top of page
በሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ የተቋቋመው አጣሪ ቡድን በምስራቅ አርሲ ዞን ስላለው ሁኔታ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት ይፋ አደረገ፡፡
ህዳር 1 2018 በኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ የተቋቋመው አጣሪ ቡድን በምስራቅ አርሲ ዞን ስላለው ሁኔታ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት ይፋ አደረገ፡፡ ከየቤተ እምነቱ የተውጣጣው አጣሪ ኮሚቴ ግድያው እምነትን፣ ዘርን፣ ፆታንና እድሜን ያልለየ መሆኑን ማረጋገጡን ተናግሯል፡፡ የማጣራት ስራው የተከወነባቸው በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ጉና ወረዳ፣ ሲርካ ወረዳ፣ ቁልቁሉ አቤ ወረዳና መርቲ ወረዳዎች ናቸው ተብሏል፡፡ የአጣሪ ኮሚቴው ዋና ሰብሳቢ መላከ ሰላም ዳዊት ያሬድ በሪፖርታቸው በእነዚህ ወረዳዎች በንጹሃን ሰዎች ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ ግድያና እገታ መፈፀሙን ማረጋገጣቸውን ጠቅሰው፤ ከአካባቢው ነዋሪዎች በተገኘው መረጃ የድርጊቱ ፈፃሚዎች በምሽት የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ብድኖች ናቸው ብለዋል፡፡ ኮሚቴው ከሄደባቸው ወረዳዎች መካከል አንዱ በሆነው በአርሲ ዞን ጉና
28 minutes ago


በ4 ዓመታት በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ይኖሩ የነበሩ ከ500,000 በላይ ኢትዮጵያዊያን መመለሳቸውን ተነገረ
ህዳር 1 2018 ባለፉት 4 ዓመታት በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ከ500,000 በላይ ኢትዮጵያዊያን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ፡፡ ኢትዮጵያዊያኑ በተለያዩ የመካከለኛ ምሥራቅ፣ የአፍሪካ እና እንደ በምይማር ያሉ የእስያ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ መሆናቸወን ሚኒስቴር መ/ቤቱ ጠቅሷል፡፡ ይህ ሥራ መቀጠሉ የተነገረ ሲሆን በሳውዲ አረቢያ በተለያዩ እስር ቤቶችና ማቆያ ማዕከላት የሚገኙ ሰዎች ከመስከረም 05 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከ17,000 በላይ ኢትዮጵያዊያን መመለስ ተችላል ተብሏል። በአሁኑ ወቅትም ከሳውዲ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን የመመለሱ ሥራ ቀጥሏል ሲልም አስረድቷል። በተመሳሳይ በየመን በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ 36 ሰዎች ወደ ሀገራ
1 hour ago


ህዳር 1 2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
#ስሎቫኪያ በአውሮፓ አገሮች ታግዶ የሚገኘው የሩሲያ ገንዘብ ለዩክሬይን በብድር የመሰጠቱ ሀሳብ ከስሎቫኪያ በኩል ጠንካራ ተቃውሞ ገጠመው፡፡ በአውሮፓ ህብረት ዘንድ ታግዶ ከሚገኘው የሩሲያ ገንዘብ 140 ቢሊዮን ዩሮው ለዩክሬይን የጦር መደገፊያ በብድር እንዲሰጣት ምክር ከተያዘ መቆየቱን አናዶሉ አስታውሷል፡፡ የስሎቫኪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሮበርት ፊኮ ግን እኛ የዚህ ውጥን አካል አይደለንም ማለታቸው ተሰምቷል፡፡ ከዚህ ይልቅ ለዩክሬይኑ ጦርነት ማብቃት ጥረቱ ቢበረታ ይሻላል ብለዋል ፊኮ፡፡ የታገደው የሩሲያ ገንዘብ ለዩክሬይን የጦር መደገፊያነት በብድር በሚሰጥበት መላ በአውሮፓ ህብረት መድረክ በመጪው ወር በታላቁ እንደሚመከርበት ታውቋል፡፡ ገንዘቡ ለዩክሬይን በብድር እንዲፈቀድላት የሁሉንም የህብረቱ አባል አገሮች ሙሉ ስምምነት እንደሚሻ ተ
2 hours ago


ዲጂታል ስርዓት እና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት)
ህዳር 1 2018 #ጉዳያችን - ዲጂታል ስርዓት እና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት) ሀገራት ወደ ዲጂታል መንገድ በሚያደርጉት ጉዞ የዛሬውን ብቻ ሳይሆን እንዳስፈላጊነቱ የቀደሙ በወረቀት ያሉ መረጃዎችንም ወደ ዲጂታል ስርዓት ያስገባሉ። ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ ምን ማድረግ ይኖርባታል? የኤ.አይ.ቲ ቴክኖሎጂ ስራ አስኪያጅና የቴክኖሎጂ ባለሙያው አቶ እስራኤል ብሩክ በጉዳዩ ላይ የሰጡንን ማብራሪያ ያድምጡ….. የቀደመው ተያያዥ ዘገባን ለማድመጥ …. https://tinyurl.com/uernphkz ቴዎድሮስ ወርቁ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 👇👇👇 🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/ 🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478 🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1 📘Fa
3 hours ago


ምርቶች በወጣላቸው ደረጃ መሰረት ተዘጋጅተው ለገበያ መዋላቸውን ለማረጋገጥ የሚደረገው የቁጥጥር የላላ ሆኖ ቀጥሏል፡፡
ህዳር 1 2018 ምርቶች በወጣላቸው ደረጃ መሰረት ተዘጋጅተው ለገበያ መዋላቸውን ለማረጋገጥ የሚደረገው የቁጥጥር የላላ ሆኖ ቀጥሏል፡፡ መረጃዎችን የሚያጸድቀው ቦርድ የሚወጡ ደረጃዎችን አተገባበር በየጊዜው እንዲከታተል የሚያስችል አዲስ አሰራር ሊከተል እንደሆነም ሠምተናል፡፡ በሌላ በኩል ለሁለት ተጨማሪ ሀገር በቀል ምግብ ነክ ምርቶች በኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንስቲትዩት ደረጃ መዘጋጀቱ ተነግሯል፡፡ የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንስቲትዩት ምግብ ነክ ለሆኑ ስድስት አገር በቀል ምርቶች ደረጃ ማዘጋጀቱ ይታወሳል፡፡ ሽሮ፣ በርበሬ፣ ቆሎ፣ በሶ፣ አረቄ እና ጠጅ ደረጃው የተዘጋጀላቸው ምርቶች ናቸው፡፡ ለምርቶቹ የወጣውን ደረጃ ህብረተሰቡ እንዲያውቀው እንዲሁም የተመረጡ የጥቃቅን እና አነስተኛ ተቋማት ደረጃውን መሰረት አድርገው ምርቱን እንዲያዘጋጁ መደረጉን በኢንስቲት
3 hours ago


ህዳር 1 2018 - በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው መታየት የነበረባቸው አዎንታዊ ለውጦች ለምን መታየት አልቻሉም?
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ሙሉ በሙሉ ስራ ላይ የዋለው ካለፈው መስከረም ወር ጀምሮ ነው፡፡ ይህን ተከትሎም ከመስከረም በኋላ የብር የመግዛት አቅም ይጠናከራል የውጪ ምንዛሪ ግኝቱ ከፍ ይላል የሚሉ እና ሌሎችም የተጠበቁ ለውጦች ነበሩ፡፡ መሬት ላይ ሲታይ ግን በተቃራኒ ሆነው የተገኙም አሉ፡፡ ምክንያቱ ምንድን ነው? የብር የመግዛት አቅም መጠናከር ሲኖርበት ከዕለት ዕለት አሳሳቢ በሚባል ደረጃ እያሽቆለቆለ መሆኑን በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው የዘርፉ ባለሞያ ጠቅሰዋል፡፡ ለዚህም አንደኛው ምክንያት የውጪ ምንዛሪ ገበያው ላይ ያለው ችግር መሆኑን አንስተዋል፡፡ የውጪ ምንዛሪውን ገበያ ከሚያውኩት መካከል የባንኮች አሰራር ግልፅ አለመሆን፣ የጥቁር ገበያው ጠንካራ ሆኖ መቀጠልና ሌሎችም ይገኙበታል ብለዋል፡፡ በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው መታየት የነበረባቸው፤ አዎንታዊ
3 hours ago


የሀይማኖት ምልክቶችን የሚያንቋሽሹ ሰዎች በህግ እንዲጠየቁ ካልተደረገ ለግጭት መንስኤ ሊሆኑ እንደሚችሉ ተነገረ
ጥቅምት 28 2018 የሀይማኖት ምልክቶችን የሚያንቋሽሹ እና ንፁሀን የሚገድሉ ሰዎች በህግ እንዲጠየቁ ካልተደረገ ለከፋ ግጭት መንስኤ ሊሆኑ እንደሚችሉ ተነገረ። በአደባባይ፣ በጎዳናዎች የሚደረጉ ስብከቶችን ጨምሮ የሀይማኖት ዶግማዎችን የሚያንቋሽሹ እና የሚያነውሩ አካላትን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ የሚረዳ ስርዓት ለማበጀት ወይይት ተጀምሯል ተብሏል። የአዲስ አበባ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ፣ የከተማዋ ኮሚኒኬሽን ጉዳይዎች ቢሮ፣ የሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ከሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን የስራ ሃላፊዎች ጋር በመሆን በሰላም ጉዳይ ላይ በትናንትናው እለት ተወያይተዋል። አንድ የውይይቱ ተሳታፊ ህጻናትን ጨምሮ ንጹሃን እየተገደሉ ነው፡፡ ይህን ወንጅል የሚፈጽሙ አካላት ለምንድነው በህግ የማይጠየቁት፣ መቼስ ነው የሚቆመው ሲሉ ጠይቀዋል። ንጹሃን እየተገደሉ እስከመቼ
3 days ago


አዋሽ ባንክ የመስመር ዲጂታል የብድር አገልግሎት ይፋ ማድረጉን ተናገረ።
ጥቅምት 28 2018 አዋሽ ባንክ የመስመር ዲጂታል የብድር አገልግሎት ይፋ ማድረጉን ተናገረ። ባንኩ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በዲጂታል መተግበሪያ በኩል የብድር አገልግሎት ማቅረብ የሚያስችል '"መስመር ዲጂታል የብድር አገልግሎት" በአዋሽ ብር ፕሮ መተግበሪያ በኩል አቅርቧል ተብሏል። ባንኩ ይህንን መተግበሪያ ይፋ ያደረገው ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን እና ከፈርስት ኮንሰልት ጋር በመተባበር እንደሆነ ተናግሯል። አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በሙሉ አቅማቸው እንዳይወጡ እና ስራዎችን እንዳይከውኑ ከሚያደርጓቸው ችግሮች መካከል የብድር አገልግሎት አለማግኘት አንዱ መሆኑን የአዋሽ ባንክ ሲኒየር ችፍ ማርኬቲንግ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ዮሀንስ መርጋ አንስተዋል። ለዚህ ችግር መፍትሄ ለመስጠት ደግሞ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የብድር አገልግ
3 days ago


ጥቅምት 27 2018 - ''በሀይማኖት ሽፋን ግጭት ለመቀስቀስ የሚንቀሳቀሱ አካላትን ከድርጊታችሁ ታቀቡ ልንላቸው ይገባል'' የአዲስ አበባ ከተማ የኮሙኒኬሽን ቢሮ
በሀይማኖት ሽፋን ስም ግጭት ለመቀስቀስ የሚንቀሳቀሱ አካላትን "ከድርጊታችሁ ታቀቡ" ልንላቸው ይገባል ሲል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮሙኒኬሽን ቢሮ ተናገረ፡፡ የአዲስ አበባ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ፣ የከተማዋ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ከሃይማኖት ሚዲያዎች የስራ ሃላፊዎች ጋር በመሆን በሰላም ጉዳይ ላይ ተወያይተዋል። በውይይቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የከተማዋ የኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ዘውዱ ከበደ ሚዲያ ሰላምን ለመስበክ፣ የእርስ በእርስ ግንኙነትን ለማጠናከር ድርሻው ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡ ይሁንና አንዳንድ ግለሰቦች ሃይማኖትን ሽፋን በማድረግ በማህበረሰብ መካከል ግጭት እና ቅራኔ ለመፍጠር እንደሚሰሩ ተናግረው እነዚህን አካላት በቃ ልንላቸው ይገባል ሲሉ አስረድተዋል፡፡ የአዲስ አበባ ሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጻሀፊ መጋቢ ታምራት አበ
4 days ago



Facebook
Twitter
Pinterest
Tumblr
Copy Link
Link Copied
Search video...

Now Playing
የነፃነትን ዋጋ የማናውቅ ነፃ ሰዎች! ዓለማየሁ ዋሴ እሸቴ /ተራኪ አበበ ባልቻ #ShegerShelf @ShegerFM1021Radio
14:51

Now Playing
ከሰሞኑ ታሽገው የሚታዩት የንግድ ቤቶች /
05:08

Now Playing
የጤና መድህን አባል መሆን ግዴታ ወይስ ውዴታ?
04:10

Now Playing
ከህዳሴው ግድብ ጀርባ እልህ አስጨራሽ ድርድሮች Eng. Sileshi Bekele
06:20

Now Playing
Sheger Cafe - ሀገራዊ ምክክር ላይ! ዶ/ር ተካልኝ ወልደማርያም እና ዶ/ር ዮናስ አሽኔ/ 19ኛ ሳምንት @ShegerFM1021Radio
57:29

Now Playing
Sheger Cafe - በሐገራችን እየተካሄደ ስላለው የሰላም ግንባታ! መዓዛ ብሩ ከዶ/ር ዮናስ አሽኔ ጋር @ShegerFM1021Radio
56:57

Now Playing
Mekoya - ጀርመን ሄጄ ነበር...ክፍል 2 በእሸቴ አሰፋ #germany #EsheteAssefa @ShegerFM1021Radio
28:23

Now Playing
Tizita Ze Arada - ኢትዮጵያ እና ጎረቤቶቿ የትብብር እና የውዝግብ አዙሪት /የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ግንኙነት ክፍል 2 #BeleteBelachew
27:13
bottom of page








