top of page
በምክክሩ የሚሳተፉ ታዛቢዎችን ለጉባኤው ዝግጁ የማድረጉ ስራ እንዴት እየሆነ ነው?
ሐምሌ 4/2018 በአዲስ አበባ የሚካሄደው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በመጪው ሳምንት ረቡዕ ይጀመራል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ሌሎችም በምክክሩ በታዛቢነት እንዲገኙ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። ለመሆኑ በዓለም አቀፍ መስፈርቱ መሰረት በምክክሩ የሚሳተፉ ታዛቢዎችን ለጉባኤው ዝግጁ የማድረጉ ስራ እንዴት እየሆነ ነው? በተቀመጡ አለም አቀፍ መስፈርቶች መሰረት መሰል የምክክር ሂደቶችን የመታዘብ ስራ ምክክሩ ከመካሄዱ 45 ቀን በፊት ጀምሮ መጀመር እንዳለበት ከባለሙያዎች ሰምተናል። የኢትዮጵያ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤትን ጨምሮ ሌሎችም ተቋማት ማቅረብ ያለባቸው የታዛቢዎች ቁጥር ተወስኖ እንዲያቀርቡ ኮሚሽኑ ጥሪ ማስተላለፉና ተቋማቱም ታዛቢዎቹን እያዘጋጁ መሆኑን በኮሚሽኑ የተደራሽነት እና አጋርነት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ፍሬሰናይ ገበየሁ ጠቁመዋል።
1 day ago


ዲጂታል ባንኪንግ ስራን ያቀለለ መሆኑ ቢነገርለትም በሌላ በኩል ለዲጂታል መጭበርበርም እያጋለጠ መሆኑ ይነገራል፡፡
ሐምሌ 4/2018 ዲጂታል ባንኪንግ ስራን ያቀለለ መሆኑ ቢነገርለትም በሌላ በኩል ለዲጂታል መጭበርበርም እያጋለጠ መሆኑ ይነገራል፡፡ ከእነዚህም የማታለያ ስልቶች መካከል አንዱ ሃሰተኛ የድጅታል ደረሰኝ ሰርቶ ሻጮችን ማጭበርበር እየተበራከተ መጥቷል። ስለ ጉዳዩ ያነጋገርናቸው ነጋዴዎች፣ አጭበርባሪዎች ከባንክ ሂሳባቸው ገንዘብ ተቀናሽ ሳያደርጉ ትክክለኛውን የሚመስል ሃሰተኛ ድጅታል ደረሰኝ እያሳዩአቸው ብዙ ገንዘብ እንደተጭበረበሩ ነግረውናል፡፡ አታላዮች ይህንን ሃሰተኛ ድጅታል ደረሰኝ ለመስራት ህገ ወጥ ሶፍትዌሮችን የሚጠቀሙ ሲሆን እነዚህ ሶፍትዌሮች የፈለጉትን የገንዘብ መጠን እና የደንበኛ ስም መፃፍ እንደሚያስችሏቸው ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ በባንክ ተቋማት ውስጥ የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት እና ስትራቴጂ ባለሙያ የሆኑት አቶ ሃብተማርያም አደረ ባንኮች አሁን በሚከ
1 day ago


በሰባተኛው ሃገራዊ ምርጫ የተከሰቱ ችግሮች እንዳይደገሙ የህግ ማሻሻያ በማድረግ እንዲታረሙ ተጠየቀ፡፡
ሐምሌ 3/2018 በሰባተኛው ሃገራዊ ምርጫ የተከሰቱ ችግሮች መልሰው እንዳይደገሙ የህግ ማሻሻያ እና የአፈፃፀም ማስተካከያ በማድረግ እንዲታረሙ ተጠየቀ፡፡ ባለፈው ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በተፈናቃይ ካምፖች በተቋቋሙ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች የተካሄደው ምርጫ የራሱ መመሪያ ወጥቶለት የተካሄደ አዲስ አሰራር ነበር፡፡ በልዩ ሁኔታ ምርጫ ስለሚካሄድባቸው ምርጫ ጣቢያዎች ማቋቋሚያ መመሪያ ወጥቶ ተፈናቃዮች የመምረጥ መብታቸውን እንዲጠቀሙ መደረጉ መልካም መሆኑ በልዩ የምርጫ ጣቢያዎች በገለልተኝት ምርጫውን የታዘበው የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች ህብረት ተናግሯል፡፡ ይሁንና ተፈናቃዮች የሚሰጡት ድምፅ ወደ ተፈናቀሉበት ቀዬ ሂዶ የሚቆጠር መሆኑ ለምርጫው ፍላጎት እንዲያጡ አድርጓቸዋል ብሏል፡፡ ለዚህም እንደማሳያ ከ20 ሺህ በላይ ተፈናቃዮች በነበሩበት ካምፕ 4
2 days ago


የሀገር ውስጥ ችግርና የአለም አቀፍ ጫና እና ተፅዕኖ ምን እና ምን ናቸው?
ሐምሌ 3/2018 የውስጥ ፖለቲካዊ ችግሯን በራሷ መፍታት የቻለች ሀገር ለውጪው ተፅዕኖ ተጋላጭ አትሆንም ይላሉ ባለሙያዎች፡፡ ኢትዮጵያም ከምንም ነገር በፊት በሀገር ውስጥ ያላትን ሰላም ታረጋግጥ እየተባለ ተደጋግሞ ሲመከር ይሰማል፡፡ ለመሆኑ የሀገር ውስጥ ችግርና ፖለቲካዊ ውጥረት እንዲሁም የአለም አቀፍ ጫና እና ተፅዕኖ ምን እና ምን ናቸው? ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…… ያሬድ እንዳሻው
2 days ago


በችግሮች እየተፈተኑ ያሉት ቴአትር ቤቶች
ሐምሌ 2/2018 በተመልካች ቁጥር ማነስና በሌሎችም ችግሮች እየተፈተኑ ያሉትን የኢትዮጵያን የቴአትር ቤቶች ከችግራቸው ለማውጣት መንግስት በትኩረት ሊሰራ ይገባል ተባለ፡፡ ከገንዘብ እጥረት እስከ ግብአት እጥረት ቲያትር ቤቶቹ በበረታ ችግር ውስጥ ናቸው ተብሏል፡፡ ረዘም ላሉ ዓመታት በቴአትር ሙያ ላይ የሰሩት አርቲስት አፅናፉ መኩሪያ የቲያትር ቤቶች መዳከም ብዙ ምክንያቶች ቢኖሩትም ትልቁ ችግር ግን መንግስት ለኪነ ጥበቡ ዘርፍ ትኩረት አለመስጠቱ ነው ይላሉ። ስለ ቴአትር በቂ ዕውቀት የሌላቸው ሰዎች በቴአትር ቤቶች አስተዳደር ውስጥ ሲሾሙ ይታያል፣ ይህም የቴአትር ዘርፉን እንደጎዳው ያስረዳሉ። ሌለኛው የቴአትር ባለሙያ አርቲስት መርዕድ ነጋሽ ደግሞ በኪነ-ጥበቡ ላይ መንግስት የጣለው ታክስ ቀድሞውኑ እምብዛም ገቢ የሌለው የቲያትር ዕድገት ላይ ተፅዕኖ አሳድ
3 days ago


ኢትዮጵያ የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ከመጠቀም ባለፈ በዘርፉ አለም አቀፍ የምርምር ስራንም እየሰራች ነው ተባለ፡፡
ሐምሌ 2/2018 ኢትዮጵያ የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ከመጠቀም ባለፈ በዘርፉ አለም አቀፍ የምርምር ስራንም እየሰራች ነው ተባለ፡፡ በአለም አቀፍ ህትመቶች ላይ የቀረቡ ከ60 በላይ ጥናቶች እስካሁን መሰራታቸው ተነግሯል፡፡ ይህን የተናገረው የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ነው። እነዚህ ጥናትና ምርምሮች በሳይንሱና በአካዳሚው አለም ከፍተኛ የምርምር እውቀና እና ማረጋገጫ አግኝተው በአለም አቀፍ ጆርናሎች እየታተሙ ነውም ተብሏል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ስነ-ምግባራዊ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መርህን የተከተለ እንደሆነም ኢንስቲትዩቱ ተናግሯል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ዘውዴ በተቋማትም ሆነ በግለሰቦች ደረጃ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴ
3 days ago


የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን ፍትሃዊነትና አካታችነት የሚታዘቡ 10 ታዛቢዎችን እንደሚያሰማራ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ተናገረ።
ሐምሌ 2/2018 የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን ፍትሃዊነትና አካታችነት የሚታዘቡ 10 ታዛቢዎችን እንደሚያሰማራ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ተናገረ። የኢትዮጵያ ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሃምሌ 8 ለሚጀመረው ሃገራዊ የምክክር ጉባኤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት 10 ታዛቢዎችን እንዲያቀርብ ኮታ እንደሰጠው ምክር ቤቱ ነግሮናል። ታዛቢዎቹ የምክክሩ ሂደት አካታችና ተደራሽ መሆን አለመሆኑን የሚከታተሉበት ሰነድ ተዘጋጅቶ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ተረፈ ደጌቲ ነግረውናል። ታዛቢዎቹ የተመረጡቱ የምክር ቤቱ አባል ከሆኑ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች መሆኑን የጠቀሱት አቶ ተረፈ፤ እነዚህ 50 የምር ቤቱ አባላት ዛሬ የተሰጠውን ስልጠና ወስደው ከመካከላቸው 10 ለታዛቢነት ይመረጣሉ ብለዋል። በተ
3 days ago


ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ የሚፈጀው የኢሰመኮ የ5 ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ
ሐምሌ 2/2018 የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን "የታጠቁ የጸጥታ አካላት መበራከት" ለትግበራው እንቅፋት ሊሆንበት እንደሚችል ስጋቱን ጠቅሶ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ የሚፈጀውን የ5 ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ ይፋ አድርጓል፡፡ ኮሚሽኑ ከ2019 እስከ 2023 የሚያገለግለውን የ5 ዓመት የሰብአዊ መብት ስትራቴጂክ እቅድ ዛሬ ሐምሌ 2 ቀን 2018 ዓ.ም የተለያዩ አካላት በተገኙበት በዋና መስሪያ ቤቱ ይፋ አድርጓል። የኢትዮጵያ ሰብብዊ መብቶች ኮሚሽን ዛሬ ይፋ ያደረገው እና ከትናንት ጀምሮ መተግበር የጀመረው እቅድ ከ7.6 ቢሊዮን ብር በላይ የሚፈጅ መሆኑ ተነግሯል፡፡ ይህኛው የስትራቴጂክ እቅድ የተዘጋጀው በ2014 ጀምሮ እስከ 2018 ያገለገለውን እቅድ በማብቃቱ ነው። በተጠናቀቀው ስትራቴጂ እቅድ ከ5,300 በላይ ለሚሆኑ አቤቱታዎች ምላሽ ተሰጥቷል። ከ1,10
3 days ago


በዚህ ዓመት ዝርያቸው ከተዳቀሉ 4.4 ሚሊዮን ከብቶች ውስጥ 2.4 ሚሊዮን የተዳቀሉ ከብቶች ሳይሳካ ቀርቷል ተብሏል።
ሐምሌ 2/2018 በዚህ ዓመት ዝርያቸው ከተዳቀሉ 4.4 ሚሊዮን ከብቶች ውስጥ 2.4 ሚሊዮን የተዳቀሉ ከብቶች ሳይሳካ ቀርቷል ተብሏል። ከተዳቀሉት ውስጥ የተወለዱት ጥጃዎች 2 ሚሊዮን ብቻ ነው ተብሏል፡፡ ይህ የተባለው የግብርና ሚኒስቴር ላለፉት 4 ዓመታት እየተተገበረ ያለውን የሌማት ትሩፋትና የበጀት ዓመቱን የእንስሳትና የዓሣ ምርትን በተመለከተ በተሰጠው መግለጫ ነው። የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር)ባለፉት አመታት 228 የመኖ ማቀነባበርያዎች ወደ ስራ መግባታቸው የጠቀሱ ሲሆን ነገር ግን አሁንም ድረስ የእንስሳት መኖች ችግር አልተቀረፈም ብለዋል። የተሰሩት ማቀነባበርያዎች እና የሚመረተው የመኖ ምርት ከእንስሳቱ ቁጥር ጋር ግን የተመጣጠነ እና በቂ አይደለም ተብሏል። በበጀት ዓመቱ 420 ሺህ ቶን ማር ፣ 250 ሺህ ቶን የዶሮ ስጋ
3 days ago



Facebook
Twitter
Pinterest
Tumblr
Copy Link
Link Copied
Search video...

Now Playing
Mekoya - ሱዳናዊው ሰላይ በኢትዮጵያ ላይ - በእሸቴ አሰፋ
28:44

Now Playing
ለመሆኑ በአንድ በግዙፍ ድርጅት አስተዳደር ምን መሳይ መልክ ሊኖረው ይገባል? #economy #business #finance
07:59

Now Playing
አልሰማንም እንዳትሉ - ከባል አካውንት ለአባት የተላለፈው 400 ሺህ ብር የማን ነው?
04:12

Now Playing
የአሜሪካና ኢራን አዲሱ ውዝግብ - ሰኔ 17/2018 @ShegerFM1021Radio #shegerfm #iranamericawar
07:15

Now Playing
እንደ ቤተሰብ - ዛሬም በኢትዮጵያ 40 ሺህ ህፃናት ከዚህ ችግር ጋር ይወለዳሉ'
57:31

Now Playing
በሳውዲ አረቢያ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ/ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
04:54

Now Playing
አልሰማንም እንዳትሉ - የፖለቲካ ሹም ሽር በፍርድ ቤት ይዳኛልን?
04:21

Now Playing
አሜሪካ ጫፌን የምትነካ ከሆነ ኬብሎቹን ቆርጬ የኢንተርኔት ስርዓቱን አስተጓጉላለው #shegerfm #iranisraelwar
07:32
bottom of page

