top of page
የወል ትርክት እንዴት መገንባት ይቻል ይሆን?
ጥር 7/2018 በኢትዮጵያ ትርክቶች በዝተው ከአንድነት ይልቅ ልዩነት እየሰፋ መምጣቱ እንዳሳሰባቸው የሚናገሩ ብዙዎች ናቸው፡፡ ለኢትዮጵያውያን የጋራ መገለጫ የሆኑ የበዙ ሁነቶች እና ታሪኮች ባለቤት ብንሆንም በተቃራኒ ትርክቶች በዝተው ከአንድነት ይልቅ ልዩነት እየሰፋ መምጣቱ እንዳሳሰባቸው የሚናገሩ ብዙዎች ናቸው፡፡ መንግስትም የፀና ሀገረ መንግስት ለመገንባትም ጭምር የሚያለያዩ ትርክቶችን በጋራ ትርክት መተካት ያስፈልጋል በሚል እየሰራበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ለመሆኑ ለዘመናት የዘለቁ የብሔርተኝነት የልዩነት ትርክቶች ለጦርነትና ራሴን ችዬ ሀገር እሆናለሁ እስከማለት በደረሰበት በአሁኑ ወቅት የጋራ ትርክትን መገንባት ይቻላል ወይ? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ….. YouTube :...
1 day ago


ግብርናውን ለማዘመን የገበሬውን ህይወት ለማሻሻል እና የተሻለ ምርታማነት እውን እንዲሆን የምርምር ስራዎች ሲከወኑ ቆይቷል፡፡
ጥር 7/2018 ግብርናውን ለማዘመን የገበሬውን ህይወት ለማሻሻል እና የተሻለ ምርታማነት እውን እንዲሆን የምርምር ስራዎች ሲከወኑ ቆይቷል፡፡ ለተጠቀሰው መሰል ዓላማ ከሰራቸው 400 የምርምር ስራዎች መካከል 20 ከመቶ የሚሆኑት በስራ ላይ ሳይውሉ መቅረታቸውን የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ተናግሯል፡፡ 80 ከመቶ ወይም 320 ተቋሙ የሰራቸው የምርምር ስራዎች ደግሞ ለታለመላቸው ዓላማ በስራ ላይ መዋላቸውን ሰምተናል፡፡ ተቋሙ ይህን ያለው የ15 ዓመታት የሰራውን ስራ በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ ነው ፡፡ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴ(ዶ/ር) ተቋማቸው ላለፉት 15 ዓመታት ከሰራቸው ጥናቶች መካከል 80 የሚሆኑት ወደ ስራ ያልገቡት እንዲጠናላቸው ያዘዙ ተቋማት ጥናቱን ለመተግበር አቅም ስላነሳቸውና
1 day ago


የኒውክሊየር ኃይል ከውሃ፣ ከንፋስና ከፅሐይ የኃይል አማራጮች በተሻለ ለኢትዮጵያ ምን የተለየ ነገር ይዞላት ይመጣ ይሆን?
ጥር 6/2018 ኢትዮጵያ 13 ቢሊየን ዶላር በጀት ይጠይቃል የተባለን የኒውክሊየር ሀይል ማመንጫ ለመገንባት በዝግጅት ላይ ነች፡፡ በውሃ፣ ነፋስና ፀሐይ ላይ ጥገኛ የነበረው የኤሌክትሪክ ሀይል አማራጭ የኒውክሊየር ሀይልንም ይጠቀማል ተብሏል፡፡ የኒውክሊየር ሀይል ግንባታ ለኢትዮጵያ ምን ይዞላት ይመጣል? የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ኮምሽን ምክትል ኮሚሽነር ኢንጅነር አብዱልቃድር ዑመር የኒውክሊየር ኃይል ከሌሎች የአሌክትሪክ ኃይል አማራጮች በተሻለ በተለዋዋጭ የአየር ሁኔታ እና ሌሎች ተፅዕኖ ውስጥ ሆኖ እንኳን የማይወዥቅ የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ ይችላል ይላሉ፡፡ ምክትል ኮሚሽነሩ ውሃ፣ ፀሐይ እና ንፋስ የኃይል አማራጮች የማመንጨት አስተማማኝነታቸው 50 ከመቶ በታች ሲሆን የኒውክለር ግን 92 በመቶ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ ይህም ኒውክለርን ከሌሎች የኃይል
2 days ago


በሀገራዊ ምክክር የፖለቲካ ልሒቃን፣ ፖለቲከኞች መሳተፍ አለመሳተፍ በውጤቱ ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ ምንድን ነው?
ጥር 6/2018 በሀገራዊ ምክክር የፖለቲካ ልሒቃን፣ ፖለቲከኞች መሳተፍ አለመሳተፍ በውጤቱ ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ ምንድን ነው? የሁለቱን ወገን ሃሳብ ጠይቀናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. ያሬድ እንዳሻው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ….. YouTube : https://url-shortener.me/2DTR Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 Facebook፡ https://url-shortener.me/2DTY WhatsApp : https://url-shortener.me/2DU0 X : https://x.com/shegerfm?s=2 Website፡ https://www.shegerfm.com/ LinkedIn : https://url-sh
2 days ago


በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የግል አየር መንገዶች ለአውሮፕላኖቻቸው ጥገና በዓመት እስከ 800,000 ዶላር ያወጣሉ ተባለ፡፡
ጥር 6/2018 በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የግል አየር መንገዶች ለአውሮፕላኖቻቸው ጥገና በዓመት እስከ 800,000 ዶላር ያወጣሉ ተባለ፡፡ አየር መንገዶቹን ከዚህ ወጪ፣ የውጭ ሀገር ጉዞና እንግልት ለማዳን ያግዛል የተባለ አገልግሎት እንዲሰጥ ለኢትዮጵያ አየር ሀይል የአውሮፕላን ጥገና ፈቃድ ተሰጥቶታል፡፡ በኢትዮጵያ ያሉ የግል አየር መንገዶች በቁጥር አስራ ሁለት መድረሳቸው ተነግሯል። የነዚህ አየር መንገዶች ንብረት የሆኑ መካከለኛና አነስተኛ አውሮፕላኖች ጥገና ሲፈልጉ አገልግሎቱን የሚሰጣቸው እራሱን የቻለ የጥገና ማዕከል በሀገር ውስጥ አልነበረም ተብሏል። በዚህም ምክንያት ለጥገና አገልግሎት ወደ ኬንያና ሌሎችም ሀገሮች ለመጓዝ እንደሚገደዱ ተሰምቷል። ይህም ብዙ ወጪን የሚያስወጣቸው አቅማቸውንም የሚፈታተን መሆኑን ሰምተናል። አሁን ግን
2 days ago


የኦሮሚያ ሕብረት ስራ ባንክ ከ20.5 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች ባለው በኮፔይ ኢ - ብር እስካሁን ከ4.8 ትሪሊዮን ብር በላይ ግብይት መፈጸሙን ተናገረ።
ጥር 6/2018 የኦሮሚያ ሕብረት ስራ ባንክ ከ20.5 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች ባለው በኮፔይ ኢ - ብር እስካሁን ከ4.8 ትሪሊዮን ብር በላይ ግብይት መፈጸሙን ተናገረ። ባንኩ ከውጭ ሀገር የሚላክላቸውን የውጭ ምንዛሬ ከባንኩ በኩል ለተቀበሉ ደንበኞቹ ባዘጋጀው የውጭ ምንዛሪ የሎተሪ እድለኞችን ሸልሟል፣ ዲጂታል ሎተሪ ሽያጭ እንደሚጀምር ተናግሯል። የተላከላቸውን የውጭ ሀገር ገንዘብ ከኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ በመቀበላቸው እድለኛ የሆኑ ደንበኞች አንድ ዘመናዊ የቤት መኪና፣ 2 የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል ፣10 ላፐቶፖች፣ 10 ቴሌቪዥኖችና 40 ስማርት ስልኮች በአጠቃላይ 63 ሸልማቶች ዕድለኞች ተበርክተዋል። የባንኩ ኦፕሬቲንግ ተጠባባቂ ቺፍ አፊሰር አቶ አብዲ ፈቀደ ባንኩ ከኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎትና ታምሶል ኮሚዩኒኬሽን ጋር በመተባበር፣ በኮፔይ ኢ-ብር
2 days ago


በትግራይ ክልል ከጦርነቱ በፊት በባንክ ብድር ተገንብተው በጦርነቱ የወደሙ ፕሮጀክቶች እዳ ሙሉ በሙሉ እንዲሰረዝ የክልሉ ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክርቤት ብሔራዊ ባንክን በደብዳቤ ጠየቀ፡፡
ጥር 5/2018 በትግራይ ክልል ከጦርነቱ በፊት በባንክ ብድር ተገንብተው በጦርነቱ የወደሙ ፕሮጀክቶች እዳ ሙሉ በሙሉ እንዲሰረዝ የክልሉ ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክርቤት ብሔራዊ ባንክን በደብዳቤ ጠየቀ፡፡ የትግራይ ክልል ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክርቤት የክልሉ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ብድር ከሰሜኑ ጦርነት በፊት ማለትም ከ2012 ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ ከነበረበት 32 ቢሊዮን ከነወለዱ አሁን ከ80 ቢሊዮን ብር በላይ ሆኗል ብሏል፡፡ ምክርቤቱ በክልሉ ለንግድ እና ኢንቨስትመንት የተወሰዱ የባንክ እዳዎች የንግዱ ማህበረሰብ መክፍል ስለማይችል ከፕሪቶሪው የሰላም ስምምነት በኋላ የመክፈያ ጊዜ ገደብ ለ18 ወራት ተራዝሞለት እንደነበር የምክርቤቱ ፕሬዝዳንት አቶ በሪሁ ሃፍቱ ተናግረዋል፡፡ ንጋዴዎቹም ሆኑ አልሚዎቹ በተሰጣቸው 18 ወራት ስራ
3 days ago


በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ከሳምንት በኋላ በሚከበረው የጥምቀት በዓልም የተሻለ የቱሪስት ፍሰት እንደሚኖር ዝግጅት ተደርጓል፡፡
ጥር 5/2018 ከፍ ያለ የውጭ ቱሪስት ከሚገኝባቸውና የሀገር ውስጥ ቱሪዝም እንቅስቃሴም ሞቅ ከሚልባቸው ሃይማኖታዊ በዓላት መካከል የጥምቀት በዓል አንዱ ነው፡፡ በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ከሳምንት በኋላ በሚከበረው የጥምቀት በዓልም የተሻለ የቱሪስት ፍሰት እንደሚኖር ዝግጅት ተደርጓል፡፡ በቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎች ለቱሪስቶች የተሻለ የትራንስፖርት አማራጭ እንዲኖርና ለብዙዎችም ጊዜያዊ የስራ እድል እንዲፈጠር እየተሰራ ነው ተብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. በረከት አካሉ YouTube : https://url-shortener.me/2DTR Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1 Facebook፡ https://url-shortener.me/2DTY WhatsApp : https://url-shortener.me/2D
3 days ago


ሠራተኞቻቸውን የጡረታ መዋጮ በጊዜው ገቢ የማያደርጉ የግል ድርጅቶች ራሳቸውን ላልተገባ ቅጣት እና ወለድ እየዳረጉ ነው ተባለ።
ጥር 5/2018 ሠራተኞቻቸውን የጡረታ መዋጮ በጊዜው ገቢ የማያደርጉ የግል ድርጅቶች ራሳቸውን ላልተገባ ቅጣት እና ወለድ እየዳረጉ ነው ተባለ። ሃብት ንብረታቸውን ሸጦ የጡረታ መዋጮው ገቢ እንዲሆን እስከ ማድረግ የሚደርስ እርምጃ ሊወስድባቸው እንደሚችልም የግል ድርጅት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር አሳስቧል። አንድ እና ከአንድ በላይ ሠው የቀጠረ ማንኛውም የግል ድርጅት ሠራተኛውን ወደ ጡረታ አቅድ የማስገባት ግዴታ እንዳለበት የግል ድርጅት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር አሳስቧል፡፡ ሠራተኛው ወደ ጡረታ ስርአቱ መግባት ያለበት ከተቀጠረ ከአርባ አምስት ቀናት በኋላ እንደሆነ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አባተ ምትኩ ተናግረዋል። አብዛኞቹ ቀጣሪ ድርጅቶች ግን ሠራተኛው ኮንትራት ነው ወይም ጊዜያዊ ነው በሚል ይህን ግዴታ ያለ ማክበር ዝንባ
3 days ago



Facebook
Twitter
Pinterest
Tumblr
Copy Link
Link Copied
Search video...

Now Playing
“ብዙ ሰው ማስቀመጥ እንጂ መክፈል አይፈልግም” @ShegerFM1021Radio
45:27

Now Playing
በመንጃፍቃድ እና በመታወቂያ ላይ የተመዘገበው የመኖርያ አድራሻ የተለያየ ነው ተብሎ ዋስትና ይከለከል ይሆን? Alsemanim Endatilu
05:54

Now Playing
አርበኛ በላይ ዘለቀ እና ወንድሙ እጅጉ ዘለቀ በስቅላት የተቀጡበት ዕለት! #Tarikn_Yehualit
02:34

Now Playing
የኢትዮጵያ ቡና ተገዳዳሪዎች!
07:24

Now Playing
Sheger Cafe - መዓዛ ብሩ ከዶ/ር ተካልኝ ወልደማርያም እና ዶ/ር ዮናስ አሽኔ ጋር
40:40

Now Playing
Sheger Cafe ‹‹የገና በዓል አከባበር በላሊበላ እንዴት ያለ ነው?›› መዓዛ ብሩ እና የታሪክ ተመራማሪው አቶ አበባው አያሌው ጋር የተደረገ ወግ
57:06

Now Playing
Mekoya - አጥፊ እና ጠፊ...ትራምፕ እና ማድሮ! Maduro And Trump /በእሸቴ አሰፋ @ShegerFM1021Radio
26:47

Now Playing
Yechewata Engida ከቶቶት የባህል ምግብ አዳራሽ ባለቤት አቶ ጠንክር ቴኒ ጋር የተደረገ ጨዋታ- 2ኛ ሳምንት ክፍል 2 @ShegerFM1021Radio
26:05
bottom of page








