top of page
የአዲስ አበባ ስነ ስሪት (የተዋቀረችበት መንገድ) ለከተማ ልማትና ዕድገት አስቸጋሪ አድርጓታል ተብሏል።
ግንቦት 4/2018 የአዲስ አበባ ስነ ስሪት (የተዋቀረችበት መንገድ) ለከተማ ልማትና ዕድገት አስቸጋሪ አድርጓታል ተብሏል። አመሰራረቷም በተጠና የከተማ ፕላን ሳይሆን በልማዳዊ ሰፈራ መሆኑ ከነገስታቱ ጀምሮ ባለው ስርዓት ውስጥ አዲስ አበባን ለማዘመን ፈተና ሆኖ መቀጠሉም ተነግሯል። ይህ የተነገረው ናሽናል ሚዲያ አክስዮን ማህበር "አዲሲቱ አዲስ" በሚል ርዕስ የአዲስ አበባ ከተማን የማደስና የልማት ሥራዎች፣ በጎ ዕድሎችና ፈተናዎች ላይ ያተኮረ ውይይት በተካሄደበት መድረክ ላይ ነው። በመድረኩ ላይ የዳሰሳ ፅሁፍ ያቀረቡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህሩ ዳዊት በንቲ (ዶ/ር)፤ አዲስ አበባ ከሌሎች የዓለም ከተሞች በዕድሜ ትንሿ መሆኗን አንስተዋል። ከተማዋ የተቆራረጠች እና ለዋና ከተማነት የማትመች ቦታ ላይ ነች ያሉት ዳዊት(ዶ/ር)፤ ይህም በየጊዜው ከተማዋ
11 hours ago


ለመገናኛ ብዙሃን ባለሞያዎች የሙያ ብቃት ማረጋገጫ መታወቂያ ለመስጠት የተጀመረው ስራ ከምን ደርሶ ይሆን?
ግንቦት 4/2018 ለመገናኛ ብዙሃን ባለሞያዎች የሙያ ብቃት ማረጋገጫ መታወቂያ ለመስጠት የተጀመረው ስራ ከምን ደርሶ ይሆን? የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤትን ጠይቀናል፡፡ የሚዲያ ባለሞያዎች የሙያ ማህበር የሆነው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት በሚዲያው ዘርፍ ያሉ ባለሞያዎችን መዝግቦ የሞያ ብቃት ማረጋገጫ መታወቂያ ለመስጠት የሚያስችለውን ጥናት ማድረጉን የተናገረው የዛሬ ዓመት በዚህ ወቅት ነበር፡፡ 102 የሚደርሱ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማትን በአባልነት እንደያዘ የሚናገረው ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ ምን ያህል ጋዜጠኞች እንዳሉ ለማወቅ ከመመዝገብ ጀምሮ የሞያ ብቃት ማረጋገጫ መታወቂያ ለመስጠት እየተዘጋጀሁ ነው ማለቱን ተከትሎ የመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣንን ጨምሮ ከጋዜጠኞችም ምክር ቤቱ የብቃት ማረጋገጫውን መስጠት አይችልም የሚሉ ትችቶች ሲሰ
16 hours ago


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት 9 ወራት የስነ ምግባር ጥሰት በፈፀሙ 1,139 የአገልግሎቱ ሠራተኞች ላይ የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃዎች መውሰዱን ተናገረ፡፡
ግንቦት 4/2018 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት 9 ወራት የስነ ምግባር ጥሰት በፈፀሙ 1,139 የአገልግሎቱ ሠራተኞች ላይ የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃዎች መውሰዱን ተናገረ፡፡ እርምጃ ከተወሰደባቸው ኃላፊዎችና ሠራተኞች መካከል 16ቱ ከስራቸው ሲሰናበቱ፤ 721ዱ የደመወዝ ቅጣት እንዲሁም 402 የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ናቸው ተብሏል፡፡ አገልግሎቱ በሠራተኞች ላይ ከወሰዳቸው አስተዳደራዊ እርምጃዎች መካከል 103 ሠራተኞች ላይ በደንበኞች የቀረበን ጥቆማ በመመርመር የወሰደው መሆኑንና ቀሪ 1,036ቱ ተቋሙ በራሱ ግኝት አጣርቶ የወሰዳቸው እርምጃዎች መሆናቸውን ተናግሯል፡፡ ባለፉት 9 ወራት አገልግሎቱ በሙስና መጠቆሚያ ዘመናዊ መተግበሪያ እና በሌሎች አማራጮች ከደንበኞቹ የደረሱትን 427 ጥቆማዎችን መርምሮ በ103 ኃላፊዎችና ሠራተኞች ላይ የ
18 hours ago


የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዘገየ አስፋው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
ግንቦት 4/2018 የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዘገየ አስፋው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። አቶ ዘገየ የግብርና ሚኒስቴርን ከ1968–1970 ዓ.ም እና ከ1983 - 1984 ዓ.ም በሚኒስትርነት ማገልገላቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል፡፡ አቶ ዘገየ አስፋው መሬት ለአራሹ አዋጅ እንዲታወጅ ከፍተኛ ድርሻ ነበራቸው፡፡ አቶ ዘገየ አስፋው ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ አለም ተለይተዋል ሲል የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተናግሯል፡፡ ከዚህ አለም በሞት እስከተለዩ ድረስም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው እየሰሩ ነበር፡፡ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at/18TS1
19 hours ago


ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለህዳሴ ግድብ 1.2 ቢሊዮን ብር ተሰብሰቧል ተባለ።
ግንቦት 3/2018 ባለፉት 9 ወራት ለህዳሴ ግድብ 1.2 ቢሊዮን ብር ተሰብሰቧል ተባለ። ይሀም ለመሰብሰብ ከታቀደው ውስጥ ከ50 በመቶ በታች ወይም 1.2 ቢሊዮን ብር ብቻ ነው ተብሏል፡፡ ባለፉት 9 ወራት ሀገሪቱ ከኤሌክትሪክ ሀይል ሽያጭ ወደ 366 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷ ታውቋል፡፡ ይህ የተነገረው የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባለፉት 9 ወራት የሰራቸውን ስራዎች ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ባለፈው ሚያዝያ 29/2018 ዓ.ም ባቀረበበት ወቅት ነው፡፡ ጷጉሜ 4/2017 ዓ.ም የግንባታ ስራው ተጠናቅቆ ለተመረቀው ታላቁ ህዳሴ ግድብ 9 ወራት ውስጥ በህዝብ ተሳትፎ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ተሳትፎ በዘጠኝ ወራት ውስጥ 2.58 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ እንደነበር ለምክር ቤቱ የቀረበው ሰነድ ያሳያል፡፡ ይሁንና የእቅዱን 50 በመቶ ገደማ
2 days ago


በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች በ500,000 እና 400,000 ብር ዋስ እንዲፈቱ ተወሰነ።
ግንቦት 3/2018 በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች በ500,000 እና 400,000 ብር ዋስ እንዲፈቱ ተወሰነ። መንሱር ጀማል የተባለው ተከሳሽ ግን አቃቢ ህግ መቃወሚያ ስላቀረበበት ዛሬ ከሰዓት ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ከድርጅቱ ጋር በተያያዘ በ1.9 ቢሊዮን ብር የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ታዋቂ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች፣ የዋስትና መብታቸው ተከብሮ በውጭ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት ፈቅዷል። ባለፈው ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ከ5 ተከሳሽ መንሱር ጀማል ውጭ ባሉ ተጠርጣሪዎች ከሀገር እንዳይወጡ እና ከፍ ያለ ዋስትና አስይዘው የዋስትና መብታቸው ተከብሮ ከውጭ ሆነው ጉዳያቸውን ቢከታተሉ እንደማይቃ
2 days ago
በአዲስ አበባ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ጉቦ እና የእጅ መንሻ፤ አካውንት ቁጥር እስከ መስጠት መድረሱ ተነገረ፡፡
ሚያዝያ 30/2018 በአዲስ አበባ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ጉቦ እና የእጅ መንሻ፤ አካውንት ቁጥር እስከ መስጠት መድረሱ ተነገረ፡፡ በአዲስ አበባ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ለአገልግሎት የሚመጡ ሰዎችን ጉቦ የሚጠይቁ እንዳሉ የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል ነው የተናገሩት፡፡ ጉቦ እና እጅ መንሻ መጠየቅ፤ አገልግሎት መስጠት ላይ እንቅፋት ሆኖ መቀጠሉም ከምክር ቤት አባል ተነስቷል፡፡ #ጉቦ ጠይቀው የተገኙት ላይም የሚወሰድባቸው እርምጃ እና የሚወሰኑ ውሳኔዎች ቀለል ያሉ ናቸው ተብሏል፡፡ ይህ መሆኑ ጉቦ ጠያቂዎቹ የበለጠ እየተደፋፈሩ እንደሆነና ቅጣቱ ሌሎችን ሊያስተምር እንዳልቻለ ተጠቅሷል፡፡ ይህ የተነገረው ዛሬ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ ነው፡፡ ይህንን ተግባር ለማስቆም ምን እየተሰራ እንደሆነም ጥያቄ ቀ
4 days ago


የሚያዝያ ወር የዋጋ ግሽበት ምጣኔ ከ11 በመቶ መሻገሩን መንግስት ተናገረ።
ሚያዝያ 30/2018 የሚያዝያ ወር የዋጋ ግሽበት ምጣኔ ከ11 በመቶ መሻገሩን መንግስት ተናገረ። አምና በዚህ ወቅት የዋጋ ግሽበቱ 14.4 በመቶ እንደነበር ያስታወሰው የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት ሲሆን ዘንድሮ በመጠኑ ቅናሽ አሳይቷል ብሏል። የዘንድሮ የሚያዝያ ወር የግሽበት ምጣኔ 11.7 በመቶ ነው። ከባለፈው ወር ደግሞ 2.2 በመቶ ያህል ጨምሯል። በተለይ ምግብ ነክ የሆኑና አልኮል የሌላቸው መጠጦች ደግሞ ከፍተኛ ሆኖ የዋጋ ግሽበት ምጣኔአቸው 13.5 በመቶ ደርሷል። ለአብነትም አትክልት፣ ስጋ፣ የወተት ተዋፅዖዎች፣ እንቁላል፣ ፍራፍሬ፣ ዘይት እና ስኳር የመሳሰሉት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ጨምሯል ብሏል አገልግሎቱ ባወጣው መረጃ። ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት 9.1 በመቶ የደረሰ ሲሆን የትራንስፖርት ዋጋ በ13 በመቶ ከፍ ብሏል። በምግብ ቤቶች እና ሆ
5 days ago


በአጭር ጊዜ ለግንባታ የሚጠይቀውን በጀት አግኝተው ግንባታን ይከውኑት ይሆን?
የሚያዝያ 29/2018 የትምህርት ሚኒስቴር በቀሪዎቹ 4 ወራት 1,452 የቅድመ መደበኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሁሉም ክልሎች ለመገንባት በቅብሩ ከክልሎች ጋር ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ እነዚህ ትምህርት ቤቶች የሚገነቡት ግማሹ በትምህርት ሚኒስቴር ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በክልሎቹ በራሳቸው ወጪ ነው፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር ለሚያስገነባቸው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 40 ሚሊዮን ዶላር ፈንድ ከአጋር አካላት በእርዳታ ማግኘቱን ተነግሯል፡፡ ታዲያ ክልሎች በአጭር ጊዜ ለግንባታ የሚጠይቀውን በጀት አግኝተው ግንባታን ይከውኑት ይሆን? የተለያዩ ክልሎችን ጠይቀናል፡፡ የደቡብ ኢትዮጵ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዮት ደምሴ በክልሉ የሚገነባው 70 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ እነዚህ ትምህርት ቤቶች ሲገነቡ በክልሉ ውስጥ
5 days ago



Facebook
Twitter
Pinterest
Tumblr
Copy Link
Link Copied
Search video...

Now Playing
መዓዛ ብሩ ከዶ/ር ተካልኝ ወልደማርያም እና ዶ/ር ዮናስ አሽኔ ጋር የተደረገ ወግ - ሚያዝያ 18 / 2018
35:12

Now Playing
መቆያ - የሁለት አምባገነን መሪዎች ሀገር - ክፍል 2 በእሸቴ አሰፋ #shegerfm #mekoya
23:16

Now Playing
ከዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ መሥራች መቶ አለቃ ትዕዛዙ ኮሬ ጋር የተደረገ ጨዋታ 3ኛ ሳምንት ክፍል - 2
34:45

Now Playing
ከዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ መሥራች መቶ አለቃ ትዕዛዙ ኮሬ ጋር የተደረገ ጨዋታ 3ኛ ሳምንት ክፍል - 1
32:51

Now Playing
ትዝታ ዘ አራዳ - ዕውቁ ዲፕሎማት እና ምሁር መላኩ በያን (ዶ/ር)
27:10

Now Playing
እስራኤል እና አሜሪካ ጦርነት አቁመው ከኢራን ጋር የስምምነት ፊርማ የሚያኖሩት መቼ ይሆን #Mamuasha #ማሟሻ
10:52

Now Playing
በአዲስ አበባ የመንግስት ሰራተኞች ለአደጋ ቅነሳ በሚል ከደመወዛቸው የመቆረጡ ጉዳይ
05:21

Now Playing
አየርላንድ ኢምባሲ ሴንት ፓትሪክ ቀንን በባህላዊ የሙዚቃ መሳሪዎች ከያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ጋር በመሆን ያካሄዱት ዝግጅት Saint Patrick’s Day!
48:15
bottom of page

