top of page
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ከሚያስተዳድራቸው ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በቀር የ22 ኤርፖርቶች መሪ እቅድ እንደሌላቸው የኦዲተር መስሪያቤት ሪፖርት አሳየ፡፡
ሰኔ 11/2018 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ከሚያስተዳድራቸው ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በቀር የ22 ኤርፖርቶች መሪ እቅድ እንደሌላቸው የኦዲተር መስሪያቤት ሪፖርት አሳየ፡፡ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የኤርፖርት መሰረተ ልማት ስራዎች እና ኤሮኖቲካል ያልሆኑ ገቢዎች አፈጻጸም ውጤታማነትን በተመለከተ በተሰራ ኦዲት 22 ኤርፖርቶች መሪ እቅድ ወይንም (Master Plan) እንደሌላቸው የኦዲተር መስሪያቤት ሪፖርት ጠቅሷል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የሚያስተዳድራቸው ኤርፖርቶች መሪ ዕቅድ (Master Plan)፣የመሬት አጠቃቀም ካርታ እና የይዞታ ካርታ ሊኖራቸው ይገባ ነበር ያለው ሪፖርቱ ነገር ግን ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በቀር የተቀሩት 22 ኤርፖርቶች የሌላቸውም ሲል አስረድቷል፡፡ ከተጠቀሱት ስምንት ኤርፖርቶ
35 minutes ago


ማስረጃ ሳይቀርብ፣ እንዲሁም መከፈል ካለበት በብልጫና ድጋሚ በተፈፀመ ክፍያ የተለያዩ መ/ቤቶች በቢሊዮን የሚቆጠብ ብር ያላግባብ ወጪ ማድረጋቸው ተረጋገጠ፡፡
ሰኔ 11/2018 የሒሳብ አያያዝ መመሪያዎችን በመጣስ ማስረጃ ሳይቀርብ፣ እንዲሁም መከፈል ካለበት በብልጫና ድጋሚ በተፈፀመ ክፍያ የተለያዩ መ/ቤቶች በቢሊዮን የሚቆጠብ ብር ያላግባብ ወጪ ማድረጋቸው ተረጋገጠ፡፡ የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የ2017 የሒሳብ ምርመራ ሪፖርት እንደሚያሳየው የተሟላ የወጪ ማስረጃ ሳይቀርብ በወጭ ተመዝግቦ የተገኘ ከ1.1 ቢሊዮን ብር በላይ ፣ ማስረጃ ሳይቀርብ ወጪ የተደረገ 35.8 ሚሊዮን ፣ ደንብና መመሪያ ያልተከተለ ወጭ ደግሞ 57.8 ሚሊዮን ብር እና በብጫና ድጋሚ ያላግባብ በተፈፀመ ክፍያ 280.6 ሚሊዮን ብር ያለአግባብ ከመስሪያ ቤቶች ወጪ ተደርጎ መገኘቱን ጠቅሷል፡፡ መመሪያ ተጥሶ መከፈል ካለበት በብልጫና ድጋሚ ያላግባብ ክፍያ ፈፅመዋል ከተባሉት መካከል፡- ጤና ሚኒስቴር 231.1 ሚሊዮን ብር፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስ
2 hours ago


ብሔራዊ ቴአትር በመዋቅር ከተፈቀደው ውጪ የዘርፍ ተጠሪነትን ለዋና ዳይሬክተር በማድረጉ ሙያዊ ነፃነቱን አጥቶ በአመራሩ ፍላጎት ላይ መመስረቱን ሪፖርት አረጋገጠ፡፡
ሰኔ 11/2018 የኢትየጵያ ብሔራዊ ቴአትር የሲቪል ሰርቪስ ይሁንታ ሳያገኝ በመዋቅር ከተፈቀደው ውጪ የዘርፍ ተጠሪነትን በቀጥታ ለዋና ዳይሬክተር በማድረጉ ሙያዊ ነፃነቱን አጥቶ በአመራሩ ፍላጎት ላይ መመስረቱን የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት አረጋገጠ፡፡ በኢትየጵያ ብሔራዊ ቴአትር፤ የቴአትር አፈጻጸምን በተመለከተ በተሰራ የክዋኔ ኦዲት ተቋሙ ተገቢው ጥናት ሳይከናወን እና የሲቪል ሰርቪስ ይሁንታ ሳያገኝ በመዋቅር ከተፈቀደው ውጭ የቴአትር ጥበባት ምዘናና እና ዴስክ ተጠሪነቱን ቀጥታ ለዋና ዳይሬክተር አድርጓል ተብሏል፡፡ በዚህም ምክንያት ውሳኔው ተቋማዊ ሥርዓቱ እንዲዛባ እና የሚደረገው ምዘና ሙያዊ ነፃነቱን አጥቶ በአመራሩ ፍላጎት ላይ እንዲመሰረት ያደረገ ነው ይላል ዛሬ ለፓርላማ የቀረበው የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት፡፡ ሪፖርቱ ለሙዚቃ እና ለ
3 hours ago


''ያለአግባብ ክፍያ መፈፀሙ የተረጋገጠ15 ቢሊዮን ብር አሁንም ተመላሽ አልሆነም’’
ሰኔ 11/2018 በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ያለአግባብ የተፈፀመ ክፍያ መሆኑ ተረጋግጦ ለመንግስት ተመላሽ እንዲደረግ ከታዘዘው ገንዘብ ወደ 15 ቢሊዮን ብር አሁንም ተመላሽ አልሆነም ተባለ፡፡ ተጨማሪ ከ23 ሺህ ዶላር በላይም ወደ መንግስት ካዝና መመለስ ሲኖርበት መ/ቤቶቹ ተመላሽ እንዳላደረጉ የተናገረው የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ነው፡፡ የመንግስትና የህዝብ ሀብት ባክኖ እንዳይቀር በቢሊዮን የሚቆጠረው ብር ተመላሽ እንዲሆን በድጋሚ ለመስሪያ ቤቶቹ ማሳሰቢያ ሰጥቻለሁ ብሏል፡፡ በ2016 በጀት ዓመትና ከዚያ በፊት ከህግ ውጪ የተፈፀሙ ክፍያዎች መሆናቸው በሒሳብ ምርመራ ተረጋግጦ 21 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር እና ከ23 ሺህ ዶላር በላይ ወይምበአሁኑ ምንዛሪ ከ3 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ለመንግስት ተመላሽ እንዲሆን ጥፋቱን የፈፀሙ ተቋማት በደብዳ
3 hours ago


‘’በመንግስት መሥሪያ ቤቶች ከ16.3 ቢሊዮን ብር በወቅቱ አልተወረራረደም’’ የፌዴራል ዋና ኦዲተር
የሰኔ 11/2018 በ138 መሥሪያ ቤቶች እና በ18 ቅርንጫፎች በወቅቱ ያልተወራረደ በጠቅላላው ብር ከ16.3 ቢሊዮን ብር በላይ ሂሳብ መኖሩን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዛሬ ለፓርላማ ያቀረበው ሪፖርት ያሳያል፡፡ ውዝፍ ተሰብሳቢው ሂሳብ ከባለፈው ዓመት ከነበረው ጋር ሲመሳከር በ50 በመቶ መቀነሱን በ65 ገጾች የተሰናዳው የዋና ኦዲተር ሪፖርት ጠቅሷል፡፡ የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የ2017 በጀት ዓመት ሒሳብ የፋይናንሺያል፣ የሕጋዊነት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርትን በዛሬው እለት በፓርላማ መደበኛ ስብሰባ ላይ ያቀርባል፡፡ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 190/2002 መሰረት ለውሎ አበልና ለመጓጓዣ የተሰጠ ቅድሚያ ክፍያ ሰራተኛው ሥራውን አጠናቅቆ ከተመለሰ በኋላ በሰባት ቀናት ውስጥ እንዲሁም የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የሒሳብ አያያዝ መመ
4 hours ago


የመሬት አጠቃቀም ፖሊሲ ለማውጣት ምንድን ነው ያስቸገረው ?
ሰኔ 10/2018 ኢትዮጵያ ለከተማ ለኢንዱስትሪ እርሻና ለሌሎች የሚውሉትን መሬቶች ለመለየት የሚያስችል የመሬት አጠቃቀም ፖሊሲ የላትም፡፡ ፖሊሲው ባለመኖሩ መታረስ የሌለባቸው ቦታዎች እየታረሱ ፋብሪካዎች መገንባት የሌለባቸው ቦታዎች ላይ እየተገነቡ እንዲሁም የተፈጥሮ ችግርም እንዲፈጠር ምክንያት መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡ ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ የመሬት አጠቃቀም ፕላን እንደሌላት ከታወቀ በኋላ ለ141 የኢትዮጵያ ከተሞችና የክልል ከተሞች የመሬት ፕላን ቢዘጋጅም እስካሁን እንዳልፀደቀና ተግባራዊ መሆን እንዳልቻለ ሰምተናል፡፡ ታድያ የመሬት አጠቃቀም ፖሊሲ ለማውጣት ምንድን ነው ያስቸገረው ? የማንስ ሃላፊነት ነው ? ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ… ማርታ በቀለ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shege
22 hours ago


በአለም አቀፍ ደረጃ የለጋሾች ድጋፍ በመቀነሱ ኢትዮጵያን ጨምሮ በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ዘላቂ ለውጥን ለማምጣት የሚያስችል የበጎ አድራጎት ተቋም መገንባት እንዳለባቸው ተመከረ፡፡
ሰኔ 10/2018 በአለም አቀፍ ደረጃ የለጋሾች ድጋፍ በመቀነሱ ኢትዮጵያን ጨምሮ በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ዘላቂ ለውጥን ለማምጣት የሚያስችል የበጎ አድራጎት ተቋም መገንባት እንዳለባቸው ተመከረ፡፡ ለዚህም በመንግስትና በግሉ ዘርፍ መካከል ትብብር መፍጠር ሀገር በቀል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን ማጠናከር እና ማስፋፋት እንደሚያስፈልግ ተነግሯል። ይህ የተነገረው ዛሬ በአዲስ አበባ በተጀመረው የምስራቅ አፍሪካ የበጎ አድራጎት ኮንፈረንስ ላይ ነው። በመድረኩ የበጎ አድራጎት ዘርፍ ላይ የድጋፍ መቀነስ በተለይ ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ ሀገራት የሚገጥሟቸውን ችግሮች ፣ እየተፈጠሩ ያሉ አዳዲስ ለውጦችና በቀጣናው ዘላቂ ልማት ማምጣት ላይ ያተኮሩ ውይይቶች የሚካሄዱበት እንደሆነ ተነግሯል። ኢትዮጵያ እንደ ዩኤስኤአይዲ(USAID) ያሉ የእርዳታ ተቋማት የሚደረግ
22 hours ago
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአንድ ጊዜ 24 መኪኖችን ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያን ወደ ስራ አስገባ።
ሰኔ 10/2018 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአንድ ጊዜ 24 መኪኖችን ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያን ወደ ስራ አስገባ። አገልግሎቱ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን (IPDC) ጋር በመተባበር በአንድ ጊዜ 24 የኤሌክትሪክ መኪኖችን አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ፈጣን ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያ ገንብቶ ወደ ስራ አስገብቷል። ተቋሙ ግዙፍ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎችን በራሱ እና ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ እና በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ለመገንባት በስፋት እየሰራ መሆኑን የአገልግሎቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው ተናግረዋል። በመጋቢት ወር ስራ ከጀመሩት የኮተቤ እና የፒያሳ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች በተጨማሪ አሁን ደግሞ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር በመተባበር ወደ ስራ ያስገባቸው ጣቢያዎች መኖራቸውን ያነሱት ዋና
1 day ago


በአዲስ አበባ 21 የቅጥር ኤጀንሲዎች መታገዳቸው ተሰምቷል
ሰኔ 10/2018 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተያዘው በጀት ዓመት ህጋዊ ፈቃድ ካላቸው የቅጥር ኤጀንሲዎች መካከል 21ዱ መታገዳቸው እና ፤ የ3ቱ ደግሞ ፍቃዳቸው መሰረዙ ተሰምቷል፡፡ 100 የሚሆኑ ኤጀንሲዎች ደግሞ ስራቸውን በአግባቡ አልከወኑም ህጋዊነትንም አልተከተሉም ተብለው ጉዳቸው በቢሮው የማኔጅመንት እየታየ ይገኛል ተብሏል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውስጥ በህጋዊ መንገድ ተመዝግበውና ፈቃድ አውጥተው የሚንቀሳቀሱ ወደ 384 የሚጠጉ የሰራተኛና አሰሪ አገናኝ ኤጀንሲዎች ይገኛሉ። የእነዚህ ኤጀንሲዎች ኃላፊነት ከተሰጣቸው ኃላፊነት ውጭ የሚሰሩ፣ ለሰራተኞች ተገቢውን ደመወዝ የማይከፍሉ፣ እንዲሁም ሰራተኞች ዓመታዊና የወሊድ ፈቃድ በሚወስዱበት ወቅት ደመወዝ የሚቀንሱ ኤጀንሲዎች ላይ ከዕገዳ እስከ ፈቃድ ስረዛ የሚደርስ ጥብቅ እርምጃ እየተወሰደ ነ
1 day ago



Facebook
Twitter
Pinterest
Tumblr
Copy Link
Link Copied
Search video...

Now Playing
እንደ ቤተሰብ - ዛሬም በኢትዮጵያ 40 ሺህ ህፃናት ከዚህ ችግር ጋር ይወለዳሉ'
57:31

Now Playing
በሳውዲ አረቢያ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ/ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
04:54

Now Playing
አልሰማንም እንዳትሉ - የፖለቲካ ሹም ሽር በፍርድ ቤት ይዳኛልን?
04:21

Now Playing
አሜሪካ ጫፌን የምትነካ ከሆነ ኬብሎቹን ቆርጬ የኢንተርኔት ስርዓቱን አስተጓጉላለው #shegerfm #iranisraelwar
07:32

Now Playing
ማሟሻ - የኔን መንግስት በመልካም ስላገለገለ ወዳጃችንን በኒሻናችን አክብረን ሾመን ሸልመነዋል #shegerfm #muamuasha
09:31

Now Playing
ስም አይቀበርም - ሠዓሊ ለማ ጉያ #Lemma_Guya
01:10:56

Now Playing
የኢትዮጵያ ነጋዴዎች ከአንድ እቃ ላይ የሚያተርፉት ምን ያክል ነው?
06:50

Now Playing
መቆያ - ሙሀሙሽን የክፉ ልማድ ሰለባዎች - በእሸቴ አሰፋ
29:19
bottom of page

