top of page

ነሀሴ 16 2017 - ኦፌኮ በ2018 ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው ምርጫ አስቻይ ሁኔታ ከሌለ ላይሳተፍ እንደሚችሉ ተናገረ

  • sheger1021fm
  • 1 day ago
  • 1 min read

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ፓርቲ ( #ኦፌኮ ) በ2018 ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው ምርጫ አስቻይ ሁኔታ ከሌለ ላይሳተፍ እንደሚችሉ ተናገረ፡፡


ፓርቲው ይህን ካደረገ ለሁለት ተከታታይ ምርጫ ራሱን ያገልላል ማለት ነው፡፡


የፓርቲው ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ሙላቱ ገመቹ ከወራት በኋላ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው ምርጫ ላይ ለመሳታፍ ተንቀሳቅሶ የምርጫ ቅስቀሳ ለማድረግ እና በነጻነት ለመምረጥ አስቻይ ሁኔታ ያስፈልጋል ሲሉ አስረድተዋል፡፡


ፓርቲው ከ4 ዓመት በፊት ተደርጎ በነበረው ሀገራዊ ምርጫም አልተሳተፈም፡፡


በቀጣይ በሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የማይሳተፍ ከሆነ ደግሞ በምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ስነ ምግባር አዋጅ መሰረት ህጋዊ እውቅናው ይሰረዛል፡፡


ይህን በተመለከተ የጠየቅናቸው የፓርቲው ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመበር አቶ ሙላቱ ገመቹ ብንሰረዝም እንሰረዝ እንጂ አስቻይ ሁኔታ ከሌለ መስፈርት ለማሟላት ኦፌኮ በምርጫው አይሳተፍም የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡


ከዚህ ቀደም በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ ተጠይቀው ምላሽ የሰጡት የምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሀይሉ ምርጫ ለማድረግ አስቻይ ሁኔታ መኖሩን ጠቁመው አንዳንድ ሰላም የሌለባቸው አካባቢዎችም ምርጫው እስኪደርስ ሰላም ይሆናሉ የሚል እምነት እንዳላቸው መናገራቸው ይታወሳል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..


ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page