top of page


የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ለከፍተኛ ት/ት ተቋማት የሚሰጠውን ሽልማት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ማሸነፉ ተነገረ፡፡
ሐምሌ 15 2018 የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ለከፍተኛ ት/ት ተቋማት የሚሰጠውን ሽልማት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ማሸነፉ ተነገረ፡፡ 3 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት በሚያስገኘው በዚህ ፕሮግራም የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ጨምሮ 5 የአፍሪካ ዩኒቨርስቲዎች ማሸነፋቸው ተነግሯል፡፡ ከዩኒቨርስቲው ገፅ ያገኘነው መረጃ እንደሚያሳየው የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን የ3 ሚሊዮን ዶላር ሽልማቱ "African Higher education for transformation prize" በሚል ፕሮግራም ስር የሚሰጥ ሲሆን ገንዘቡም የትምህርት እድል ፣ ፈጠራ እና ምርምርን ለማጠናከር ተግባር የሚውል ነው ተብሏል፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲም በምርምር እና ፈጠራ ባሳየው ልህቀት መሸለሙ ተነግሯል፡፡ የአካዳሚው የምርምር ስራዎች በሀገር ደረጃ ቅድሚያ ከተሰጠው አካሄድ ጋር የተስማማ መሆኑ ፣ ሳ
7 hours ago
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡
ሐምሌ 15 2018 በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡ ከጥቂት አመታት በፊት የህፃናት ማቆያዎቹ ጥቂት ነበሩ ያለው የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አሁን ላይ ከፍተኛ መሻሻሎች ታይተውበታል ብሏል፡፡ ጥናቱም በግል እና በመንግስት ማቆያዎች ላይ ያሉ ለውጦችን እና መሻሻሎችን ለማየት ሞክሯል የተባለ ሲሆን በመንግስት የሚሰሩት ማዕከላት የስራ ቦታ እና የህዝብ ማቆያዎች ናቸው ብሏል፡፡ በዚህም የህዝብ የሚባሉት ማቆያዎችን መንግስት ከምግብ ጀምሮ መሰረተ ልማቶችን እና ሌሎች ለህፃናቱ የሚያስፈልጉ ነገሮችን አሟልቶ የሚያቀርብ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ሌላኛው በመንግስት ተቋማት ለሚሰሩ ሰራተኞች ልጆች የተዘጋጀው የስራ ቦታ የህፃናት ማቆያዎች ነው፡፡ የጥናቱ ውጤት የሚያሳየውም የተ
8 hours ago


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግል ትምህርት ቤቶችን የክፍያ ጭማሪ ጉዳይ በተመለከተ አምና ያወጣው ደንብ ትምህርት ቤቶች እንደ ደረጃቸው እስከ 68 በመቶ የዋጋ ጭማሪ እንዲያደርጉ ፈቅዷል።
ሐምሌ 15 2018 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግል ትምህርት ቤቶችን የክፍያ ጭማሪ ጉዳይ በተመለከተ አምና ያወጣው ደንብ ትምህርት ቤቶች እንደ ደረጃቸው እስከ 68 በመቶ የዋጋ ጭማሪ እንዲያደርጉ ፈቅዷል። የዋጋ ጭማሪውም ለሁለት ዓመት የሚያገለግል ቢሆንም ለሁለተኛ ጊዜ ጭማሪ ያደረጉና የተጋነነ ክፍያ የሚጠይቁ እንዳሉ እየተሰማ ነው። ይህ በፍፁም ህጋዊ አይደለምም ተብሏል። ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ... ፋሲካ ሙሉወርቅ
8 hours ago


የነዳጅ የሚያጓጉዙ ቦቴ ባለንብረቶች በየሁለት አመቱ የትራንስፖርት ታሪፍ እንዲሻሻልላቸው ህግ ቢኖርም ስራ ላይ እየዋለ ባለመሆኑ የባንክ እዳ መክፈል አልቻልንም አሉ፡፡
ሐምሌ 15 2018 የነዳጅ የሚያጓጉዙ ቦቴ ባለንብረቶች በየሁለት አመቱ የትራንስፖርት ታሪፍ እንዲሻሻልላቸው ህግ ቢኖርም ስራ ላይ እየዋለ ባለመሆኑ የባንክ እዳ መክፈል አልቻልንም አሉ፡፡ የመኪና መለዋወጫ ውድነትና ሌላም ጫና ቢኖርብንም በሚገባን ልክ ክፍያ እያገኘን ባለመሆኑ ከስራው ለመውጣት እየተገደድን ነው ይላሉ፡፡ የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ማህበር የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን በተገኘበት በጉዳዩ ላይ ውይይት አድርጓል፡፡ በዘርፉ ላይ ጥናት አድርጋቸው አምጡ ብንባልም ከአንዴም ሁለቴ ጥናት አድርገን ለሚመለከተው አካል ብንሰጥም ምንም የተለወጠም የተሻሻለው ነገር የለም ሲሉ ያስረዳሉ፡፡ የባንክ እዳ የኢንሹራንስ የመኪና መለዋወጫና የአሽከርካሪ ክፍያ እና ሌላም ሌላም ተደማምሮ ኪሳራ ውስጥ ገብተናል መንግስት ሊመለከተን ይገባል ሲሉ ባለ
8 hours ago
በአዲስ አበባ ደረሰኝ ያልቆረጡ ከ4ሺህ 100 በላይ የጭነት መኪኖች ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ ተቀጡ፡፡
ሐምሌ 15 2018 በአዲስ አበባ ደረሰኝ ያልቆረጡ ከ4ሺህ 100 በላይ የጭነት መኪኖች ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ ተቀጡ፡፡ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በከተማዋ ጭነት ይዘው የሚገቡና የሚወጡ ተሸከርካሪዎች ለጫኑት እቃ በእለቱ የተቆረጠ ደረሰኝ መያዛቸውን እየተከታተለ ካለፈው ዓመት ጀምሮ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን ተናግሯል፡፡ ይህንን መቆጣጠር ያስፈለገውም ነጋዴዎች ደረሰኝ ላለመቁረጥ እቃዎችን በየመጋዘኑ በማከማቸት ሽያጩን ከዚያው ከመጋዘን እያደረጉ በመሆኑ ነው የሚለው ቢሮው፤ እየተገባደደ ባለው ዓመትም ቁጥጥሩን ጠንከር አድርጎ መቀጠሉን ነግሮናል፡፡ በገቢ ግብር ህጉ መሰረት ደረሰኝ ያልተቆረጠበትን እቃ ጭኖ የተገኘ ነጋዴ ለያዘው እቃ ደረሰኝ እንዲቆርጥ እንዲሁም ደረሰኝ ባለመቁረጥ የሚጣልበትን የ100 ሺህ ብር ቅጣት እንዲከፍል ይደረጋል፡፡ ቢሮው ባለፉት
9 hours ago












bottom of page
_edited.jpg)












