top of page
የካቲት 2/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
የካቲት 2/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች #ጃፓን በጃፓን LDP መራሽ ገዢ የፖለቲካ ጥምረት አብዛኛውን የፓርላማ መቀመጫ አሸነፈ ተባለ፡፡ ጥምረቱ 465 መቀመጫዎች ባሉት የህዝብ ተወካዮቹ ምክር ቤት 352ቱን ማሸነፉን ቢቢሲ ፅፏል፡፡ LDP ብቻውን 316 መቀመጫዎችን ማሸነፉ እንደ ታላቅ የምርጫ ስኬቱ ተቆጥሮለታል፡፡ ይሄ የፓርላማ አብላጫነት ለአዲሲቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሳናኤ ታካይቺ ከፍተኛ አቅም ይፈጥርላቸዋል ተብሏል፡፡ ታካይቺ በአገሪቱ ታሪክ የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ናቸው፡፡ ከሳቸው ቀዳሚ የነበሩ ሁለት የLDP ጠቅላይ ሚኒስትሮች የፓርላማውን አብላጫነት አጥተው እንደነበር መረጃው አስታውሷል፡፡ #ሶማሊያ የሶማሊያ የፀጥታ ሀይሎች 8 የአልሸባብ ፅንፈኛ ቡድን ታጣቂዎችን ገደልን አሉ፡፡ 8ቱ የአልሸባብ ታጣቂዎች የተገደሉት በመካከለኛ ጁባ ግዛት ቡ
13 minutes ago


የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የፖሊሲ አውጪዎች የሚመክሩበት አህጉራዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነዉ ።
ጥር 29/2018 በበርካታ አፍሪካ ሀገራት የሚገኙ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የፖሊሲ አውጪዎች የሚመክሩበት PANAF (Pan-African Network for Artistic Freedom) አህጉራዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነዉ ። በሰላም ኢትዮጵያ (Selam Ethiopia) እና በአጋሮቹ አዘጋጅነት "ለመፍጠር ነፃነት በድጅታል እና በኢኮኖሚ መልክዓ ምድር ውስጥ ያሉ ሃይል ፣ተፅኖ እና እድሎች " በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ጉባኤ፣ የተለያዩ የፓናል ውይይቶች እንደሚቀርቡበት ተነግሯል። በተለያዩ ፖለቲካዊ ጫናዎች ምክንያት ስጋት ላይ የሚገኙ የጥበብ ባለሙያዎችን መብት መጠበቅ ፣የማህበራዊ ሚዲያ እና የዲጂታል መድረኮች መስፋፋትን ተከትሎ የሚመጡ አዳዲስ የሳንሱር አይነቶችን መከላከል፣የአፍሪካ መንግስታት ለኪነ-ጥበብ ዘ
3 days ago


በአማራ እና በትግራይ ክልል፤ ለትምህርት ዘርፍ ማጠናከሪያ የሚውል ወደ 10 ሚሊዮን ዶላር የተጠጋ በጀት የተያዘለት ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ፡፡
ጥር 29/2018 በአማራ እና በትግራይ ክልል፤ ለትምህርት ዘርፍ ማጠናከሪያ የሚውል ወደ 10 ሚሊዮን ዶላር የተጠጋ በጀት የተያዘለት ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ፡፡ ፕሌይፉል ኢዱኬሽን ፓዝዌይስ ኢን ኢትዮጵያ(PEPE) የተሰኘው ይህ ፕሮጅክት በአማራ እና ትግራይ ክልሎች ከትምህርት ውጪ ያሉና በግጭት የተጎዱ አካባቢዎች ውስጥ ከትምህርት ውጪ የሆኑ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ለመመለስ ታሳቢ ያደረገ ነው ተብሏል፡፡ የማጠናከሪያ ፕሮግራሙ በኢንተርናሽናል ሬስኪው ኮሚቴ (IRC) መሪነት፣ ከሉሚኖስ ፈንድ(Luminos Fund)፣ ኢማኑኤል ደቨሎፕመንት አሶሴሽን(EDA) እና ከሌሎች ባለድርሻ ተቋማት ጋር በመተባበር ይተገበራል ተብሏል። ለዚህ ስራ 9,980,000 ዶላር እንደተያዘለትም ሰምተናል፡፡ የPEPE ፕሮግራም የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ዬዲት ፀጋዬ፤ ስራው በ3 ዓመት
3 days ago


የተሰጠው የስራ ጊዜ ሲጠናቀቅ 2 ሳምንት የቀረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል አለ፡፡
ጥር 29/2018 የተሰጠው የስራ ጊዜ ሲጠናቀቅ 2 ሳምንት የቀረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል አለ፡፡ የካቲት 14 ቀን 2018 ዓ.ም የተሰጠው ጊዜ ገደብ የሚጠናቀቀው የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን "የጀመርኩት ስራ ተንጠልጥሎ እንዳይቀር " ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል ብሏል። መሰረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ተነጋግሮ መፍትሄ ለመስጠት በ2014 ዓ.ም እና አላግባብ ብለው በቆዩ ሃገራዊ የተቋቋመው የምክክር ኮሚሽን መጀመሪያ የተሰጠው የጊዜ ገደብ 3 ዓመት ነበር። በሰላም እጦት፣ በፖለቲካ አለመረጋጋት እና በተለያዩ ምክንያቶች በተሰጠው 3 ዓመት ተልዕኮውን ማጠናቀቅ ባለመቻሉ የህዝብ እንዳራሴዎች ምክር ቤት የካቲት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው አስቸኳይ ሰብሰባ ነበር የኮሚሽኑን የስራ ዘመን በአንድ ዓመት ያራዘመው። ኮሚሽኑም በተሰጠው
3 days ago


የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ የፋይናንስ ተቋም ኪሳራ ላይ ሲወድቅ ለገንዘብ አስቀማጮች የሚከፍለውን ኢንሹራንስ ከፍ ለማድረግ እያሰበበት እንደሚገኝ ተናገረ፡፡
ጥር 29/2018 የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ የፋይናንስ ተቋም ኪሳራ ላይ ሲወድቅ ለገንዘብ አስቀማጮች የሚከፍለውን ኢንሹራንስ ከመቶ ሺህ ብር ከፍ ለማድረግ እያሰበበት እንደሚገኝ ተናገረ፡፡ አሁን ላይ ኪሳራ ለደረሰበት አንድ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ገንዘብ አስቀማጮች ኢንሹራንስ እየከፈልኩ እገኛለሁም ብሏል፡፡ የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ በባንኮች እና በማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ገንዘብ ላስቀመጡ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ፤ የኢንሹራንስ ሽፋን በመስጠት ለገንዘብ አስቀማጮች ጥበቃ ለማድረግ የተቋቋመ ነው። ከተቋቋመ ወደ ሶስት ዓመት እየተጠጋ ሲሆን በዚህ ጊዜ ውስጥ በአጠቃላይ ከአባል ፋይናንስ ተቋማት የሰበሰበው አረቦን 17 ነጥብ 80 ቢሊየን ብር መድረሱን ሠምተናል። እስከ አሁን ከተሰበሰበው አጠቃላይ አረቦን ውስ
3 days ago


በደቡብ ምስራቅ እስያ ይሰሩ የነበሩ ባለሃብቶች በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የታሪፍ ተጽዕኖ ምክንያት መዳረሻቸውን ኢትዮጵያ እያደረጉ ነው ተባለ።
ጥር 29/2018 በደቡብ ምስራቅ እስያ ይሰሩ የነበሩ ባለሃብቶች በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የታሪፍ ተጽዕኖ ምክንያት መዳረሻቸውን ኢትዮጵያ እያደረጉ ነው ተባለ። ኢትዮጵያም ዕድሉን በመጠቀም በተለይ ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ተጨማሪ ባለሃብቶችን ከአካባቢው ሀገራት ለመሳብ ጠንክራ እየሰራች እንደምትገኝ ተነግሯል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢትዮጵያን ጨምሮ አንድ መቶ በሚደርሱና ምርቶቻችውን ወደ አሜሪካ በሚልኩ ሀገራት ላይ ታሪፍ መጣላቸው ይታወሳል። ትራምፕ ከ10 በመቶ እስከ 54 በመቶ የሚደርስ ታሪፍ ነው በሀገራቱ ላይ የጣሉት። አስር በመቶ ታሪፍ ከተጣለባቸው ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ ፤ ኬንያ፣ ኤርትራ፣ ጅቡቲ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ይገኙባቸዋል። የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት የሆኑ
3 days ago


በ2018 በጀት ዓመት በመንፈቅ ጊዜ 52.26 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ።
ጥር 29/2018 በ2018 በጀት ዓመት በመንፈቅ ጊዜ 52.26 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ። አጠቃላይ ወጪው ደግሞ 52.02 ቢሊዮን ብር መሆኑን አንስቷል። አገልግሎቱ ከኢነርጂ ሽያጭ፣ ከአዲስ ደንበኛ መስተንግዶ፣ ከማያገለገሉ ንብረቶች ሽያጭና ከልዩ ልዩ ገቢ በጠቅላላው 54.23 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ሲሰራ እንደነበር ተነግሯል። የተቋሙ የሰበሰበው ገቢ ከእቅዱ 96 በመቶ ያሳካ ነው ተብሏል፡፡ አገልግሎቱ ይህንን ያለው የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት አፈፃፀሙን በተመለከተ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው። በመጀመሪያ ስድስት ወራት ከኢነርጂ ሽያጭ 34.34 ቢሊዮን ብር፣ ከአዲስ ደንበኞች መስተንግዶ 16.7 ቢሊዮን ብር፣ እንዲሁም የማያገለግሉ ንብረቶችን በማስወገድና ከልዩ ልዩ ገቢ 1.2 ቢሊዮን
3 days ago


ከመንግስትጋር እርቅ አድርጎ ወደ ሰላማዊ ትግል የገባው አፋሕድ አጀንዳ ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረከበ።
ጥር 28/2018 በኢትዮጵያ ገለልተኛ በሆነ ተቋም የህዝብ ቆጠራ እንዲካሄድ እና የአማራ ክልል ተወላጆችም በሚኖርበት ክልል የፖለቲካ ውክልና እንዲኖራቸው ከመንግስትጋር እርቅ አድርጎ ወደ ሰላማዊ ትግል የገባው አፋሕድ አጀንዳ አድርጎ ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረከበ። የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዛሬ ከድርጅቱ አመራሮች እና ተወካይዎች ጋር ተወያይቶ አጀንዳዎችን ተረክቧል። ደርጅቱ መሳሪያ አንስቶ ወደ ጨካ ለመግባት ምክንያት ሆነውኝ ነበር ያላቸውን በ17 ከፍል የተደራጁ አጀንዳዎቹን ለምክክር ኮሚሽን ዛሬ ከሰዓት በኋላ ማስረከቡን የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አቶ ኢያሱ አባተ ነግረዉናል። አቶ እያሱ የአማራ ክልል ህዝብ መፈናቀል ፣መሰደድ ፣ወሰን አለመከበር እና የማንንት ጥያቄዎች አለመመለስ ጫካ
4 days ago


በቂ የነዳጅ ምርት ቢኖርም የነዳጅ አቅራቢዎች በየቀኑ ወደ አዲስ አበባ መግባት ያለበትን መጠን እያስገቡ አይደለም ተብሏል።
ጥር 28/2018 በአሁኑ ወቅት በቂ የነዳጅ ምርት ቢኖርም የነዳጅ አቅራቢዎች በየቀኑ ወደ አዲስ አበባ መግባት ያለበትን መጠን እያስገቡ አይደለም ተብሏል። በዚህም ምክንያት ከሰሞኑ ነዳጅ ለመቅዳት በማዲያዎች የሚደረጉ ረጃጅም ሰልፎች ተስተውለዋል ያለን የዘርፉን ግብይት የሚቆጣጠረው የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ነው። በከተማዋ ባሉ 125ቱም ማደያዎች ምን ያህል ነዳጅ በየትኛው ማደያ አለ የሚለውን እለታዊ መረጃ በማሰራጨት ቁጥጥር የሚያደርገው ቢሮው በቂ ነዳጅ አለ ለማለት በቀን ከ2.8 ሚሊዮን ሊትር በላይ ናፍጣ፣ ቤንዚን 2 ሚሊዮን ሊትር መኖር አለበት፤ አሁን ያለው 2.5 ሚሊዮን ሊትር ናፍጣ ነው ፤ ለዚህ ነው በየቦታው ሰልፍ የበዛው ሲሉ በቢሮው የንግድ ኢንስፔክሽንና ሬጉላቶሪ ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ አሰፋ አስረድተዋል። የወሩ መጨረሻ ሲቃረብ ሆን ብለው
4 days ago



Facebook
Twitter
Pinterest
Tumblr
Copy Link
Link Copied
Search video...

Now Playing
የፖለቲካ ፓርቲዎች ስለ ሰባተኛው ምርጫ ምን ይላሉ? - 547
33:06

Now Playing
የህክምና ስህተት ፈጽመዋል የተባሉ 21 የህክምና ባለሙያዎች
06:10

Now Playing
Sheger Tintane አዲሱ የትራምፕ የሰላም ቦርድ !@ShegerFM1021Radio
06:40

Now Playing
ከእኔ በላይ ዋሌት ቦርሳ የሚሰራ ካለ አስይዛለሁ / ከወጣት ዑመር ዱሪ ጋር ያደረግነው ቆይታ!
32:02

Now Playing
በሸገር ከተማ መልካ ኖኖ ክፍለ-ከተማ እናጣራለን!@ShegerFM1021Radio
20:15

Now Playing
ኃያላን ሀገሮች የሀገራቸውን ማዕድን ጨርሰው ወደ አፍሪካ እየገቡ ነው፤ ኢትዮጵያስ?
05:17

Now Playing
የሂትለር ናዚ ፓርቲ ፣የመረረ ስቃይና ግፍ የፈፀመበት የአሸዋትዝ ማጎሪያ ካምፕ በሶቪየት ሕብረት ወታደሮች ነፃ የሆነው ፣ በ1937 ዓ.ም በዛሬው ቀን ነበር
02:36

Now Playing
ብሔራዊ ባንክ፤ ባንኮች ለተመረጡ የገቢ ዕቃዎች የጉምሩክ ዋጋን እንደ አመላካች ዋጋ እንዲጠቀሙ ለምን ወሰነ ?
06:00
bottom of page








