top of page


በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ሀይማኖቶች ወሳኝ መሆናቸውን ሀገራዊ ምክከር ኮሚሽን ተነገረ።
ሐምሌ 11/2018 በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ሀይማኖቶች ወሳኝ መሆናቸውን ሀገራዊ ምክከር ኮሚሽን ተነገረ። በስራ ላይ ካሉት ኮሚሽነሮች አንዱ እና ከስምንቱ አጀንዳዎች ውስጥ ሀይማኖትን የሚመለከተው ቡድን መሪ ኮሚሽነር የሆኑት መላኩ ወልደማርያም ትናንት ሃምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም የምክከር ጉባዔ አስመልክተው ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ ኮሚሽኑ 4,000 ተሳታፊዎችን በ8 ቡድን ማዋቀሩን ተናግረዋል። ኮሚሽኑ የምክክር ጉባዔው ሃምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨማሮ የአፍሪካ ህብረት ተወካዮች በተገኙበት በይፋ መጀመሩን ቢያበስርም "ቴክኒካል"ባላቸው ችግሮች ምክንያት እስከ ሃምሌ 10 ቀን ጉባዔ ማካሄድ እንዳልቻለ ኮሚሽነሩ አስረድተዋል። ትናንት ሃምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ግን 4,000ውን ጉባዔተኛ በ8 ቡድን በአምስት አምስት መቶ አድ
1 day ago


ባለፉት 5 ዓመታት በም/ቤት አባልነት የቆዩት እንደራሴዎችአሳካነው የሚሉት ድል ምንድን ነው?
ሐምሌ 10/2018 ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ተከትሎ ኢትዮጵያን ለመጪዎቹ 5 ዓመታት የሚመራው መንግስት በመስከረም ወር ይሰየማል። በስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ ያሸነፈው የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤትም ለሰባተኛው ተመራጭ ቦታውን ያስረክባል። ለመሆኑ የስድስተኛው የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የስራ ዘመን እንዴት ያለ ነበር? በፓርላማው የነበሩና በሰባተኛው ምርጫው ዳግም ያሸነፉ የህዝብ እንደራሴዎችን አነጋግረናቸዋል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp :
2 days ago


ኢትዮጵያ የትንባሆ ኢንዱስትሪዎች የሚያደርሱትን ተፅዕኖ በመቋቋም ከዓለም 6ኛ መሆኗን ሪፖርት አሳየ፡፡
ሐምሌ 10/2018 ኢትዮጵያ የትንባሆ ኢንዱስትሪዎች የሚያደርሱትን ተፅዕኖ በመቋቋም ከዓለም 6ኛ ከአፍሪካ 2ኛ መሆኗን አለም አቀፉ የትንባሆ ተፅዕኖ ተጋላጭነት ሪፖርት አሳየ፡፡ ለዚህም ምክንያቱ ጠንካራ የትንባሆ ቁጥጥር ህግ ያላት መሆኑና ኢንዱስትሪዎቹ ጫና እንዳያደርጉ መቆጣጠር በመቻሏ ነውም ተብሏል፡፡ ኢትዮጵያ በ2011ዓ.ም ባወጣችው የምግብና መድሃኒት አስተዳደር አዋጅ የትንባሆ ኢንዱስትሪን ጣልቃ ገብነት ስለመቆጣጠር በሰፈረው ድንጋጌ የትንባሆ ኢንዱስትሪዎች ከመንግስት አካላት ጋር ምንም አይነት የጥቅም ትስስር እንዳይኖራቸው ይከለክላል፡፡ እነዚህ ኢንዱስትሪዎች ለመንግስት አካላት በስጦታ ገንዘብ እንዳይሰጡ፤ የበጎ አድራጎት ስራ ላይ እንዳሰማሩ አዋጁ ይከለክላል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት በድጋፍ ስም የትንባሆ ምርት እንዳያስተዋውቁ፤ ስማቸውን እ
2 days ago


ተከለከሉ የተባሉት የፕላስቲክ ምርቶች አምርቶ የሚሸጠው ማን ነው?
ሐምሌ 10/2018 የፕላስቲክ ከረጢት በጤና እና አካባቢ ላይ የሚያደርሰውን ተፅእኖ ለመቀነስ በሚል የወጣው የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ አዋጅ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ 5 ወር አልፎታል። አሁንም ግን የት እንደተመረቱ የማይታወቅ የተከለከሉ ፕላስቲኮች በገበያው ሲሸጡ ይታያል። እነዚህን ፕላስቲኮች አምርቶ የሚሸጠው ማነው? ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ፍቅሩ አምባቸው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1 Telegram : https://shorturl.at/68aeK Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4 WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx X :- https://x.com/shegerfm?s=2 LinkedIn
2 days ago


ከ3,800 በላይ ሰዎችን በሕገ-ወጥ መንገድ አዘዋውረዋል የተባሉት እነ ይትባረክ ዳዊት ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጣቸው፡፡
ሐምሌ 10/2018 ከ3,800 በላይ ሰዎችን በሕገ-ወጥ መንገድ አዘዋውረዋል የተባሉት እነ ይትባረክ ዳዊት ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጣቸው፡፡ ከ3,800 በላይ ሰዎችን በሕገ-ወጥ መንገድ በማደራጀትና በማዘዋወር፣ ለ133 ሰዎች ሞት እንዲሁም ለ116 ሴቶች መደፈር ምክንያት ሆነዋል በሚል ክስ የተመሠረተባቸው እነ ይትባረክ ዳዊት ላይ ፍርድ ቤት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። በአጠቃላይ 16 ክሶች የቀረቡባቸው 11 ተከሳሾች ሲሆኑ፤ ከእነዚህ መካከል ስድስቱ በቁጥጥር ስር ውለው የዋስትና መብታቸው በመታገዱ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ። ቀሪዎቹ 5 ተከሳሾች ግን በሌሉበት ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው በችሎቱ እየታየ ነው። በዐቃቤ ሕግ ከቀረቡት 16 ክሶች መካከል ከኢትዮጵያ፣ ሶማሊያ እና ኤርትራ እስከ ሱዳንና ሊቢያ የሚዘልቅ ዓለም አቀፍ የወንጀል ቡድን
2 days ago












bottom of page
_edited.jpg)
















