top of page
‘’የሕዝብ አደራተ ቀብለው የሚሰርቁ አሉ፤ ነገር ግን ሌብነቱ ተቋማዊ አይደለም’’ ሲሉ ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ።
ሰኔ 30/2018 ‘’የሕዝብ አደራተ ቀብለው የሚሰርቁ አሉ፤ ነገር ግን ሌብነቱ ተቋማዊ አይደለም’’ ሲሉ ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ። ቃለ መሐላ ፈጽመው፣ የመንግሥትንና የሕዝብን አደራ ተቀብለው ከዚህ ምስኪን ሕዝብ የሚሰርቁ ግለሰቦች አሉ፤ ሆኖም ግን በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የታየው ሌብነት ተቋማዊ ሳይሆን በግለሰቦች ደረጃ የሚፈጸም መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተናግረዋል። ሌብነት ጸያፍና ቆሻሻ ተግባር እንደሆነ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፣ ሆኖም ግን ጉዳዩ ሰዎች በየመድረኩ እንደሚናገሩት ቀላል አለመሆኑንና እርምጃ ለመውሰድ በቅድሚያ በተጨባጭና በሕግ የሚያስጠይቅ ነገር መኖር እንዳለበት ጠቁመዋል። በአሁኑ ወቅት ከሌብነት ጋር በተያያዘ በርካታ አሉባልታዎች ይሰማሉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እነዚህ አሉባልታዎች በሁለት መንገድ እንደሚከሰቱ አስረድተዋል። አን
1 hour ago


የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በኢትዮጵያ ኮዲንግ ሰልጣኞች ቁጥር እንዲያድግ ስታደርግ የነበረውን ድጋፍ እንደምትቀጥል ተናገረች።
ሰኔ 30/2018 የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በኢትዮጵያ ኮዲንግ ሰልጣኞች ቁጥር እንዲያድግ ስታደርግ የነበረውን ድጋፍ እንደምትቀጥል ተናገረች። 5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን በኮዲንግ ለማሰልጠን ታቅዶ የነበረው እቅድ ከጊዜው ቀድሞ ተሳክቷል መባሉ ይታወሳል። በዚህ እቅድ ድጋፍ ማድረጓን ያስታወሰችው የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ፕሮጀክቱ ከተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ አስቀድሞ በመሳካቱ የሰልጣኞችን ቁጥር ወደ 7 ሚሊዮን ከፍ ለማድረግ በሁለቱ አገራት አማካኝነት መወሰኑን አስታውሳለች። በዚህም መሰረት ተጨማሪ 2 ሚሊዮን ወጣቶች የኮዲንግ ስልጠና ኦንዲወስዱ ያስችላቸዋል ተብሏል። ይህም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ዲጂታል አቅምን የመገንባት፣ የመንግሥት ሥራዎችን የማዘመን እና የወጣቶችን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ያጠናክረዋል ተብ
2 hours ago


‘’በእስር ላይ ያሉ ሰዎችን ለመፍታት፣ በጫካ እና በውጭ ያሉትን ደግሞ በይቅርታ ለማስገባት ልባችን ሰፊ መሆን ይኖርበታል" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
ሰኔ 30/2018 "የመንግስት ሀላፊዎችና ፖለቲከኞች የሀይማኖት አባቶችንና ትላልቅ ሰዎችን ተጠቅመን በተቻለ መጠን በእስር ላይ ያሉ ሰዎችን ለመፍታት፣ በጫካ እና በውጭ ያሉትን ደግሞ በይቅርታ ለማስገባት ልባችን ሰፊ መሆን ይኖርበታል" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በፓርላማ በነበራቸው ቆይታ ማጠቃለያ ላይ ይህንን ማድረግ የሚያስፈልገው ለኢትዮጵያ ሲባል ነው ብለዋል። “TPLF 'ም ጭምር ቀልብ ከገዛ፣ አእምሮ ከገዛ ለመነጋገርና ሰላም ለማምጣት ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል” ሲሉም አስረድተዋል። “ከሰላም ሙከራ ውጪ ያለው አይጠቅመንም፣የሚያስፈልገን ብልፅግና ላማት ነው” ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ያለፉትን አምስት አመታት በፓርላማ የቆዩ የተፎካካሪ ፖርቲ አባላት ሀሳባቸውን በግልፅ ያቀረቡ እንደራሴዎችንም አመ
2 hours ago


በአርሲው ግጭት የ11 ሰዎች ህይወት ማለፉን ከዚህ ውስጥ 8ቱ የፀጥታ አካላት መሆናቸወን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ፡፡
ሰኔ 30/2018 በአርሲው ግጭት የ11 ሰዎች ህይወት ማለፉን ከዚህ ውስጥ 8ቱ የፀጥታ አካላት መሆናቸወን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ፡፡ በዚህ ግጭት 22 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል ያሉ ሲሆን ከ90 በመቶ በላይ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው መመለሳቸወን አስረድተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ይህንን ያሉት የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሳላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እየሰጡ ባለበት ወቅት ነው። ከሃይማኖት ግጭቶች ጋር በተያያዘ ለተነሳላቸው ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ በቅርቡ በአርሲ የነበረውን ግጭት አንስተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአርሲው ግጭት ምርጫውን ለማደናቀፍ ጥረት ሲያደርጉ ነበር ያሏቸው ኃይሎች በአዲስ አበባ እና በምርጫ አከባቢ ከፍተኛ የፀጥታ ጥበቃ ሲደረግ ስለነበር ወደ
5 hours ago


የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ለስራ ጉብኝት አዲስ አበባ መግባታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ይፋ አድርጓል።
ሰኔ 30/2018 የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ለስራ ጉብኝት አዲስ አበባ መግባታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ይፋ አድርጓል። ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓና አሜሪካ ጉዳይ ዳይሬክተር ጄነራል አምባሳደር መለሰ ዓለም አቀባበል ተደርጎላቸዋል። የቱርኩ አናዶሉ እና የሩሲያ መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት የሰርጌይ ላቭሮቭ የኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት የአፍሪካ ሀገራትን የመጎብኘት እቅዳቸው አካል እና መጀመሪያ ነው። በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታም ዛሬ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጤሞቲዮስ እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ጋር ይመክራሉ ተብሏል። በኢትዮጵያ የሚገነባው የኒውክሊየር ሀይል ማመንጫ ማዕከልን የተመለከተው ጉዳይ አንደኛው መነጋገሪያ ነጥብ ሊሆን ይችላል ብለዋል የመረጃ ምንጮቹ። ካለፈው
6 hours ago


ህገወጥ ደላሎች፤ ሰዎች በህገወጥ መንገድ ጉዞ ለመጀመር ሲያስቡ ወይም ህገወጥ ስደትን እዲያስቡ ከሚያደርጓቸው ከቀዳሚ ምክንያቶች መካከል ይጠቀሳል።
ሰኔ 26/2018 በየአካባቢው ያሉ ህገወጥ ደላሎች፤ ሰዎች በህገወጥ መንገድ ጉዞ ለመጀመር ሲያስቡ ወይም ህገወጥ ስደትን እዲያስቡ ከሚያደርጓቸው ከቀዳሚ ምክንያቶች መካከል ይጠቀሳል። እነዚህ ደላሎች ኢትዮጵያውያኑ በህገ- ወጥ መንገድ ከሀገራቸው እንዲወጡ የተለያዩ ማማለያዎች በመጠቀም በሺዎች የሚቆጠሩትን አስወጥተዋል፡፡ ነገር ግን በዚሁ መንገድ ከሚወጡት ሰዎች መካከል የአውሬ እራት የሚሆኑ እና ካሰቡበት ሳይደርሱ መንገድ ላይ የሚቀሩትም ብዙ ናቸው፡፡ ይህንን ስራ የሚሰሩት ደላሎችም ቢሆኑ ለህግ ሲቀርቡ እንደማይስተዋል የተነገረ ሲሆን ማህበረሰቡ ቢያውቃቸውም ደፈር ብሎ ለህግ አካላት አሳልፎ የመስጠት ልምድ እንደሌለውም በጉዳዩ ላይ የሚሰሩ ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡ ህገወጥ ደላሎች ህግ ፊት ለማቅረብ ማህበረሰቡ እንዲጠቁም ለማድረግ ቢሞክርም ያ ሲሆን እንደማይ
4 days ago


በ2018 ወደ ውጪ ከተላከ ቡና 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን የግብርና ሚ/ር ተናገረ፡፡
ሰኔ 25/2018 በ2018 በጀት ዓመት ወደ ውጪ ከተላከ ቡና 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር ተናገረ፡፡ በጀት ዓመቱ ከቡና ወጪ ንግድ 3 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ለማግኘት የተያዘው ዕቅድ ማሳካቱን ሚኒስቴር መ/ቤቱ አስረድቷል፡፡ በባለፈው በጀት ዓመት ከቡና ወጪ ንግድ 2.65 ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን ሚኒስቴር መ/ቤቱ አስታውሷል፡፡ መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት የቡናውን ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስራዎች እየተሰሩ ነው ያለው የግብርና ሚኒስቴር በዚህም ለውጥ መጥቷል ሲል አስረድቷል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ላይ 5.8 ሚሊዮን ገበሬ በቡና አምራችነት ተሰማርቶ የሚገኝ ሲሆን ገበሬው ከሰራው ስራ ወደ ኪሱ የተጣራ ገቢ የሚያገኘው 40 ከመቶውን ብቻ መባሉ ይታወሳል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….. በረከት አካሉ
5 days ago


የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት በየጊዜው ገበያው በሚፈልገው ልክ እያጠኑ የሚሰጡትን ስልጠና እንደማይከልሱ ጥናት አሳየ፡፡
ሰኔ 25/2018 የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት በየጊዜው ገበያው በሚፈልገው ልክ እያጠኑ የሚሰጡትን ስልጠና እንደማይከልሱ ጥናት አሳየ፡፡ ሰልጣኞቻቸው የወሰዱትን ስልጠና እንዴት ወደ ቢዝነስ መለወጥ እንዳለባቸው የሚያስችል ጥራት ያለው ስልጠና የማይሰጡም አሉ ተብሏል፡፡ አቶ ሀብታሙ አለማየሁ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የመንግስት ቴክኒክና ሞያ ማሰልጠኛ ተቋማት ውስጥ ያለው የስልጠና አካሄድን በተመለከተ ጥናት አድርገዋል፡፡ በዚህ ጥናታቸው 14 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ያሉ የቴክኒክና ሞያ ስልጠና ተቋማትን የተመለከቱ ሲሆን በተቋማቱ ውስጥ ወጥ የሆነ አሰራር እየተተገበረ አይደለም ይላሉ፡፡ አንዳንድ ማሰልጠኛ ተቋማት የሚሰጡት ስልጠና ወቅቱ በምን መንገድ ይፈልገዋል የሚለውን በትክክል አያጠኑም ሲሉም የስረዳሉ፡፡ ይህ ዘርፍ በየጊዜው የሚሰጡ ስ
5 days ago


ተሻሽሎ ስራ ላይ መዋል ከጀመረ አንድ ዓመት ያስቆጠረው የፌዴራል ገቢ ግብር አዋጅ ነባራዊ ሁኔታዎችን ያላገናዘቡ አንዳንድ ጥብቅ ድንጋጌዎች ያሉበት ነው ተባለ።
ሰኔ 25/2018 ተሻሽሎ ስራ ላይ መዋል ከጀመረ አንድ ዓመት ያስቆጠረው የፌዴራል ገቢ ግብር አዋጅ ነባራዊ ሁኔታዎችን ያላገናዘቡ አንዳንድ ጥብቅ ድንጋጌዎች ያሉበት ነው ተባለ። ድርጅቶች ቢከስሩ እንኳን ከዓመታዊ ሽያጫቸው 2.5 በመቶ ግብር መክፈል አለባቸው የሚለው አንዱ ድንጋጌ መሆኑ ተጠቅሷል። የድንጋጌው መነሻ ነጋዴዎች እያተረፉም ጭምር ከስረናል በሚል ያሳውቃሉ ከሚል እንደሆነ ተነግሯል። በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል በሚካሄደው ውይይት ድንጋጌው በግሉ ዘርፍ ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ እንደሚገኝ ትኩረቱን በታክስ ዙርያ አድርጎ ተነስቷል። በተለይ ከፍተኛ ሽያጭ ያላቸው ግን ደግሞ የትርፍ ህዳጋቸው አነስተኛ የሆኑ እንደ ማኑፋክቸሪንግ እና ጅምላ ንግድ ያሉ ዘርፎች እየተጎዱ ነው። በአንድ የግብይት ወቅት ከ50 ሺህ ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ የተከፈለን ወጪ ከታክስ
5 days ago



Facebook
Twitter
Pinterest
Tumblr
Copy Link
Link Copied
Search video...

Now Playing
Mekoya - ሱዳናዊው ሰላይ በኢትዮጵያ ላይ - በእሸቴ አሰፋ
28:44

Now Playing
ለመሆኑ በአንድ በግዙፍ ድርጅት አስተዳደር ምን መሳይ መልክ ሊኖረው ይገባል? #economy #business #finance
07:59

Now Playing
አልሰማንም እንዳትሉ - ከባል አካውንት ለአባት የተላለፈው 400 ሺህ ብር የማን ነው?
04:12

Now Playing
የአሜሪካና ኢራን አዲሱ ውዝግብ - ሰኔ 17/2018 @ShegerFM1021Radio #shegerfm #iranamericawar
07:15

Now Playing
እንደ ቤተሰብ - ዛሬም በኢትዮጵያ 40 ሺህ ህፃናት ከዚህ ችግር ጋር ይወለዳሉ'
57:31

Now Playing
በሳውዲ አረቢያ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ/ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
04:54

Now Playing
አልሰማንም እንዳትሉ - የፖለቲካ ሹም ሽር በፍርድ ቤት ይዳኛልን?
04:21

Now Playing
አሜሪካ ጫፌን የምትነካ ከሆነ ኬብሎቹን ቆርጬ የኢንተርኔት ስርዓቱን አስተጓጉላለው #shegerfm #iranisraelwar
07:32
bottom of page

