top of page
ኢትዮዽያ በአለም የሎጅስቲክስ ሜዳ
የካቲት 27/2018 የሎጅስቲክስ ስራ ፍፁም የሰላም መስመር እና እውቀት ይፈልጋል፡፡ ሎጅስቲክስ በኢትዮጵያ እንዲዘምን፣ እንዲቀላጠፍ አሁንም ብርቱ ስራ ይጠይቃል። እቃዎችን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ለማንቀሳቀስ፣ መያዝ፣ ማከማቸት እና ማስተናገድ ፤ በየትኛውም የአለም መሮጫ ኮሪደር እና ባህር ማገላበጥ ፤ በአየር በየብስ ምድር ለመላወስ ጥንቅቅ ያለ የሎጅስቲክስ ስራ ይፈልጋል። ለዚህ ደግሞ በየጊዜው በአለም በሚደረጉ ጉባኤዎች እና የሎጅስቲክስ ማህበራት ላይ በኃላፊነት ቦታ መገኘት እንደሚያስፈልግ ይታመናል። በተለይ ከአፍሪካ ብቸኛው የአለም ፍሬይት ፎርዋርደርስ ማህበር ፊያታ የቦርድ አባል እና በ ኢትዮጵያም የማህበሩ ፕሬዝዳንት አቶ ዳዊት ውብሸት በዚህ ጉዳይ ስጋት እንዳላቸው ነግረውናል። ኢትዮዽያ በአለም የሎጅስቲክስ ሜዳ ፤ በጭነት መርከቦች እና አጠቃላ
2 days ago


ደንበኞች ባሉበት ሆነው የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም ብቻ የቆጣሪ ንባባቸውን የሚያስገቡበት አሰራር በሙከራ ደረጃ መጀመሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አግልግሎት ተናገረ፡፡
የካቲት 27/2018 ደንበኞች ባሉበት ሆነው የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም ብቻ የቆጣሪ ንባባቸውን የሚያስገቡበት አሰራር በሙከራ ደረጃ መጀመሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አግልግሎት ተናገረ፡፡ ይህም በተደጋጋሚ ከደንበኞች የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት ይረዳኛል ብሏል። የሙከራ ትግበራው ከ16 ሺህ በላይ የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች ባሉበት የሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን መጀመሩን የተቋሙ የኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ አንዋር አብራር ነግረውናል ፡፡ ሥራ አስፈፃሚው የዲጂታል አሰራሩ ለደንበኞች በቀላሉ ተደራሽ ለመሆን፣ የፍጆታ ሂሳብን በወቅቱ ለመፈጸም፣ ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት እንዲሁም ጊዜና ወጪን ለመቆጠብ ያስችላል ብለውናል፡፡ በዚህም ከየካቲት 13 ቀን እስከ የካቲት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ደንበኞች የፍጆታ ንባባቸውን በቀላሉ በቤታቸው ሆነው ለዚሁ አ
2 days ago


የባቱ - አርሲ ነገሌ 57 ኪሎ ሜትር የፍጥነት መንገድ ግንባታ ዋና ዋና ሥራዎቹ ተጠናቅቀዋል ተባለ።
የካቲት 26/2018 የሞጆ - ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ አካል የሆነው የባቱ - አርሲ ነገሌ 57 ኪሎ ሜትር የፍጥነት መንገድ ግንባታ ዋና ዋና ሥራዎቹ ተጠናቅቀዋል ተባለ። የመንገድ ኮሪደሩ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ እና ምዕራብ አርሲ ዞኖች የሚገኙትን የባቱ ከተማን፣ የአዳሚ ቱሉ እና አርሲ ነገሌ ወረዳዎችን ጨምሮ ከ17 በላይ ቀበሌዎችን ያስተሳስራል ተብሏል። የመንገድ ግንባታው የአዲስ አበባ - ሞያሌ - ናይሮቢ - ሞምባሳ የመንገድ ኮሪደር አካል መሆኑ ተነግሯል። ግንባታውን ለማከናወን ከዓለም ባንክ የተገኘ 5.3 ቢሊዮን ብር ወጪ መሆኑ ተነግሯል። 57 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የባቱ - አርሲ ነገሌ የፍጥነት መንገድ ግንባታ በ90 ሜትር የመንገድ ወሰን ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፤ የጎን ስፋቱ የመንገድ አካፋይን ጨምሮ 31.6 ሜትር መሆኑን የኢትዮጵያ መን
3 days ago


በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት ዓመታት በነበሩ ግጭቶች ከ300 በላይ ትምህርት ቤቶች ተዘግተው እንደነበር ተነግሯል።
የካቲት 26/2018 በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት ዓመታት በነበሩ ግጭቶች ከ300 በላይ ትምህርት ቤቶች ተዘግተው እንደነበር ተነግሯል። ይህም የክልሉን አጠቃላይ 20 በመቶ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ማራቁን የክልሉ ምክትል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በሽር አብዱረሂም ተናግረዋል። አሁን ላይ ግን በክልሉ በተሰሩ ስራዎች በአብዛኛው በሚባል ደረጃ ትምህርት ቤቶች ወደ መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደታቸው መመለሳቸውን ኃላፊው አንስተዋል። ኃላፊው ይህንን ያሉት ኩሶ ኢንተርናሽናል የተባለ የተራድኦ ተቋም በክልሉ ባለፉት 6 ዓመታት ሴት ተማሪዎችን ለዩንቨርሲቲ የማብቃት ፕሮጀክት (U_Girls project) የማጠቃለያ መድረክ ላይ ነው። የትምህርት ቢሮ ኃላፊው በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመማር ማስተማር ችግሮችን በመፍታት ሂደት ውስጥ የኩሶ ኢንተርናሽናልን
3 days ago


ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ለመደገፍ የሚያስችል ሁለተኛ ዙር ፕሮጀክት ወደ ስራ መግባቱ ተነገረ፡፡
የካቲት 26/2018 በተለያዩ አካባቢዎች ባለ የሰላም እጦት እና የሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ለመደገፍ የሚያስችል ሁለተኛ ዙር ፕሮጀክት ወደ ስራ መግባቱ ተነገረ፡፡ በአለም ባንክ የሚደገፈው እና ለ5 ዓመታት ይቆያል የተባለው ይህ ፕሮጀክት ሊጠናቀቅ 2 ዓመታት እንደቀረው ሲነገር ሰምተናል፡፡ በዚህም ሁለተኛው ምዕራፍ እና በሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ይተገበራል የተባለው ስራ ወደ ትግበራ መግባቱ ተነግሯል፡፡ በጦርነት ምክንያት ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች የጤና ድጋፍ እንዲያገኙ፣ የኢኮኖሚ ምስቅልቅል የገጠማቸው ወደ ቀድሞ ስራቸው እንዲመለሱ እና ሌሎች ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮቻቸው ላይ የሚሰራ ፕሮጀክት መሆኑ ተነግሮለታል፡፡ ፕሮጀክቱም በ5 ክልሎች የሚተገበር ሲሆን አማራ፣ ትግራይ፣ ኦሮሚያ፣ አፋር፣ ቤኒሻን
3 days ago


ከጎርጎርሳውያኑ ከ2024 ጀምሮ ኢትዮጵያ የውጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ከአፍሪካ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች ተብሏል።
የካቲት 26/2018 ከጎርጎርሳውያኑ ከ2024 ጀምሮ ኢትዮጵያ የውጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ከአፍሪካ ሁለተኛ ፤ ከምስራቅ አፍሪካ ደግሞ አንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች ተብሏል። በቀጣይ ወር በአዲስ አበባ በሚዘጋጀው የኢንቨስትመንት ፎረም ላይ ብቻ ከ2.4 ቢሊየን ዶላር በላይ ግምት ያለው የኢንቨስትመንት ስምምነት ይፈረማል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተነግሯል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እና የገንዘብ ሚኒስቴር ፎረሙን አስመልክተው ትናንት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት እና ሌሎች ዘርፎችን የሚደግፉ ከ123 በላይ አዳዲስ ህጎችን ባለፉት ሰባት ዓመታት አውጥታለች ተብሏል። ማሻሻያ የተደረገባቸው ህጎች ከተጨመሩበት ደግሞ ቁጥሩ ከ198 እንደሚልቅ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ዶክተር ዘለቀ ተመስገን ተናግረዋል።
3 days ago


አዋሽ ባንክ ለ7 ግብረ ሰናይ ድርጅቶች 25 ሚሊዮን ብር ሰጠ።
የካቲት 26/2018 አዋሽ ባንክ ለ7 ግብረ ሰናይ ድርጅቶች 25 ሚሊዮን ብር ሰጠ። ባንኩ ለግብረ ሰናይ ድርጅቶቹ ድጋፉን ያደረገው ያለንበትን የረመዳን ወርን ምክንት በማድረግ ነው። 25 ሚሊዮን ብር ድጋፍ የተደረገላቸው ድርጅቶችም ህጻናትን፣ በአረጋዊያንን እና አካል ጉዳተኞችን በመደገፍና በመንከባከብ ላይ የተሰማሩ መሆናቸው ተጠቅሷል። ወንድም ካሊድ ፋውንዴሽን፣ የስራ ለና የበጎ አድርጎ ድርጅት፣ ተስፋ አዲስ ፓረንትስ ቻይልድሁድ ሰፖርት ኦረጋናይዜሽን፣ ዘ ችልድረንስ ኸርት ፈንድ ኦፍ ኢትዮጵ፣ እዝነት አካል ጉዳተኛ ህፃናትና ወላጆች መርጃ ድርጅት እና አብደላ ኢብኑ ኡሚ መክቱም ቁራን ማህበር ናቸው ድጋፉ የተደረገላቸው። አዋሽ ባንክ የ1447ኛውን የረመዳን ወር ምክንያት በማድረግ ትናንት ምሽት በሸራተን አዲስ ሆቴል ባዘጋጀው የኢፍጣር መርሃ-ግብር ላ
3 days ago


አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ በውስጡ ምን ይዟል?
የካቲት 25/2018 የሚኒስትሮች ምክር ቤት 53ተኛ ስብሰባውን ባደረገበት ወቅት በቱሪዝም ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ውይይት አድርጎ በምክር ቤቱ ከፀደቀበት ቀን ጀምሮ ወደ ስራ እንዲገባ ፈቃድ ሰጥቷል፡፡ ኢትዮጵያ የቱሪዝም ፖሊሲዋን ለመጨረሻ ጊዜ ያሻሻለችው በ2001 ዓ.ም ነበር፡፡ ታዲያ አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ በውስጡ ምን ይዟል? ስንል በፖሊሲ ማርቀቁ ላይ የተሳተፉትን አቶ ኤንዲ አሰፋን ጠይቀናቸዋል፡፡ የቱሪዝም ባለሙያው አቶ ኤንዲ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ወደ ስራ እንዲገባ የተፈቀደው አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ በዘርፉ ከዚህ ቀደም ይነሱ ለነበሩ ችግሮች ምላሽ ይዞ መጥቷል ይላሉ፡፡ ከዚህ ቀደም ቱሪዝም መሰረተ ልማትን በተመለከተ በፖሊሲ ደረጃ የተቀመጠ ነገር አልነበረም አዲሱ ፖሊሲ በዚህ ዙሪያ ምላሽ አለው በዘርፉ የተማሩ ባለሙያዎችም እንዴት መሰማራት እንዳለባቸው
4 days ago


አሁን ላይ ሁሉም ክልሎች ከፌዴራሉ ጋር ተመሳሳይ ይዘት ያለው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ አዘጋጅተው ጨርሰዋል ተባለ
የካቲት 25/2018 አሁን ላይ ሁሉም ክልሎች ከፌዴራሉ ጋር ተመሳሳይ ይዘት ያለው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ አዘጋጅተው ጨርሰዋል ተባለ። በተለያየ ምክንያት አዋጁን የማዘጋጀቱ ስራ በክልሎች ተጓቶ እንደቆየ የፌዴራል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ተናግሯል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ በፌዴራል ደረጃ መሻሻሉን ተከትሎ ክልሎችም ተመሳሳይ ማዕቀፍ ያለው ህግ ማዘጋጀት እንዳለባቸው ተጠቅሶ በዚሁ ላይ ሲሰራ መቆየቱ ተነግሯል። ክልሎች ተመሳሳይ ይዘት ያለው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ማውጣት አለባቸው የተባለው የፌዴራሉ አዋጅ ተፈጻሚነት በፌዴራል በሚመዘገቡት ላይ ብቻ ስለሆነ ነው ተብሏል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ እንዳሉት የውጪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ወ
4 days ago



Facebook
Twitter
Pinterest
Tumblr
Copy Link
Link Copied
Search video...

Now Playing
የእጅጋየው ሽባባው ሰርክ ገዝፎ የሚንጥ ዕሩቅ ግን ቅርብ ወብ ስሜት አድዋ // ሸገር ሼልፍ
16:11

Now Playing
በትግራይ ክልል አዲስ በተፈጠው ውጥረት ምክንያት የንግድ እንቅስቃሴ የለም በሚባል ደረጃ ላይ እንደደረሰ....
04:54

Now Playing
የእስራኤሉ ፕሬዝዳንት አይዛክ ሄርዞግ ጉብኝት ለኢትዮጵያና ለአካባቢው ሀገራት ምን ትርጉም ይኖረው ይሆን?
05:55

Now Playing
ዴሞክራቷ የሚኒሶታ የም/ቤት አባል ኢልሐን ኦማር እና ፕሬዘዳንት ትራምፕ
01:26

Now Playing
ስም አይቀበርም በዓሉ ግርማ ሲታወስ
01:22:43

Now Playing
ባለፈው እሁድ የወንጀል ቡድኑ መሪ መገደልን ተከትሎ ሜክሲኮ ረብሻ ውስጥ ገብታለች ፡፡ ግን ይህ ሁሉ ለምን? Sheger Tintane
07:19

Now Playing
ፌስታል ከተከለከለ በኋላ ለእቃ መያዣነት እየተጠቀምንባቸው ያሉ ተተኪ ተብለው እየቀረቡ ያሉ ከረጢቶች ብዙ ጥያቄዎች እየተነሱባቸው ነው፡፡
07:26

Now Playing
የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት በመንግስት በኩል የተሰሩ ሥራዎች በተጠበቀው ልክ ለምን ውጤት ማምጣት አቃታቸው?
04:38
bottom of page

