top of page
የሰለጠኑ ብቁ ወጣት ኢትዮጵያውያን በካናዳ የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ ሚያስችል ስምምነት ተፈመ፡፡
ሚያዝያ 1/2018 የሰለጠኑ ብቁ ወጣት ኢትዮጵያውያን በካናዳ የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ ሚያስችል ስምምነት ተፈመ፡፡ ስምምነቱን የተፈራረሙት የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴርና ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል ድርጅት ነው፡፡ ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ውስጥ ወደ ካናዳ ስራ ለማሰማራት ብቸኛው በመንግስት ፈቃድ የተሰጠው ተቋም መሆኑን የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡ ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል በማእድን ፣ በኢሮስፔስ ፣ በኮንስትራክሽንና በጤናው ዘርፍ የሚወጡ መስፈርቶችን የሚያሟሉ ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን መልምሎ በማሰልጠን ለስራ ዝግጁ እንደሚያደርግ የስራ እና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈርያት ካሚል ተናግረዋል፡፡ እነዚህ ወጣቶች የሚሰለጥኑት በካናዳ የስልጠና መስፈርት ነው የተባለ ሲሆን ምልመላውም በኢትዮጵያ ገበያ መረጃ ስርዓት አማካኝነት በ
2 days ago


የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር የገቢና ወጭ ጭነት ፍላጎት በብርቱ መጨመሩን እና ስራ እንደበዛበት ተናግሯል።
ሚያዝያ 1/2018 የ ኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር የገቢና ወጭ ጭነት ፍላጎት በብርቱ መጨመሩን እና ስራ እንደበዛበት ተናግሯል። በተለይ የመንግስት እና የግል ከፍተኛ ጭነቶች ከተፈጠረው ነዳጅ እጥረት ጋር በተገናኘ ሎጅስቲክሱ ፊቱን ወደ ባቡር አዙሯል ተብሏል። ድርጅቱ ፤ ያሉትን ማጓጓዣዎች ጠባያቸውን እየቀየረ እና ከ ጉምሩክ ኮሚሽን ፈቃድ እየጠየቀ የምርመራ ቦታዎች በመዳረሻቸው እንዲሆኑ ጠይቋል። ለዚህም ይረዳው ዘንድ የ ጎንዶላ ዋገኖችን መጠቀም መጀመሩን ሰምተናል። ጎንዶላ ዋገን በጠባዩ የላይኛው ክፍሉ ክፍት ነው ፤ ይህም አይነት ዋገን በቀይ በቢጫ እና በአረንጔዴ የሚያልፋ ጭነቶች ከጉምሩክ ኮሚሽን ጋር መናበብን የሚጠይቅ እንደሆነ ይታወቃል። ተህቦ ንጉሴ
2 days ago


በ'ፊንቴክ' የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ ፖሊስ የጠየቀው የተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ ላይ ለመወሰን ፍርድ ቤት ለነገ ቀጥሯል።
ከ"ፊንቴክ" (Fintech) ኢንቨስትመንት ጋር በተያያዘ በከፍተኛ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ዛሬ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። መርማሪ ፖሊስ በቀሪ የምርመራ ስራዎች ምክንያት ተጨማሪ 14 ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋል። ባለፉት 12 የምርመራ ቀናት ያከናወናቸውን ተግባራት ለፍርድ ቤቱ ያስረዳው ፖሊስ፣ 12 የመንግስት እና የግል ሚዲያዎች እንዲሁም ሁሉም የሀገሪቱ ባንኮች በጉዳዩ ዙሪያ ያላቸውን መረጃ በጽሁፍ እንዲልኩ መጠየቁን አስረድቷል። እስካሁን የ150 ምስክሮችን ቃል የተቀበለ ሲሆን፣ ገና ያልተሰሙ ሌሎች ተጨማሪ ምስክሮች መኖራቸውን ጠቁሟል። እያንዳንዱ ተጠርጣሪ በወንጀል ድርጊቱ ውስጥ የነበረውን የግል ተሳትፎ እና የጥቅም ትስስር የሚገልጽ ማብራሪያ
2 days ago
‘’የበጋው መብረቅ’’ ሌተና ጀነራል ጃገማ ኬሎ
#ታሪክን_የኋሊት ‘’የበጋው መብረቅ’’ በሚል ቅፅል ስማቸው የሚታወቁት ሌተና ጀነራል ጃገማ ኬሎ ከዚህ አለም በሞት የተለዩት በ2009 ዓ.ም በዛሬዋ ዕለት ነበር፡፡ አርበኛው ጃገማ ኬሎ ጣሊያን ኢትዮጵያ በወረረችበት ወቅት ከፍተኛ ተጋድሎ በማድረጋቸው ይታወቃሉ፡፡ ጃጋማ ኬሎ የተወለዱት በጅባትና ሜጫ አውራጃ በደንቢ ዮብዲ ወረዳ ውስጥ በ1913 ዓ.ም ነው፡፡ ጃገማ ለቤተሰቦቻቸው የመጨረሻ ልጅ ናቸው፡፡ በልጅነታቸው ወላጅ አባታቸውን በሞት በማጣታቸው ያደጉት ከአጎታቸው ጋር ነው፡፡ አደን ይወዱ የነበሩት ጃገማ የ15 ዓመት ወጣት እያሉ ጣሊያን ኢትዮጵያን ወረረች፡፡ ታዳጊው አዳኝ ከሌሎች የኢትዮጵያ አርበኞቸ ጋር ሆነው ጫካ ገቡ፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥ በርካታ አርበኞችን በማስተባበር ታዋቂ የጦር መሪና አስተባባሪ መሆን ቻሉ፡፡ በተለያዩ የጦር ሜዳዎች የኢጣሊያ
4 days ago


ኢትዮጵያ ከወጪ ንግድ ከምታገኘው ገቢ ግብርና በአማካይ ከሶስት ቢሊየን ዶላር በላይ የሚሆነውን እንደሚያመጣ ይነገራል።
መጋቢት 29/2018 ኢትዮጵያ ከወጪ ንግድ ከምታገኘው ገቢ ግብርና በአማካይ ከሶስት ቢሊየን ዶላር በላይ የሚሆነውን እንደሚያመጣ ይነገራል። መንግስት ደግሞ የዘርፉን ምርታማነት በማሳደግ ገቢውን ይበልጥ ከፍ ለማድረግ እየሰራሁ ነው ብሏል። ምርታማነትን ከማሳደግ ጎን ለጎን ጥራት ማረጋገጡም እኩል ትኩረት የሚሰጠው ነው የሚለው የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ወደ ውጪ የሚላኩትም ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡትም በጠንካራ የፍተሻ ስርአት ውስጥ እንደሚያልፉ ተናግሯል። ግብርና በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ድርሻው ከፍ ያለ እንደሆነ ከግብርና ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ ያመለክታል። እንደ መረጃው ዘርፉ ለጥቅል ሀገራዊ ምርት ( #GDP ) 32 በመቶ ድርሻ ያበረክታል። ከአጠቃላይ የሀገሪቱ ህዝብም እስከ 75 በመቶ የሚሆነው በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋዋሪ በግብርና ተሰማርቶ የሚ
4 days ago


አንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ-ጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
መጋቢት 29/2018 አንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ-ጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። አምባሳደር ቆንጂት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከ1950ዎቹ አንስቶ ከዴስክ ኦፊሰርነት እስከ ከፍተኛ ሀላፊነት ማገልገላቸው ተነግሯል። አምባሳደር ቆንጂት የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት ከመመስረቱ አንድ ዓመት አስቀድመው ወደ ዲፕሎማትነት ህይወት መግባታቸው ይነገራል። በዲፕሎማትነት ሀገራቸውን በማገልገል ቀዳሚ ከሆኑ ሴት አፍሪካዊ ዲፕሎማቶች ውስጥ አንዷ ተደርገውም ስማቸው ይነሳል። ለዚሁ የረጅም ጊዜ አገልግሎታቸውን ከዚህ ቀደም በሀገር ደረጃ እውቅና ተሰጥቷቸዋል። #አምባሳደር_ቆንጂት ከዮዲት እምሩ በመቀጠል፤ በኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሴት አምባሳደርም ናቸው። አምባሳደሯ በኦቶዋ፣ ካይሮ፣ ቴል አቪቭና ቬይና በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች
4 days ago


መጋቢት 28/2018 - ዓለም አቀፍ ወሬዎች
#ፍልስጤም የፍልስጤማውያኑ የጦር እና የፖለቲካ ድርጅት (ሐማስ) የእስራኤል ጦር በጋዛ የሚፈፀመውን ጥቃት አቁሞ ጠቅልሎ ካልወጣ በስተቀር በጭራሽ ትጥቅ አልፈታም አለ፡፡ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለጋዛ ሰርጥ የወደፊት ሰላም ቀደም ሲል ያቀረቡት ባለ 20 ነጥቦች የሰላም እቅድ ሐማስ ሙሉ በሙሉ ትጥቅ እንዲፈታ የሚጠይቅ መሆኑን ሬውተርስ አስታውሷል፡፡ የሐማስ የበላዮች በዚህ ጉዳይ ትናንት ከአደራዳሪዎቹ ጋር መመካከራቸው ተሰምቷል፡፡ ይሄን ተከትሎም የሀማስ ወታደራዊ ክንፍ ቃል አቀባይ አቡ ኦባይዳ የእስራኤል ጦር ከመንፈቅ በፊት በተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት መሰረት የጋዛ ሰርጥን ለቅቆ ካልወጣ በስተቀር በጭራሽ ትጥቅ አንፈታም ብለዋል፡፡ በጋዛ የወደፊት ዘላቂ ስለማለቱ የሐማስ ትጥቅ መፍታት ነገር በጣሙን አስቸጋሪው ጉዳይ እንደሆነ ይነገራል
5 days ago


በቀን እስከ 50 ሺህ ስኩዌር ሜትር ወይም ከ40 እስከ 45 ኮንቴነር ሴራሚክ ማምረት የሚችል ፋብሪካ ከ3 ሳምንት በኋላ ምርት ይጀምራል ተባለ።
መጋቢት 28/2018 በቀን እስከ 50 ሺህ ስኩዌር ሜትር ወይም ከ40 እስከ 45 ኮንቴነር ሴራሚክ ማምረት የሚችል ፋብሪካ ከ3 ሳምንት በኋላ ምርት ይጀምራል ተባለ። በ50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ኢንቨስትመንት ከአዲስ አበባ 65 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው በቱለፋ ከተማ የተገነባው ይህን ፋብሪካ የገነባው ባይጂያ ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ የተባለ ድርጅት ነው። በ30 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ የሴራሚክ እና የፖርስሊን ምርቶች ፋብሪካ ምርት ሲጀምር ብቻውን አሁን ካለው የሴራሚክ ፍላጎት እስከ 70 በመቶ ድረስ የማቅረብ አቅም አለው ተብሎለታል። በባይጂያ ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ የሚመረቱን ምርቶች ለገበያ የሚያቀርበው ማንሰን ኢንቨስትመንትስ ነው። የማንሰን ኢንቨስትመንትስ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳዊት እርገቱ እና የባይጂያ ሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ ዋና
5 days ago


የአካቶ ትምህርት ስርዓት ለአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች
መጋቢት 25/2018 በአካቶ ትምህርት ስርዓት አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች እንዳለባቸው ችግር ተለይተው እንደማንኛውም ሰው የትምህርት እድል እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ቢባልም ልዩ ፍላጎት የሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች ግን ጎዶሎዎች እንዳሉባቸው ይናገራሉ፡፡ በልዩ ፍላጎት የሰለጠነ በቂ መምህራን አለመኖር፣ የትምህርት ቁሳቁስ እጥረት፣ የመሰረተ ልማት ምቹ አለመሆንን ጨምሮ ሌሎች ችግሮች እንዳሉባቸው ያነሳሉ፡፡ ትምህርት ሚኒስቴርም በበኩሉ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች የሚያነሱት ቅሬታ ትክክል ነው ለዚህ ደግሞ እንደ እኩዮቻቸው የትምህርት እድል እንዲያገኙ የአካቶ ትምህርት ሥርዓትን ዘርግቼ እየሰራሁ ነው ብሏል፡፡ በተለይ የአካቶ ትምህርት ትግበራ ሲታሰብ የቁሳቁስ እጥረት፣ የሰለጠኑ መምህራን አለመኖር፣ የመሰረተ ልማት ምቹ አለመሆን በዋናነት የሚነሱ ጥያቄዎች
Apr 3



Facebook
Twitter
Pinterest
Tumblr
Copy Link
Link Copied
Search video...

Now Playing
እስራኤል እና አሜሪካ ጦርነት አቁመው ከኢራን ጋር የስምምነት ፊርማ የሚያኖሩት መቼ ይሆን #Mamuasha #ማሟሻ
10:52

Now Playing
በአዲስ አበባ የመንግስት ሰራተኞች ለአደጋ ቅነሳ በሚል ከደመወዛቸው የመቆረጡ ጉዳይ
05:21

Now Playing
አየርላንድ ኢምባሲ ሴንት ፓትሪክ ቀንን በባህላዊ የሙዚቃ መሳሪዎች ከያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ጋር በመሆን ያካሄዱት ዝግጅት Saint Patrick’s Day!
48:15

Now Playing
ለአእምሮ ጤና እክል አጋላጭ የሆኑ የስራ ዘርፎች የትኞቹ ናቸው፣ምን ጥንቃቄ ማድረግስ ይገባል?
05:40

Now Playing
አልሰማንም እንዳትሉ - እናት ማናት?
05:56

Now Playing
መቆያ - ሞትን የናቀው ጦረኛ - ድራር አልዘዋር - በእሸቴ አሰፋ #shegerfm #mekoya
24:28

Now Playing
መዓዛ ብሩ ከዶ/ር ተካልኝ ወልደማርያም እና ዶ/ር ዮናስ አሽኔ ጋር የተደረገ ወግ መጋቢት 13/ 2018
40:57

Now Playing
ትዝታ ዘአራዳ - የጣሊያን ዘር ከሀበሻ ዘር እንዳይደባለቅ ይደነግግ የነበረው አዋጅ
20:46
bottom of page

