top of page
ዋና ገጽ
ወሬ
መሰናዶዎች
የጊዜ ሰሌዳ
ከእኛ ጋር ያስተዋውቁ
ስለ እኛ
መገናኛችን
More
Use tab to navigate through the menu items.
የተከለከሉ ፕላስቲኮችን ሲያከፋፍሉ የተገኙ 46 የምርት አከፋፋዮች እንዲዘጉ መደረጉ ተሰማ።
ሐምሌ 18 2018 የተከለከሉ ፕላስቲኮችን ሲያከፋፍሉ የተገኙ 46 የምርት አከፋፋዮች እንዲዘጉ መደረጉ ተሰማ። ይህንን የሰማነው የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዛሬ ባስጀመረው 3ኛ ዙር “ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ “ የከተማ አቀፍ መድረክ ላይ ነው። ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በፕላስቲክ ብክለት መከላከል ቁጥጥር ስራ 150 ልዩ ልዩ አካላትን ቀጥቼ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ ከቅጣት ገቢ መሰብሰቡ ችያለው ሲል ተናግሯል። በሌላ በኩል በወንዝ ብክለት መከላከል ቁጥጥር ላይ ሰፊ ስራ ሰርቻለሁ ያለው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በተጠናቀቀው በጀት አመት ፍሳሻቸውን ወደ ወንዝ በለቀቁ ተቋማት ላይ ከተወሰደ እርምጃ ከ110 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ ተነግሯል። የፍሳሽ ብክለት ያስከትላሉ የተባሉ 12ሺህ ግለሰብ እና ተቋማት ላይ የመለየት ስራ መሰራቱም ተነግሯል።
7 hours ago
የዚህ የስደት ነገር ማስታገሻው ምን ይሆን?
ሐምሌ 18 2018 የስደት ነገር የማያቋርጥ ሆነ፡፡ የውጭ ሀገር ጉዞ በህጋዊ መንገድ እንዲከናወን ስራ ቢጀመርም አሁንም ህገ-ወጡን መንገድ እየተከተሉ ችግር ላይ የሚወድቁት ዜጎች ቁጥር እንደበዛ ነው፡፡ ኑሮ አቀበት የሆነበት ፣ የግጭት ስጋት ያስጨነቀው የደላሎች ማግባቢያ ያመላለጡ ሁሉ ህገ-ወጡን መንገድ እየተከተሉ ለአደጋ እየተጋለጡ ነው፡፡ የዚህ የስደት ነገር ማስታገሻው ምን ይሆን? ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ... ፋሲካ ሙሉወርቅ
7 hours ago
የሐምሌ 18 የውጪ ሀገር ወሬዎች
#ስፔን በስፔኗ ርዕሰ ከተማ ማድሪድ አቅረቢያ ነዋሪዎች በመዛመት ላይ በሚገኘው ከባድ የሰደድ እሳት ምክንያት ለቅቀው እንደወጡ ታዘዙ፡፡ የማድሪድ ምዕራባዊ ክፍል አቅራቢያ የሰደድ እሳቱ በጣሙን ያየለበት እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡ እስከ ትናንት ምሽትም ከ19 ሺህ በላይ ሰዎች ለቀው መውጣታቸው ተጠቅሷል፡፡ በስፔን ወቅታዊ የሰደድ እሳት ምክንያት በአገሪቱ ብሔራዊ የአደጋ ጊዜ መታወጁ ታውቋል፡፡ ፈረንሳይም በሰደድ እሳት መዛመት እየተፈተነች ነው፡፡ የሰደድ እሳቱ በሁለቱም አገሮች ከ220 ሺህ በላይ ሰዎችን የመኖሪያቸው አፈናቅሏል ተብሏል፡፡ በአውሮፓ የሰደድ እሳቱ ለመባባሱ ወቅታዊው የሙቀት ማዕበል በዋና ምክንያትነት እየቀረበ ነው፡፡ #አሜሪካ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቻይና እና ሩሲያ ለኢራን የጦር መሳሪያ እንዳይሰጡም ሆነ እንዳይሸጡ በብርቱ ማ
7 hours ago
በኮንጎ ኪንሻሣ በፍጥነት በመዛመት ላይ የሚገኘውን የኢቦላ ወረርሽኝ ለመከላከል የታለመ የሙከራ ክትባት ለአንድ ፈቃደኛ የሙከራው ተሳታፊ መሰጠቱ ተሰማ፡፡
ሐምሌ 18 2018 በኮንጎ ኪንሻሣ በፍጥነት በመዛመት ላይ የሚገኘውን የኢቦላ ወረርሽኝ ለመከላከል የታለመ የሙከራ ክትባት ለአንድ ፈቃደኛ የሙከራው ተሳታፊ መሰጠቱ ተሰማ፡፡ የሙከራው የመጀመሪያው ተሳታፊ የእንግሊዙ ኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ ፈቃደኛ ተማሪ እንደሆነ አለም አቀፉ የክትባት ጥምረት ጋቢ በድረ ገፁ ባሰፈረው መረጃ እወቁልኝ ብሏል፡፡ የሙከራ ክትባቱ የኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ የጤና ልሒቃን ውጤት መሆኑ ታውቋል፡፡ የሙከራው ውጤታማነት ለማረጋገጥ ተጨማሪ 49 ፈቃደኞች ይመለመላሉ ተብሏል፡፡ ከተከሰተ ከ2 ወራት በላይ ያስቆጠረው የኮንጎ ኪንሻሣው የቡንዲ ቡጉዮ የኢቦላ በሽታ ከ1 ሺህ በላይ ሰዎችን መግደሉ ተረጋግጧል፡፡ ከ2 ሺህ 500 የሚልቁ ሰዎች ደግሞ በበሽታው እንደተያዙ ተጠቅሷል፡፡ ዩንጋዳ የወረርሽኙን መዛመት በፍጥነት መቆጣጠሯ ተነግሮላታል፡፡ የአ
7 hours ago
ኢትዮጵያኖች አብሮ የሚያኖራቸውን መላና ሥርዓት ተስማምተው ለማበጀት እየሞከሩ ነው፡፡
ሐምሌ 18 2018 ኢትዮጵያኖች አብሮ የሚያኖራቸውን መላና ሥርዓት ተስማምተው ለማበጀት እየሞከሩ ነው፡፡ 4 ሺህ የሚሆኑት ዜጎች በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ለመምከር የሚያቀርቧቸው ሀሳቦች የተለያዩ ምናልባትም ፅንፍ የሚዳረሱ መሆናቸው የሚገመት ነው፡፡ የራቀውን አቅርበው የተወጠረውን አርግበው ውጤት ላይ ለመድረሱ የጀመሩት ሂደት እንዴት ከርሟል? ምንታምር ፀጋው ከተካፋዮቹ ውስጥ አነጋግራለች፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ...
8 hours ago
1
2
3
4
5
የሐምሌ 17 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች
1 day ago
የሐምሌ 16 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች
2 days ago
የሐምሌ 15 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች
3 days ago
1/98
የተከለከሉ ፕላስቲኮችን ሲያከፋፍሉ የተገኙ 46 የምርት አከፋፋዮች እንዲዘጉ መደረጉ ተሰማ።
7 hours ago
የዚህ የስደት ነገር ማስታገሻው ምን ይሆን?
7 hours ago
የሐምሌ 18 የውጪ ሀገር ወሬዎች
7 hours ago
1/1372
በኢትዮጵያ በቆዳና ሌጦ ዘርፍ ሲሰሩ ከነበሩ 31 ፋብሪካዎች ውስጥ አሁን በስራ ላይ ያሉት ሰባት ብቻ ናቸው ተባለ።
2 days ago
በኢትዮጵያ የጭነት ማስተላለፍ ስራ ለውጭ ባለሃብቶች ሙሉ በሙሉ ክፍት እንዲሆን ተወስኗል።
Jul 1
የሜትር ታክሲ አገልግሎት አቅራቢው ''ያንጎ'' ከአዲስ አበባ ውጪ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀዋሳ ከተማ ሥራ በመጀመሩ ተሰማ።
Jun 8
1/90
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Load More
bottom of page