top of page
በ2018 ወደ ውጪ ከተላከ ቡና 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን የግብርና ሚ/ር ተናገረ፡፡
ሰኔ 25/2018 በ2018 በጀት ዓመት ወደ ውጪ ከተላከ ቡና 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር ተናገረ፡፡ በጀት ዓመቱ ከቡና ወጪ ንግድ 3 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ለማግኘት የተያዘው ዕቅድ ማሳካቱን ሚኒስቴር መ/ቤቱ አስረድቷል፡፡ በባለፈው በጀት ዓመት ከቡና ወጪ ንግድ 2.65 ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን ሚኒስቴር መ/ቤቱ አስታውሷል፡፡ መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት የቡናውን ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስራዎች እየተሰሩ ነው ያለው የግብርና ሚኒስቴር በዚህም ለውጥ መጥቷል ሲል አስረድቷል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ላይ 5.8 ሚሊዮን ገበሬ በቡና አምራችነት ተሰማርቶ የሚገኝ ሲሆን ገበሬው ከሰራው ስራ ወደ ኪሱ የተጣራ ገቢ የሚያገኘው 40 ከመቶውን ብቻ መባሉ ይታወሳል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….. በረከት አካሉ
2 hours ago


የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት በየጊዜው ገበያው በሚፈልገው ልክ እያጠኑ የሚሰጡትን ስልጠና እንደማይከልሱ ጥናት አሳየ፡፡
ሰኔ 25/2018 የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት በየጊዜው ገበያው በሚፈልገው ልክ እያጠኑ የሚሰጡትን ስልጠና እንደማይከልሱ ጥናት አሳየ፡፡ ሰልጣኞቻቸው የወሰዱትን ስልጠና እንዴት ወደ ቢዝነስ መለወጥ እንዳለባቸው የሚያስችል ጥራት ያለው ስልጠና የማይሰጡም አሉ ተብሏል፡፡ አቶ ሀብታሙ አለማየሁ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የመንግስት ቴክኒክና ሞያ ማሰልጠኛ ተቋማት ውስጥ ያለው የስልጠና አካሄድን በተመለከተ ጥናት አድርገዋል፡፡ በዚህ ጥናታቸው 14 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ያሉ የቴክኒክና ሞያ ስልጠና ተቋማትን የተመለከቱ ሲሆን በተቋማቱ ውስጥ ወጥ የሆነ አሰራር እየተተገበረ አይደለም ይላሉ፡፡ አንዳንድ ማሰልጠኛ ተቋማት የሚሰጡት ስልጠና ወቅቱ በምን መንገድ ይፈልገዋል የሚለውን በትክክል አያጠኑም ሲሉም የስረዳሉ፡፡ ይህ ዘርፍ በየጊዜው የሚሰጡ ስ
3 hours ago


ተሻሽሎ ስራ ላይ መዋል ከጀመረ አንድ ዓመት ያስቆጠረው የፌዴራል ገቢ ግብር አዋጅ ነባራዊ ሁኔታዎችን ያላገናዘቡ አንዳንድ ጥብቅ ድንጋጌዎች ያሉበት ነው ተባለ።
ሰኔ 25/2018 ተሻሽሎ ስራ ላይ መዋል ከጀመረ አንድ ዓመት ያስቆጠረው የፌዴራል ገቢ ግብር አዋጅ ነባራዊ ሁኔታዎችን ያላገናዘቡ አንዳንድ ጥብቅ ድንጋጌዎች ያሉበት ነው ተባለ። ድርጅቶች ቢከስሩ እንኳን ከዓመታዊ ሽያጫቸው 2.5 በመቶ ግብር መክፈል አለባቸው የሚለው አንዱ ድንጋጌ መሆኑ ተጠቅሷል። የድንጋጌው መነሻ ነጋዴዎች እያተረፉም ጭምር ከስረናል በሚል ያሳውቃሉ ከሚል እንደሆነ ተነግሯል። በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል በሚካሄደው ውይይት ድንጋጌው በግሉ ዘርፍ ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ እንደሚገኝ ትኩረቱን በታክስ ዙርያ አድርጎ ተነስቷል። በተለይ ከፍተኛ ሽያጭ ያላቸው ግን ደግሞ የትርፍ ህዳጋቸው አነስተኛ የሆኑ እንደ ማኑፋክቸሪንግ እና ጅምላ ንግድ ያሉ ዘርፎች እየተጎዱ ነው። በአንድ የግብይት ወቅት ከ50 ሺህ ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ የተከፈለን ወጪ ከታክስ
5 hours ago


በዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ ከ4,000 በላይ ተወካዮች በመጪው ሳምንት አዲስ አበባ ይገባሉ ተባለ።
ሰኔ 25/2018 በዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ ከ4,000 በላይ ተወካዮች በመጪው ሳምንት አዲስ አበባ ይገባሉ ተባለ። ተወካዮች ከትግራይ ክልል ውጪ ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የተወከሉ እና የተለያዩ የማህበረሰብ ከፍሎችን የወከሉ ናቸው። በምክክሩ ወቅት 4ሺዎች ጉባዔተኞች በስምንት ቡድን ተከፋፍለው ይመክራሉ ሲሉ የተናገሩት ምክትል ኮሚሽነር ሂሩት ገብረስላሴ ናቸው። በእያንዳንዱ ቡድን 500 ጉባኤተኞች ይካተታሉ ተብሏል፡፡ ምክትል ኮሚሽነር ሂሩት ገብረ ስላሴ ይህን የተናገሩት ሐምሌ 8 ቀን 2018 በሚጀመረው ዋናው የምክክር ጉባኤ ወቅት ሙያዊ ማብራሪያ ከሚያቀርቡ ( Panel of experts) ጋር በስካይ ላይት ሆቴል ውይይት ሲደረግ ነው:: በምክክር ወቅት ሞያዊ ማብራሪያ የሚቀርበው ቡድን ከተለያዩ የትምህርት ተቋማት እና የሞያ ዘር
5 hours ago


በኢትዮጵያ በተለያዩ የትምህርት ተቋማት እንደሚደረጉ ጥናትና ምርምሮች
ሰኔ 23 2018 በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ14,000 በላይ ጥናቶች እና ምርምሮች በተለያዩ የትምህርት ተቋማት እንደሚደረጉ ይነገራል። ከእነዚህ ጥናቶችና ምርምሮች ስራ ላይ ውለው የህብረተሰቡን ችግር ለመፍታት እያገዙ ያሉት ግን ጥቂቶቹ ናቸው ተብሏል። ጥናቶቹ የህብረተሰቡን ችግር መነሻ አድርገው አለመካሄዳቸው እና በጋራ መድረክ አለመገምገማቸው የችግሩ መነሻ እንደሆነ ተጠቅሷል። በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የሚገጥሙ ችግሮችን ለመፍታት በተማሪዎች እና በምሁራን እንዲሁም በተመራማሪዎች የሚደረጉ ጥናትና ምርምሮች በአንድ መድረክ ቀርበው ውይይት ቢደረግባቸው መፍትሄ ያመጣሉ ተብሏል። ይህ የተባለው ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ባካሄደው 18ተኛው የዘርፈ ብዙ ጥናት እና ምርምር ጉባኤ ላይ ነው። በጉባኤው በተለያዩ ዘርፎች ማለትም በቢዝነስ እና ኢንድስትሪ በፋይናስ በግብ
1 day ago


በኢትዮጵያ የጭነት ማስተላለፍ ስራ ለውጭ ባለሃብቶች ሙሉ በሙሉ ክፍት እንዲሆን ተወስኗል።
ሰኔ 24/2018 በኢትዮጵያ የጭነት ማስተላለፍ ስራ ለውጭ ባለሃብቶች ሙሉ በሙሉ ክፍት እንዲሆን ተወስኗል። ከዚህ ቀደም የውጭ ኩባንያዎች ከ49 በመቶ ያልበለጠ ድርሻ ይዘው ከአገር ውስጥ ባለሃብቶች ጋር በጥምረት እንዲሰሩ ነበር የሚፈቀድላቸው። ገደቡ የሎጂስቲከስ ዘርፉ የሚፈለገው ያህል የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ እንቅፋት ሆኖ መቆየቱን ፤ውሳኔውን ይፋ ያደረገው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ አመልክቷል። ዝርዝር የህግ ማዕቀፎችን የማጠናቀቅ ስራ በሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት በኩል እየተከወነ እንደሚገኝም ጠቅሷል። የኢትዮጵያ የሎጅስቲክስ አገልግሎት አሰጣጥ ዝቅተኛ እንደሆነ በየጊዜው የሚወጡ የአለም ባነክ ሪፖርቶች ያሳያሉ የሚሉት ፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሎጂስቲክስ እና የንግድ ሠንሠለት ማኔጅመንት ክፍል መምህር ፕሮ
1 day ago


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚያስተዳድራቸው መ/ቤቶች የተገኘባቸውን የኦዲት ከፍተቶች በ10 የስራ ቀናት ውስጥ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወስዱ የሚያስገድድ መመሪያ ወጣ፡፡
ሰኔ 24/2018 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚያስተዳድራቸው መስሪያ ቤቶች የተገኘባቸውን የኦዲት ከፍተቶች በ10 የስራ ቀናት ውስጥ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወስዱ የሚያስገድድ መመሪያ ወጣ፡፡ የኦዲት መረጃዎችን ማየት የፈለገ ማንኛውም አካል ደግሞ የኦዲት አድራጊ መስሪያ ቤቶችን ኃላፊዎች ፍቃድ ማግኘት ግዴታ አለበት ይላል መመሪያው፡፡ የመንግስት ንብረት ኦዲት መመሪያ ቁጥር190/2018 ኦዲት ተደራጊ መስሪያ ቤት ሥራ አመራርና የህንፃና ንብረት ሰራተኞች ኃላፊነታቸውን በብቃት መወጣታቸውን ለመረዳት ያስችላል ተብሏል፡፡ በተጨማሪም ንብረቶች ለታለመላቸው ዓላማ መዋላቸውን እና በስራ ላይ ባለ የህንፃና ንብረት አስተዳደር ሕጎች መሠረት ሥራዎች መከናወናቸውን ማረጋገጥ እና በኦዲት ግኝቱ መሠረት ኦዲት ተደራጊ መሥሪያ ቤቶች የእርምት እርምጃ መውሰዳቸውን መ
1 day ago


በኢትዮጵያ ሰዎች የጤና እክል ሲገጥማቸው የተሻለ ህክምናም ሲያስፈልጋቸው ምን ማድረጋቸው ይጠበቅባቸዋል ?
የሰኔ 24/2018 ሰው ጤናው ሲጓደል ለፈውስም መፍትሄ ሲፈልግ መካሪው ብዙ ሆኖ ይታያል፡፡ ሰዎች አንዳች የጤና ክልል ሲገጥማቸው፣ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ሐሳብ ሲገባቸው የሚያግዛቸውን ፣ የተሻለ ህክምና አገልግሎትም ሲያሻቸው የሚጠቁማቸውንና የሚያማክራቸውን የጤና ማማከር አገልግሎትን ምርጫቸው ማድረግ በተለይ በውጩው አለም የተለመደ ነው ይባላል። ለመሆኑ በኢትዮጵያ ሰዎች የጤና እክል ሲገጥማቸው የተሻለ ህክምናም ሲያስፈልጋቸው ምን ማድረጋቸው ይጠበቅባቸዋል ? የጌትዌል ሜዲካል ትራቭል መስራች እና ስራ አስኪያጅ የሆኑትን ዶ/ር በጋሻው ባይለየኝን ጠይቀናል። ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….. ፍቅሩ አምባቸው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at
1 day ago


ለሴቶችና ወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር ኑሯቸውን ለማሻሻል ሲተገበር የቆየው የሊዌ ፕሮጀክት የስራ ፈጣሪዎችን አቅም አሻሽሎታል ተባለ፡፡
የሰኔ 24/2018 ለሴቶችና ወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር ኑሯቸውን ለማሻሻል በኔዘርላንድስ የልማት ድርጅት ድጋፍ ሲተገበር የቆየው የሊዌ ፕሮጀክት የስራ ፈጣሪዎችን አቅም አሻሽሎታል ተባለ፡፡ የኔዘርላንድስ የልማት ድርጅት (SNV) ከመርሲ ኮርፕስ (Mercy Corps) ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ከተማ ሲተገብር የቆየው የሴቶች እና ወጣቶች የኑሮ ማሻሻያ (LIWAY) ፕሮግራም ተመዝግበዋል የተባሉ ለውጦችን የታዩበት ዝግጅት በትናንትናው እለት ተካሂዷል፡፡ ፕሮጀክቱ ለስራ ፈጣሪዎች ማስያዣ ሳይጠየቁ ከባነኮች ብድር የሚያገኙበትን ሁኔታ ፈጥሯል አንዲሁም መቀጠር ለሚፍሉጉ ድግሞ የቅም ግንባታ ስልጠና እንዲያገኙ ተድረጓል ሲሉ የፕሮጀክቱ ሃላፊ ሄለን ጌታቸው አስረድተዋል፡፡ በዚህም ላለፉት 4 ዓመታት 402,000 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ወጣቶችና ሴቶችን የራሳቸው
1 day ago



Facebook
Twitter
Pinterest
Tumblr
Copy Link
Link Copied
Search video...

Now Playing
Mekoya - ሱዳናዊው ሰላይ በኢትዮጵያ ላይ - በእሸቴ አሰፋ
28:44

Now Playing
ለመሆኑ በአንድ በግዙፍ ድርጅት አስተዳደር ምን መሳይ መልክ ሊኖረው ይገባል? #economy #business #finance
07:59

Now Playing
አልሰማንም እንዳትሉ - ከባል አካውንት ለአባት የተላለፈው 400 ሺህ ብር የማን ነው?
04:12

Now Playing
የአሜሪካና ኢራን አዲሱ ውዝግብ - ሰኔ 17/2018 @ShegerFM1021Radio #shegerfm #iranamericawar
07:15

Now Playing
እንደ ቤተሰብ - ዛሬም በኢትዮጵያ 40 ሺህ ህፃናት ከዚህ ችግር ጋር ይወለዳሉ'
57:31

Now Playing
በሳውዲ አረቢያ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ/ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
04:54

Now Playing
አልሰማንም እንዳትሉ - የፖለቲካ ሹም ሽር በፍርድ ቤት ይዳኛልን?
04:21

Now Playing
አሜሪካ ጫፌን የምትነካ ከሆነ ኬብሎቹን ቆርጬ የኢንተርኔት ስርዓቱን አስተጓጉላለው #shegerfm #iranisraelwar
07:32
bottom of page

