMYwCmw Telegram : https://t.me/S
Jan 51 min read


በኢትዮጵያ በጦርነት ምክንያት ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆኑ ሴቶች ላይ ጾታዊ ጥቃት እንደደረሰባቸው ጥናቶች ያስረዳሉ፡፡
ታህሳስ 24/2018 በኢትዮጵያ በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆኑ ሴቶች ላይ ጾታዊ ጥቃት እንደደረሰባቸው የተለያዩ ጥናቶች ያስረዳሉ፡፡ በነበረው ግጭት ሴቶች መደፈርን ጨምሮ ሌሎች ስነልቦናዊና አካላዊ ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ እነዚህ ሴቶች ጾታዊ ጥቃት ከደረሰባቸዉ በኋላ ተመልሰው ከዚህ ቀደም ከሚኖሩት ማህበረሰብ ጋር ኑሯቸውን መግፋ እንደሚከብዳቸው የነገሩን በደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ሳይንስ መምህርና በዚህ ጉዳይ ጥናት ያደረጉት አቶ ዘረብሩክ ዘውዱ ናቸው፡፡ የደረሰባቸዉን ጥቃት ማበረሰቡ በራሱ በበቂ ሁኔታ አልተረዳውም የሚሉት መምህሩ የተለያዩ ተቋማትና የተለያዩ በየዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎች ጥናት ስላደረጉበት ብቻ ጉዳዩን በጥልቀት ማህበረሰቡ ተረድቶታል ማለት አይደለም ይላሉ፡፡ በአንድ ወቅት በተደረገ ጥናት እሳቸውም በተሳተ
Jan 21 min read


የሶማሊላንድ አስተዳደር በግዛቷ የእስራኤል የጦር ሰፈር እንዲገነባ ተስማምቷል መባሉን ሐሰት ነው አለ፡፡
ታህሳስ 24/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #ሶማሊላንድ የሶማሊላንድ አስተዳደር በግዛቷ የእስራኤል የጦር ሰፈር እንዲገነባ ተስማምቷል መባሉን ሐሰት ነው አለ፡፡ እስራኤል ባለፈው ሳምንት አርብ ለሶማሌላንድ የነጻ አገርነት እውቅና ሰጥታለች፡፡ የእስራኤል እርምጃ በሶማሌያ እና በምስራቅ አፍሪካዊቱ አገር አጋሮች ዘንድ ውግዘት አስከትሏል፡፡ የሶማሊያው ፕሬዘዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ ሶማሌላንድ ከእስራኤል እውቅና ለማግኘት የጦር ሰፈር እንድትገነባ መፍቀዷን ተናግረዋል፡፡ ይሄም በደህንነት መረጃዎች የተደረሰበት ነው ማለታቸው አልጀዚራ ፅፏል፡፡ ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በተጨማሪም በእስራኤል ከጋዛ ሰርጥ የሚነቀፉ ፍልስጤማውያን በሶማሌላንድ ለማስፈር ስምምነት ተደርሷል ብለዋል፡፡ የሶማሌላንድ አስተዳደር ግን ይሄ በፍፁም ሐሰት ነው ማለቱ ተሰምቷል፡፡ እስራኤልም ለ
Jan 22 min read


''በጤናና በግብርና ሚ/ር ስር ያሉ 22 ተጠሪ ተቋማት ልዩ ትኩረት የሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎችን በተመለከተ የሚሰሩት ስራ አጥጋቢ አይደለም'' በሚል ተተቹ
ታህሳስ 24/2018 በጤና እና በግብርና ሚኒስቴር ስር ያሉ 22 ተጠሪ ተቋማት ሴቶችን፣ አካል ጉዳተኞችን፣ አረጋዊያንን እና ሌሎች ልዩ ትኩረት የሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎችን በተመለከተ የሚሰሩት ስራ አጥጋቢ አይደለም በሚል ተተቹ፡፡ ትችቱን ያቀረበው የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ነው። ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ በስርዓተ ጾታና በማህበራዊ አሳታፊነት ወይም አካቶ ዙርያ በ22 የጤና ሚኒስቴርና የግብርና ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት ላይ ያደረገውን የምዘና ውጤት ይፋ አድርጓል። ተቋማቱ የተመዘኑትም የሴቶችን፣ የሕፃናትን ፣ የወጣቶችን፣ የአካል ጉዳተኞችን፣ የአረጋዊያንን እና ሌሎች ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጉዳዮች በስራዎቻቸው ምን ያህል አሳትፈዋል? ምን ያህልስ ተጠቃሚነታቸውን አረጋግጠዋል? በሚል ነው። ምዘና ከተደረገባቸው ተቋማት ዉስጥ አብ
Jan 21 min read


‘’በህገወጥ መንገድ ድንበር አቋርጠው የሚሰደዱ ሰዎች ቁጥር ቀንሷል’’ ሲል የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ፡፡
ታህሳስ 24/2018 ‘’በህገወጥ መንገድ ድንበር አቋርጠው የሚሰደዱ ሰዎች ቁጥር ቀንሷል’’ ሲል የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ፡፡ የድንበር ቁጥጥር መበርታት እና በሰው አዘዋዋሪ ደላሎች ላይ የሚወስደው እርምጃ ለቁጥር መቀነስ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብሏል፡፡ በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የህገወጥ የሰዎች ዝውውር መከላከልና የተመላሽ ጉዳይ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ተግይበሉ በአዋሳኝ ድንበር የሚደረገውን ህገወጥ ፍልሰት በተመለከተ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በመተባበር እየተደረገ ባለው ጥብቅ የቁጥጥር ስራ በርካታ ህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን በመያዝ ተጠያቂ እየሆኑ ነው ብለዋል። በዚህም ከዚህ ቀደም በአጎራባች ሀገራት በኩል ይደረጉ የነበሩ በርካታ ህገወጥ ፍልሰቶች እንዲቀንሱ አድርገዋል ይላሉ። በሌላ በኩል ምያንማርን
Jan 21 min read


የልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመክፈል አቅም የሌላቸው ሰዎች በሚኖሩበት አካባቢ ሊስፋፋ ይገባል ተባለ፡፡
ታህሳስ 24/2018 የልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመክፈል አቅም የሌላቸው ሰዎች በሚኖሩበት አካባቢ ሊስፋፋ ይገባል ተባለ፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር በቅርቡ የፌደራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርትቤት በተለያዩ አካባቢዎች ስራ አስጀምሯል፡፡ በአዳሪ ትምህርትቤቶቹ ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎች በ8ተኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና የተሻለ ውጤት ያመጡና የትምህርት ሚኒስቴር የሰጠውን የመግቢያ ፈተና ማለፍ የቻሉት ብቻ ናቸው፡፡ ይህ ስራ በባለሙያዎች እንዴት ይታያል? በምንስ መንገድ መመራት አለበት? የዘርፉን ባለሙያ ጠይቀናል፡፡ የትምህርት ባለሙያ እና በደብረ ብርሃን ዩንቨርስቲ መምህር ሆኑት ዳምጠው ወልዴ (ዶ/ር) ከዚህ ቀደም በግልና በምንግስት ልዩ አዳሪ ትምህርትቤቶችን ለማስፋፋት መሞከሩን ያስታውሳሉ፡፡ እንዲህ አይነት ትምህርትቤቶች መስፋፋታቸው ክ
Jan 21 min read


የፍትህ ሚኒስቴር "የሰው እና ሰነድ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ፤ በማንነታቸው እና በፖለቲካ አቋማችው የታሰሩ ሰዎች ለከፍተኛ ሰብዓዊ ጉዳት " ተዳርገዋል ሲሉ የምክርቤት አባል ተናገሩ፡፡
ታህሳስ 23/2018 የፍትህ ሚኒስቴር "የሰው እና ሰነድ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ፤ በማንነታቸው እና በፖለቲካ አቋማችው የታሰሩ ሰዎች ለከፍተኛ ሰብዓዊ ጉዳት " ተዳርገዋል ሲሉ የምክርቤት አባል ተናገሩ፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት በበኩሉ በማንነቱ ሆነ በፖለቲካ አቋሙ የሚታሰርም ሆነ የተሰረ ሰው እንደሌለ ተናገሮ ግን እንድ ሰው የፖለቲካ ግቡን ለማሳካት በህገወጥ መንገድ የሚንቀሳቀስ ፖለቲከኛም ፣የመንግስት ሰራተኛም ሆነ የመንግስት ሃላፊ ላይ የህግ ተጠያቂነትን አረጋግጣለሁ ብሏል፡፡ ይህ ጉዳይ የተነሳው የፍትህ ሚኒስቴር ዛሬ በፓርላማ መደበኛ ስብሰባ ላይ ቀርቦ ከምክርቤት አባላት ለተነሱለት ጥያቄዎች የ25 ደቂቃ ምላሽ እና ማብራርያ ባቀረበበት ወቅት ነው፡፡ የምክርቤት አባሉ አበባው ደስአለው (ዶ/ር) የፍትህ ሚኒስቴር ዋነኛው ስራው ክስ በ
Jan 12 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page








