top of page

ነሀሴ 16 2017 - የዲጂታል የአድራሻ ሥርዓት በ6 ከተሞች በ4 ወር ውስጥ ስራ እንደሚጀምር የስፔስ ሳይንስና ጂኦ እስፓሻል ኢንስቲትዩት ተናገረ

  • sheger1021fm
  • 2 days ago
  • 1 min read

የዲጂታል የአድራሻ ሥርዓት አዲስ አበባን ጨምሮ በ6 ከተሞች በ4 ወር ውስጥ ስራ እንደሚጀምር የስፔስ ሳይንስና ጂኦ እስፓሻል ኢንስቲትዩት ተናገረ፡፡

ree

ተጨማሪ በ9 ከተሞች ላይ የዲጂታል የአድራሻ ስርዓተ ስራዎች እየተሰራ ሲሆን በ2018 በጀት ዓመት አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ ነው ተብሏል፡፡


የስፔስ ሳይንስና ጂኦ እስፓሻል ኢንስቲትዩት የዲጂታል አድራሻ ሥርዓት ፕሮጀክት ማናጀር አግማሴ ገበየሁ እንደነገሩን በአዲስ አበባ፣ ባህር ዳር ጨምሮ በ6 ከተሞች የዲጂታል የአድራሻ ሥርዓት ተጠናቆ ሙከራ እየተደረገ ነው፡፡


በቢሾፍቱ ከተማ ይህ አገልግሎት ወደ ስራ ገብቷል ያሉት አቶ አግማሴ ገበየሁ በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሙከራ ተደርጎ ወደ ስራ መግባቱን ነግረውናል፡፡


የዲጂታል አድራሻ ሥርዓቱ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ወደ አገልግሎት ሲገባ በዲጂታል መንገድ እየተሰጡ ያሉ አገልግሎቶች የበለጠ ታማኝ እንዲሆኑና ስራዎች እንዲቀላጠፉ ያደርጋል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበታል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




댓글


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page