top of page


#ሸገር_ትንታኔ
ሩሲያ የግዛት አካሎቼ ናቸው የምትላቸው የኩሪል ደሴቶች ጉዳይ ጃፓንን ከ80 አመታት በላይ ሲቆጭ ሲያንገበግባት ኖሯል፡፡ ሰሞኑን የሩሲያው ፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን በኩል ደሴቶች ጉብኝት ማድረጋቸው ጃፓንን ክፉኛ አንጨርጭሯታል፡፡ የኩሪል ውዝግብ ዳግም እየተጋጋለ ነው፡፡ ዝርዝሩን የኔነህ ከበደ አዘጋጅቶታል
16 hours ago


በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ሽፋኑ 63 በመቶ ገደማ ደርሷል፡፡
ነሐሴ 9 2018 በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ሽፋኑ 63 በመቶ ገደማ ደርሷል፡፡ ይሁን እንጂ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ያላቸው ሰዎች 6 ሚሊዮን ብቻ ናቸው፡፡ ህዝቡ በነፍስ ወከፍ የሚያገኘው ኢነርጂ መጠንም ከሰሀራ በስተደቡብ ካሉት ሀገራት አኳያ ሲታይም ከእጥፍ በላይ ያነሰ ነው፡፡ ይህንን የኤሌክትሪክ ሀይል ችግርን ሙሉ ለሙሉ ለመፍታት ፣ ሁሉንም የሀገሪቱ ህዝብ ከኤሌክትሪክ ጋር ለማገናኘት 30.65 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል፡፡ ታዲያ ይህ ሁሉ ሀብት ከየት ይመጣል ? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ.... ቴዎድሮስ ወርቁ ጠይቋል
16 hours ago


ያልሰራሁትን ፣ ያላተረፍኩትን ግብር ክፈል ተባልኩ የሚሉ ነጋዴዎች መንግስት ይመልከተን ሲሉ ይሰማሉ።
ነሐሴ 9 2018 ያልሰራሁትን ፣ ያላተረፍኩትን ግብር ክፈል ተባልኩ የሚሉ ነጋዴዎች መንግስት ይመልከተን ሲሉ ይሰማሉ። መንግስት በበኩሉ የሚሰበስበው ግብር አሁንም ዝቅተኛ መሆኑን ያስረዳል፡፡ የመንግስትም ገቢ እንዲጨምር ፣ ነጋዴዎችም ያላገኙትን ክፈሉ እንዳይባሉ ማድረግ የሚቻለው እንዴት ነው? ፍቅሩ አምባቸው
17 hours ago


ሌብነት ወይንም ሙስና አገልግሎት ሰጪንና ተቀባይን የሚያግባባ ብቸኛ ቋንቋ የሆነ መስሏል፡፡
ነሐሴ 9 2018 ሌብነት ወይንም ሙስና አገልግሎት ሰጪንና ተቀባይን የሚያግባባ ብቸኛ ቋንቋ የሆነ መስሏል፡፡ ህብረተሰቡም መሬት ፣ ንግድ ፣ ገቢዎች ፣ ጉምሩክ ፣ ግንባታ ሙስና የከፋባቸው ተቋማት ናቸው ብሎ እንደሚያምን ጥናት አሳይቷል፡፡ ሌቦችን ፣ ሙሰኞችን ለመቅጣት ግን ህግ አለ፡፡ ሙስናንን ለመከላከል በሚል የተቋቋሙ ተቋማት አሉ፡፡ መንግስትም ሌቦችን እየቀጣሁ ነው ፣ የምታገሰው ጉዳይ አይደለም ይላል፡፡ ግን ሌብነት ቀጥሏል፡፡ ለምን? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ..... ያሬድ እንዳሻው
17 hours ago
የነሐሴ 9 የውጪ ሀገር ወሬዎች
#ኮንጎ የኮንጎ ኪንሻሣው የኢቦላ ወረርሽኝ አድማሱን እያሰፋ ነው ተባለ፡፡ ወረርሽኙ ወደ ተጨማሪ ግዛትም መዛመቱን የአፍሪካ የበሽታዎች መከላከያ እና መቆጣጠሪያ /አፍሪካ CDC/ መረጃ ማሳየቱን አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡ በኮንጎ የኢቦላ ወረርሽኝ ያዳረሳቸው ግዛቶች ብዛት 6 ደርሷል፡፡ ኢቱሪ ወረርሽኙ ከፍተኛ ጫና ያሳደረባት ግዛት ነች፡፡ ወረርሽኙ መቀስቀሱ ከተነገረ 3 ወር ሆኖታል፡፡ እስከ ትናንትም የገደላቸው ሰዎች ብዛት 2 ሺህ 100 ደርሷል፡፡ የኮንጎው ኢቦላ በከፍተኛ የመዛመት ፍጥነት ላይ ነው፡፡ በታሪክም ታላቁ የኢቦላ ወረርሽኝ ሊሆን የሚችልበት እድል የሰፋ ነው ተብሏል፡፡ #ሩሲያ የሩሲያው ፕሬዘዳንት ቭለድሚር ፑቲን በቀጠናዊ የፀጥታ እና ደህንነት ጉዳይ ከሰሜን ኮሪያ ጋር በትብብር እንሰራለን አሉ፡፡ ፑቲን ከሰሜን ኮሪያ ጋር ቀጠናዊ የፀጥታ እና የ
17 hours ago












bottom of page
_edited.jpg)










