top of page


ኢትዮዽያ በአለም የሎጅስቲክስ ሜዳ
የካቲት 27/2018 የሎጅስቲክስ ስራ ፍፁም የሰላም መስመር እና እውቀት ይፈልጋል፡፡ ሎጅስቲክስ በኢትዮጵያ እንዲዘምን፣ እንዲቀላጠፍ አሁንም ብርቱ ስራ ይጠይቃል። እቃዎችን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ለማንቀሳቀስ፣ መያዝ፣ ማከማቸት እና ማስተናገድ ፤ በየትኛውም የአለም መሮጫ ኮሪደር እና ባህር ማገላበጥ ፤ በአየር በየብስ ምድር ለመላወስ ጥንቅቅ ያለ የሎጅስቲክስ ስራ ይፈልጋል። ለዚህ ደግሞ በየጊዜው በአለም በሚደረጉ ጉባኤዎች እና የሎጅስቲክስ ማህበራት ላይ በኃላፊነት ቦታ መገኘት እንደሚያስፈልግ ይታመናል። በተለይ ከአፍሪካ ብቸኛው የአለም ፍሬይት ፎርዋርደርስ ማህበር ፊያታ የቦርድ አባል እና በ ኢትዮጵያም የማህበሩ ፕሬዝዳንት አቶ ዳዊት ውብሸት በዚህ ጉዳይ ስጋት እንዳላቸው ነግረውናል። ኢትዮዽያ በአለም የሎጅስቲክስ ሜዳ ፤ በጭነት መርከቦች እና አጠቃላ
3 days ago1 min read


ደንበኞች ባሉበት ሆነው የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም ብቻ የቆጣሪ ንባባቸውን የሚያስገቡበት አሰራር በሙከራ ደረጃ መጀመሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አግልግሎት ተናገረ፡፡
የካቲት 27/2018 ደንበኞች ባሉበት ሆነው የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም ብቻ የቆጣሪ ንባባቸውን የሚያስገቡበት አሰራር በሙከራ ደረጃ መጀመሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አግልግሎት ተናገረ፡፡ ይህም በተደጋጋሚ ከደንበኞች የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት ይረዳኛል ብሏል። የሙከራ ትግበራው ከ16 ሺህ በላይ የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች ባሉበት የሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን መጀመሩን የተቋሙ የኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ አንዋር አብራር ነግረውናል ፡፡ ሥራ አስፈፃሚው የዲጂታል አሰራሩ ለደንበኞች በቀላሉ ተደራሽ ለመሆን፣ የፍጆታ ሂሳብን በወቅቱ ለመፈጸም፣ ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት እንዲሁም ጊዜና ወጪን ለመቆጠብ ያስችላል ብለውናል፡፡ በዚህም ከየካቲት 13 ቀን እስከ የካቲት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ደንበኞች የፍጆታ ንባባቸውን በቀላሉ በቤታቸው ሆነው ለዚሁ አ
3 days ago1 min read


የባቱ - አርሲ ነገሌ 57 ኪሎ ሜትር የፍጥነት መንገድ ግንባታ ዋና ዋና ሥራዎቹ ተጠናቅቀዋል ተባለ።
የካቲት 26/2018 የሞጆ - ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ አካል የሆነው የባቱ - አርሲ ነገሌ 57 ኪሎ ሜትር የፍጥነት መንገድ ግንባታ ዋና ዋና ሥራዎቹ ተጠናቅቀዋል ተባለ። የመንገድ ኮሪደሩ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ እና ምዕራብ አርሲ ዞኖች የሚገኙትን የባቱ ከተማን፣ የአዳሚ ቱሉ እና አርሲ ነገሌ ወረዳዎችን ጨምሮ ከ17 በላይ ቀበሌዎችን ያስተሳስራል ተብሏል። የመንገድ ግንባታው የአዲስ አበባ - ሞያሌ - ናይሮቢ - ሞምባሳ የመንገድ ኮሪደር አካል መሆኑ ተነግሯል። ግንባታውን ለማከናወን ከዓለም ባንክ የተገኘ 5.3 ቢሊዮን ብር ወጪ መሆኑ ተነግሯል። 57 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የባቱ - አርሲ ነገሌ የፍጥነት መንገድ ግንባታ በ90 ሜትር የመንገድ ወሰን ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፤ የጎን ስፋቱ የመንገድ አካፋይን ጨምሮ 31.6 ሜትር መሆኑን የኢትዮጵያ መን
3 days ago2 min read


በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት ዓመታት በነበሩ ግጭቶች ከ300 በላይ ትምህርት ቤቶች ተዘግተው እንደነበር ተነግሯል።
የካቲት 26/2018 በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት ዓመታት በነበሩ ግጭቶች ከ300 በላይ ትምህርት ቤቶች ተዘግተው እንደነበር ተነግሯል። ይህም የክልሉን አጠቃላይ 20 በመቶ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ማራቁን የክልሉ ምክትል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በሽር አብዱረሂም ተናግረዋል። አሁን ላይ ግን በክልሉ በተሰሩ ስራዎች በአብዛኛው በሚባል ደረጃ ትምህርት ቤቶች ወደ መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደታቸው መመለሳቸውን ኃላፊው አንስተዋል። ኃላፊው ይህንን ያሉት ኩሶ ኢንተርናሽናል የተባለ የተራድኦ ተቋም በክልሉ ባለፉት 6 ዓመታት ሴት ተማሪዎችን ለዩንቨርሲቲ የማብቃት ፕሮጀክት (U_Girls project) የማጠቃለያ መድረክ ላይ ነው። የትምህርት ቢሮ ኃላፊው በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመማር ማስተማር ችግሮችን በመፍታት ሂደት ውስጥ የኩሶ ኢንተርናሽናልን
3 days ago1 min read


ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ለመደገፍ የሚያስችል ሁለተኛ ዙር ፕሮጀክት ወደ ስራ መግባቱ ተነገረ፡፡
የካቲት 26/2018 በተለያዩ አካባቢዎች ባለ የሰላም እጦት እና የሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ለመደገፍ የሚያስችል ሁለተኛ ዙር ፕሮጀክት ወደ ስራ መግባቱ ተነገረ፡፡ በአለም ባንክ የሚደገፈው እና ለ5 ዓመታት ይቆያል የተባለው ይህ ፕሮጀክት ሊጠናቀቅ 2 ዓመታት እንደቀረው ሲነገር ሰምተናል፡፡ በዚህም ሁለተኛው ምዕራፍ እና በሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ይተገበራል የተባለው ስራ ወደ ትግበራ መግባቱ ተነግሯል፡፡ በጦርነት ምክንያት ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች የጤና ድጋፍ እንዲያገኙ፣ የኢኮኖሚ ምስቅልቅል የገጠማቸው ወደ ቀድሞ ስራቸው እንዲመለሱ እና ሌሎች ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮቻቸው ላይ የሚሰራ ፕሮጀክት መሆኑ ተነግሮለታል፡፡ ፕሮጀክቱም በ5 ክልሎች የሚተገበር ሲሆን አማራ፣ ትግራይ፣ ኦሮሚያ፣ አፋር፣ ቤኒሻን
4 days ago1 min read


ከጎርጎርሳውያኑ ከ2024 ጀምሮ ኢትዮጵያ የውጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ከአፍሪካ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች ተብሏል።
የካቲት 26/2018 ከጎርጎርሳውያኑ ከ2024 ጀምሮ ኢትዮጵያ የውጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ከአፍሪካ ሁለተኛ ፤ ከምስራቅ አፍሪካ ደግሞ አንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች ተብሏል። በቀጣይ ወር በአዲስ አበባ በሚዘጋጀው የኢንቨስትመንት ፎረም ላይ ብቻ ከ2.4 ቢሊየን ዶላር በላይ ግምት ያለው የኢንቨስትመንት ስምምነት ይፈረማል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተነግሯል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እና የገንዘብ ሚኒስቴር ፎረሙን አስመልክተው ትናንት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት እና ሌሎች ዘርፎችን የሚደግፉ ከ123 በላይ አዳዲስ ህጎችን ባለፉት ሰባት ዓመታት አውጥታለች ተብሏል። ማሻሻያ የተደረገባቸው ህጎች ከተጨመሩበት ደግሞ ቁጥሩ ከ198 እንደሚልቅ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ዶክተር ዘለቀ ተመስገን ተናግረዋል።
4 days ago2 min read


አዋሽ ባንክ ለ7 ግብረ ሰናይ ድርጅቶች 25 ሚሊዮን ብር ሰጠ።
የካቲት 26/2018 አዋሽ ባንክ ለ7 ግብረ ሰናይ ድርጅቶች 25 ሚሊዮን ብር ሰጠ። ባንኩ ለግብረ ሰናይ ድርጅቶቹ ድጋፉን ያደረገው ያለንበትን የረመዳን ወርን ምክንት በማድረግ ነው። 25 ሚሊዮን ብር ድጋፍ የተደረገላቸው ድርጅቶችም ህጻናትን፣ በአረጋዊያንን እና አካል ጉዳተኞችን በመደገፍና በመንከባከብ ላይ የተሰማሩ መሆናቸው ተጠቅሷል። ወንድም ካሊድ ፋውንዴሽን፣ የስራ ለና የበጎ አድርጎ ድርጅት፣ ተስፋ አዲስ ፓረንትስ ቻይልድሁድ ሰፖርት ኦረጋናይዜሽን፣ ዘ ችልድረንስ ኸርት ፈንድ ኦፍ ኢትዮጵ፣ እዝነት አካል ጉዳተኛ ህፃናትና ወላጆች መርጃ ድርጅት እና አብደላ ኢብኑ ኡሚ መክቱም ቁራን ማህበር ናቸው ድጋፉ የተደረገላቸው። አዋሽ ባንክ የ1447ኛውን የረመዳን ወር ምክንያት በማድረግ ትናንት ምሽት በሸራተን አዲስ ሆቴል ባዘጋጀው የኢፍጣር መርሃ-ግብር ላ
4 days ago1 min read


አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ በውስጡ ምን ይዟል?
የካቲት 25/2018 የሚኒስትሮች ምክር ቤት 53ተኛ ስብሰባውን ባደረገበት ወቅት በቱሪዝም ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ውይይት አድርጎ በምክር ቤቱ ከፀደቀበት ቀን ጀምሮ ወደ ስራ እንዲገባ ፈቃድ ሰጥቷል፡፡ ኢትዮጵያ የቱሪዝም ፖሊሲዋን ለመጨረሻ ጊዜ ያሻሻለችው በ2001 ዓ.ም ነበር፡፡ ታዲያ አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ በውስጡ ምን ይዟል? ስንል በፖሊሲ ማርቀቁ ላይ የተሳተፉትን አቶ ኤንዲ አሰፋን ጠይቀናቸዋል፡፡ የቱሪዝም ባለሙያው አቶ ኤንዲ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ወደ ስራ እንዲገባ የተፈቀደው አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ በዘርፉ ከዚህ ቀደም ይነሱ ለነበሩ ችግሮች ምላሽ ይዞ መጥቷል ይላሉ፡፡ ከዚህ ቀደም ቱሪዝም መሰረተ ልማትን በተመለከተ በፖሊሲ ደረጃ የተቀመጠ ነገር አልነበረም አዲሱ ፖሊሲ በዚህ ዙሪያ ምላሽ አለው በዘርፉ የተማሩ ባለሙያዎችም እንዴት መሰማራት እንዳለባቸው
4 days ago1 min read


አሁን ላይ ሁሉም ክልሎች ከፌዴራሉ ጋር ተመሳሳይ ይዘት ያለው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ አዘጋጅተው ጨርሰዋል ተባለ
የካቲት 25/2018 አሁን ላይ ሁሉም ክልሎች ከፌዴራሉ ጋር ተመሳሳይ ይዘት ያለው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ አዘጋጅተው ጨርሰዋል ተባለ። በተለያየ ምክንያት አዋጁን የማዘጋጀቱ ስራ በክልሎች ተጓቶ እንደቆየ የፌዴራል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ተናግሯል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ በፌዴራል ደረጃ መሻሻሉን ተከትሎ ክልሎችም ተመሳሳይ ማዕቀፍ ያለው ህግ ማዘጋጀት እንዳለባቸው ተጠቅሶ በዚሁ ላይ ሲሰራ መቆየቱ ተነግሯል። ክልሎች ተመሳሳይ ይዘት ያለው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ማውጣት አለባቸው የተባለው የፌዴራሉ አዋጅ ተፈጻሚነት በፌዴራል በሚመዘገቡት ላይ ብቻ ስለሆነ ነው ተብሏል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ እንዳሉት የውጪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ወ
4 days ago2 min read


‘’በአርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ ጃዊ ቀበሌና በሮቤ ወረዳ ገባ ቀበሌ በተፈጸመ ጥቃት ቁጥራቸው በውል ያልተለዩ ሰዎች መገደላቸውን አረጋግጫለሁ ’’
የካቲት 25/2018 በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን የካቲት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በዞኑ ሽርካ ወረዳ ጃዊ ቀበሌ እና በሮቤ ወረዳ ገባ ቀበሌ በተፈጸመ ጥቃት ቁጥራቸው በውል ያልተለዩ ሰዎች መገደላቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አረጋግጫለሁ አለ፡፡ የሕይወታቸው ካለፈው በተጨማሪ፣ አካል ጉዳት፣ እገታ እንዲሁም መፈናቀል የደረሰባቸው ሰዎች አንዳሉ በተለያዩ መንገዶች ባሰባሰብኳቸው መረጃዎች አረጋግጫለሁ ብሏል። ጥቅቱንም የፈጸመው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (በተለምዶ “ኦነግ ሸኔ”) መሆኑን ኮሚሽኑ ባወጣው መገልጫ አስረድቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በአርሲ በተለያዩ ወረዳዎች በአዲስ መልክ በቀጠለው ጥቃት የ21 ንጹሐን ህይወት ማለፉን መናገሩ ይታወሳል፡፡ የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ
4 days ago2 min read


እስራኤል በመላዋ ኢራን በአገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤት ቢሮዎች እና ፅህፈት ቤቶች በላይ ያነጣጠረ ታላቅ ድብደባ ፈፀምኩ አለች፡፡
የካቲት 25/2018 እስራኤል በመላዋ ኢራን በአገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤት ቢሮዎች እና ፅህፈት ቤቶች በላይ ያነጣጠረ ታላቅ ድብደባ ፈፀምኩ አለች፡፡ በሊባኖስ ድብደባ እየፈፀመች መሆኑን ቢቢሲ ፅፏል፡፡ የርዕሰ ከተማዋ ቤይሩት ደቡባዊ ክፍል ነዋሪዎችም አካባቢውን ለቅቀው እንዲወጡ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች ተብሏል፡፡ እስራኤል እና አሜሪካ በጣምራ በኢራን ላይ ድብደባ መፈፀም ከጀመሩ ወዲህ የሊባኖሱ ታጣቂ ቡድን ሔዝቦላህ ወሰን አሻግሮ ወደ እስራኤል ሮኬቶችን እየተኮሰ መሆኑ ይነገራል፡፡ የሊባኖሷ ርዕሰ ከተማ ቤይሩት ደቡባዊ ክፍል የሄዝቦላህ መሪዎች መናኽሪያ ነው ይባላል፡፡ ሔዝቦላህ የኢራን የጦር እና የፖለቲካ አጋር እንደሆነች መረጃው አስታውሷል፡፡ በሌላ መረጃ ሲሪላንካ አቅራቢያ የኢራን የጦር መርከብ መስመጡ ተሰምቷል፡፡ በኔፓን የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች የ
4 days ago1 min read


በበጀት ዓመቱ በመንፈቅ ዓመት በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ 8,183 ሊትር ነዳጅ መወረሱን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ተናገረ፡፡
የካቲት 25/2018 በበጀት ዓመቱ በመንፈቅ ዓመት በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ 8,183 ሊትር ነዳጅ መወረሱን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ተናገረ፡፡ ህገወጥ የነዳጅ ዝውውሩ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ሲፈፀም የተገኘ ነው፡፡ ቢሮው በውሃ ኮዳ እና በሌሎች ያልተፈቀዱ እቃዎች ሲጓጓዙ ተገኝተዋል ካለው 8,183 ሊትር ነዳጅ ውስጥ ናፍጣ 5,900 ሊትር ከ2,000 ሊትር በላይ ቤንዚን እና ነጭ ጋዝን እንደሆነ ተሰምቷል፡፡ በከተማዋ ባሉት ሁሉም ማዲያዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ ነው ያለው ቢሮው በህገ-ወጥ ንግድ ላይ የተሰማሩትን ፣ ነዳጅ እያላቸው የለንም የሚሉትን እርምጃ እየወሰድንባቸው ነው ብሏል ቢሮው፡፡ በዚህም ባለፉት 6 ወራት ነዳጅ እያላቸው ጨርሰናል በማለት አገልግሎት ያቆሙ ሶስት ማደያዎችን ክስ ተመስርቶባቸው እንዲታሸጉ ተደርጎ እንደገና የ
4 days ago1 min read


ከማረሚያ ቤት በሮቶ የሚወጣ ቆሻሻ አስመስለው የህግ ታራሚዎችን ያስመለጡ የማረሚያ ፖሊስ አባላት መቀጣታቸው ተነገረ፡፡
የካቲት 25/2018 ከማረሚያ ቤት በሮቶ የሚወጣ ቆሻሻ አስመስለው የህግ ታራሚዎችን ያስመለጡ የማረሚያ ፖሊስ አባላት መቀጣታቸው ተነገረ፡፡ ይህንን የሰማነው ከፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ነው፡፡ ድርጊቱ ግን ግላዊ ጥቅማቸውን በማስቀደም ከህግ ታራሚዎች ጋር ቀድመው ተመሳጥረው ለማስጠፋት ዘዴ በዘየዱ የማረሚያ ፖሊስ አባላት ተፈፅሟል ሲልም ኮሚሽኑ አክሏል፡፡ በእርምት ላይ ይገኙ የነበሩት 1ኛ የህግ ታራሚ ቢኒያም ካህሳይ ገብሩ እና 2ኛ የህግ ታራሚ ዳንኤል ጎይቶም ተስፋዬ እየታረሙ ከሚገኙበት የከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ከሚኖሩበት ዞን ውጥተው በመጥፋታቸው ባደረግሁት ክትትል እና ማጣራት ነው ያስመለጧቸው አጃቢ የፖሊስ አባላት እንደሆኑ ደርሼበታለሁ ብሏል ኮሚሽኑ፡፡ ሁለቱ የህግ ታራሚዎች ለመጥፋት ይመቸናል ያሉትን ሃሳብና
4 days ago1 min read


በኢትዮጵያ የዛሬ 51 ዓመት በዛሬው ቀን የገጠር መሬት አዋጅ ታወጀ፡፡
#ታሪክን_የኋሊት በኢትዮጵያ የዛሬ 51 ዓመት በዛሬው ቀን የገጠር መሬት አዋጅ ታወጀ፡፡ የካቲት 25 ቀን 1967 የወጣው የመሬት አዋጅ ከዚያ በፊት ሰፍኖ የቆየውን የመሬት አጠቃቀምና ስሪት ለውጦ ከባለርስቱ ወደ አራሹ ገበሬ ያዛወረ አዋጅ ነበር፡፡ የመሬትን ባለቤትነት ላራሹ የማድረግ አስፈላጊነት ጥያቄ በጊዜው ለነበረው ንጉሳዊ መንግስት ከተለያዩ ክፍሎች ሲቀርብ ቆይቷል፡፡ ገበሬዎች በሰላማዊና በአመፅ ጥያቄያቸውን አቅርበዋል፡፡ የጊዜው የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችም በተደራጀ መልኩ በአመፅ ጥያቄውን ሲያነሱ ቆይተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ያለው የመሬት ስሪት ፣ በርስትነት በገባርነት የሚያዝ ሆኖ ቆይቷል፡፡ መሬት በአብዛኛው ትውልድ ቆጥሮ ወይም በውርስ የሚይዙት ፣ ሲሆንም ነባሩን ነዋሪ አፈናቅሎ በአገልግሎትና በስጦታ የሚሰጥ ይዞታ ነበረው፡፡ በአገልግሎትና በስጦታ በሰ
5 days ago2 min read


የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የአየር እና የባህር ሀይሎች እንዳልነበሩ አድርገን አውድመናቸዋል አሉ፡፡
የካቲት 25/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #አሜሪካ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የአየር እና የባህር ሀይሎች እንዳልነበሩ አድርገን አውድመናቸዋል አሉ፡፡ ትራምፕ የኢራንን የአየር እና የባህር ሀይሎች እንዳልነበሩ አድርገን ደምስሰናቸዋል ያሉት በዋይት ሐውስ ከጀርመኑ መራሄ መንግስት ፍሬድሪክ ሜርዝ ጋር ከተመካከሩ በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሆነ አልጀዚራ ፅፏል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኢራን የባህር እና የአየር ሀይል እንዳይኖራት ማድረጋቸው ትራምፕ ተናግረዋል፡፡ አሜሪካ እና እስራኤል ካለፈው ሳምንት ቅዳሜ አንስቶ በጣምራ በኢራን ላይ ከባድ ድብደባ እየፈፀሙ ነው፡፡ ቢቢሲ እንደፃፈው ትራምፕ የኢራንን የጦር አቅም አነካክቼዋለሁ ቢሉም ፋርሳዊቱ አገር በእስራኤል እና በቀጠናው በሚገኙ የአሜሪካ ተቋሞች ላይ የአፀፋ ጥ
5 days ago2 min read


የኤ ኤፍ ጂ ኤርክራፍት ፋይናንስ ጀርመን (AFG) እህት ኩባንያ የሆነው ኤ ኤፍ ጂ አቪየሺን አየርላንድ ኩባንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው አፍሪካ ሀገራት መግባቱን ተናገረ።
የካቲት 24/2018 በአውሮፕላን ንግድና ሀብት አስተዳደር የሚታወቀው ኤ ኤፍ ጂ ኤርክራፍት ፋይናንስ ጀርመን (AFG) እህት ኩባንያ የሆነው ኤ ኤፍ ጂ አቪየሺን አየርላንድ ኩባንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው አፍሪካ ሀገራት መግባቱን ተናገረ። ኩባንያው ለአፍሪካ ስራው ሲልም ሁለት ከፍተኛ ባለሞያዎቹን በአፍሪካ ተገኝተው እንዲሰሩ እንደመደባቸው ባወጣው መግለጫ ተናግሯል። AFG አቪዬሽን አየርላንድ የናይጄሪያው ካሊ ኤር ሁለት CRJ1000 አውሮፕላኖች ባለቤት እንዲሆን ማስቻሉን ተናግሯል። በዚህም የተነሳ የአፍሪካ ሀገራት አየር መንገዶች፣ አፕሬተሮች፣ የመንግሥት እና የአቪዬሽን ዘርፍ ሀላፊዎች ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለቸው ተረድቻለሁ ብሏል። ይህ ፍላጎት የአፍሪካ የአቪዬሽን ዘርፍ በአለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀየረ መምጣቱን ያሳል ሲልም ኩ
5 days ago2 min read


በሚቀጥሉት 10 ቀናት በአብዛኛው የኢትዮጵያ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር የሚቴዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ተናገረ
የካቲት 24/2018 በሚቀጥሉት 10 ቀናት አዲስ አበባን ጨምሮ በአብዛኛው የኢትዮጵያ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቴዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ተናገረ፡፡ አሁን ያለንበት የየካቲት ወርን ጨምሮ እስከ ግንቦት ድረስ በሚዘልቀው የበልግ ወቅት ሰሞኑን እተስተዋለ ያለው የአየር ሁኔታ ለውጥ የሚጠበቅ ነው ብሏል ኢንስቲትዩቱ፡፡ በዚህ ወቀት የደቡብ አጋማሽ የሃገሪቱ ክፍል ማለትም ሶማሌ ክልል ደቡባዊ ክፍል፣የጉጂና ቦረና ዞኖች፣የሲዳማ ክልል ዞኖች፣የደቡብና ደቡብ ምዕራብ ክፍሎች እስከ 55 በመቶ የሚሆነውን የዝናብ መጠን የሚያገኙበት ዋንኛ የዝናብ ወቅታቸው ነው፡፡ በተጨማሪም የደቡብና ምስራቅ ትግራይ ዞኖች፣የምስራቅ አማራ ዞኖች፣የምስራቅ የሃገሪቱ አካባቢዎች፣አዲስ አበባና የመካከለኛው ኢትዮጵያ ክፍሎች ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው
5 days ago1 min read


የአንድ ሀገር መረጃ በሌሎች ሀገሮች እጅ ቢገባ ምን ሊያስከትል ይችላል?
የካቲት 24/2018 በአሁኑ ጊዜ መረጃ ብዙ ነገሮችን የመበየን አቅም እንዳለው ይነገራል፡፡ ሀገራት ከሃገራት ጋር በሚያደርጉት አብሮ ለመስራት የጋራ ስምምነቶች ቀድሞ ከሚነሱ ጉዳዮች መካከል የዲጂታሉ ዘርፍ ይገኝበታል፡፡ ለመሆኑ የአንድ ሀገር የጤና፣ የማዕድን የሌላ ሌላውም ዘርፍ መረጃ በሌሎች ሀገሮች እጅ ቢገባ ምን ሊያስከትል ይችላል? ስንታየሁ ሂርጳሳ(ዶ/ር ) በአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የዳታ ምህንድስና ምርምር መምህር ናቸው፡፡ የአንድ ሀገር መረጃ በሌሎች ሃገራት እጅ ላይ ቢገባ ስለሚያስከትለው ጉዳት ነግረውናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… ማርታ በቀለ
5 days ago1 min read


እስራኤል በኢራን ላይ ድንገተኛ የሚሳኤል ጥቃት መፈፀሟ ተነገረ፡፡
የካቲት 21/2018 እስራኤል በኢራን ላይ ድንገተኛ የሚሳኤል ጥቃት መፈፀሟ ተነገረ፡፡ አልጀዚራን ጨምሮ የተለያዩ አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጥቃቱን የተመለከተ መረጃን በሰበር ወሬ ይዘው ቀርበዋል፡፡ እስራኤል በፈፀመችው የሚሳኤል ጥቃት በቴህራን ማዕከላዊ ከተማ የፍንዳታ ድምፅ መሰማቱ ተሰምቷል፡፡ ፋርስ የወሬ ምንጭ እንደዘገበው በማዕከላዊ ቴህራን ዩኒቨርስቲ ጎዳና እና ጃዋሆሪ በተባሉት ማዕከላዊ የቴህራን ክፍል ተደጋጋሚ የሚሳኤል ጥቃት ተሰንዝሯል፡፡ የእስራኤሉ የመከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እርምጃው እራስን ከጥቃት የመጠበቅና ቀርቦ የመከላከል ነው ብለውታል፡፡ አሶሼትድ ፕሬስ የመረጃ ምንጭ ደግሞ የእስራኤል ጥቃት የተፈፀመው በኢራን ዋና ከተማ በከፍተኛ መንፈሳዊው መሪው አያቶ አሊ ካሚኒ ቢሮ አካባቢ ነው ብሏል፡፡ ዝርዝር መረጃ
Feb 281 min read


''ደንብ አስከባሪ ባለሞያዎች በሞያ ስነ ምግባር ታንፀው እንዲሰሩ እያደረግሁ ነው'' የደንብ ማስከበር ባለስልጣን
የካቲት 20/2018 ደንብ አስከባሪዎች ህግን በተከተለ መልኩ እና ሞያዊ ስነ ምግባርን ጠብቀው የተሰጣቸውን ሀላፊነት እንዲወጡ እያደረግሁ ነው ሲል የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ በማስከበር ባለስልጣን ተናገረ። ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከዚህ ቀደም አልፎ አልፎ በደንብ አስከባሪዎች የሚፈጸሙ የሥነ ምግባር ጥሰቶች አሁን እየቀነሱ ነው ብሏል። ከዚህ ቀደም ህግን ለማስከበር አልፎ አልፎ በደንብ አስከባሪዎች በኩል ይስተዋሉ የነበሩ የስነ ምግባር ግድፈቶች እንዳይኖሩ እየሰራ መሆኑንም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ተናግሯል። ደንብ አስከባሪዎች ህግን በተከተለ መልኩ እና ሙያዊ ስነ-ምግባርን ጠብቀው የተሰጣቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ፣ ማህበረሰቡን ስነ-ምግባር በተሞላበት መልኩ እንዲያገለግሉ ለማስቻል የስነ ምግባር ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረገ መሆኑን ሰምተናል። ከዚህ ቀደም
Feb 271 min read


ኢትዮጵያ የምታካሄደውን ሀገራዊ ምክክር በተመለከተ መገናኛ ብዙሀን በኃላፊነት ሊሰሩ ይገባል ተባለ፡፡
የካቲት 20 2018 ኢትዮጵያ የምታካሄደውን ሀገራዊ ምክክር በተመለከተ መገናኛ ብዙሀን በኃላፊነት ሊሰሩ ይገባል ተባለ፡፡ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ በሚከውናቸው ስራዎች አካታችነቱን የጠበቀ እንዲሆንና ሃገራዊ ምክክሩ የታለመለትን ዓላማ እንዲያሳካ መገናኛ ብዙሃን ብዙ ሃላፊነት አለባቸው ተብሏል፡፡ ይህ የተባለው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከመገናኛ ብዙሃን ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር ትናንት በአዳማ ከተማ ባደረገው ውይይት ነው፡፡ መገናኛ ብዙሃን በተለይ የሀገራዊ ምክሩን ሂደት በተመለከተ የሚከውኗቸው ስራዎች በደንብ የተጠኑ በኋላም ሊያመጡት የሚችለው ጥሩም ይሁን አሉታዊ ተጽዕኖ ተመዝኖ ሙያዊ ኃላፊነት በተሞላበት መንገድ መሆን አለበት ሲሉ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር ሙሃመድ ድሪር ተናግረዋል፡፡ ሚዲያ በሀገር ግንባታ ላይ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ
Feb 271 min read
ፕሮግራሞች
bottom of page

