top of page

ግንቦት 21፣2016 - በሀገር አቀፍ በሚካሄደው የምክክር ጉባኤ 3,500 ተወካዮች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የምክክር ኮሚሽን ተናገረ

  • May 29, 2024
  • 1 min read

በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው የምክክር ጉባኤ 3,500 ተወካዮች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተናገረ፡፡

 

ለሀገራዊ ምክክሩ አጀንዳ ሆነው የሚቀርቡ ርዕሰ ጉዳዮችን የማሰባሰቡ ስራ ዛሬ በአዲስ አበባ መጀመሩ ይታወቃል፡፡

 

አጀንዳዎቹ በመጨረሻ ለሚደረገው የምክክር ጉባኤ 3,500 ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች እንደሚሳተፉ ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ(ዶ/ር) ለሸገር ተናግረዋል፡፡

 

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዛሬ በአዲስ አበባ በአደዋ ሙዚየም የመጀመሪያ ዙር የአጀንዳ ማሰባሰቢያ የምክክር ምዕራፍ እያካሄደ ይገኛል፡፡

 

ኮሚሽነር  ዮናስ አዳዬ(ዶ/ር) እየተካሄደ ካለው የምክክር ጉባኤ ሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ኮሚሽኑ ይጠብቃል ብለዋል፡፡

እነሱም አንጀንዳ የማሰባሰብ፣ በአጀንዳዎቹ ላይ ጥልቅ ውይይት ማካሄድ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው የምክክር ጉባኤ አዲስ አበባ ተወክለው የሚሳተፉ ተወካዮችን መምረጥ እንደሆነ ነግረውናል፡፡

 

ተሳታፊዎቹም አንዱ የሌላውን ሀሳብ የማክበር፣ የመደማመጥ እና ሀሳባቸውን በነፃነት የመግለፅ ይጠበቀባቸዋል፡፡

 

ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የመጀመሪያ ምዕራፍ የአጀንዳ ማሰባሰቢያ ምክክር በአዲስ አበባ የተጀመረ ሲሆን ለተከታታይ 7 ቀናት የሚካሄድ ነው፡፡

 

በዛሬው መድረክ ከአዲስ አበባ ከ 119 ወረዳዎች የተወከሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል፡፡

 

ያሬድ እንዳሻው

 

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

 

 

 

 
 
 

Recent Posts

See All
በኢትዮጵያ እያንዳንዱ ብሄረሰብ የራሱን ታሪክ ብቻ ለይቶና አጉልቶ የሚያቀርብበት ስርዐት መቀየር እንዳለበት የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ተናገሩ ።

ሐምሌ 23 2018 በኢትዮጵያ እያንዳንዱ ብሄረሰብ የራሱን ታሪክ ብቻ ለይቶና አጉልቶ የሚያቀርብበት ስርዐት መቀየር እንዳለበት የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ተናገሩ ። በኢትዮጵያ የብሄረሰቦች ታሪክ ጥልቅ ትስስር እና መስተጋብር ያለው ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የታሪክ ባለሞያዎች ማህበር ከላይፍ ኤንድ ፒስ ኢንስ

 
 
 
በ2018 በጀት ዓመት ከ1.2 ቢሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

ሐምሌ 23 2018 በ2018 በጀት ዓመት ከ1.2 ቢሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። በየዓመቱ በሀገሪቱ የሚገኘው የምርት መጠን እያደገ እንደሚመጣ ሪፖርቶች ያመልክታሉ። በገበያው ውስጥ ግን የምርት ዋጋ ከአመት አመት እየጨመረ እንጂ ሲቀንስም አይታይም። ይህ ለምን ሆነ? እውነትስ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page