top of page

መጋቢት 21፣2016 - መልሶ ግንባታው ከምጣኔ ሐብት አንፃር!

  • Mar 30, 2024
  • 1 min read

አዲስ አበባ መልሳ ልትገነባ ፈራርሳለች፡፡


እዚህም እዚያም መንገድ ፣በመንገድ ላይ የተተከለው ዛፍ፣ የንግድና የመኖሪያ ቤት፣ ህንፃውና አጥሩ ሳይቀር ወደ ፍርስራሽነት ተቀይሯል፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሚዩኒኬሽን ሀላፊ ከሰሞኑን ሸገር ስቱዲዮ ተገኝተው ስለ ጉዳዩ ሲያብራሩ ለተነሺዎች ከ7 ወር በፊት መረጃ ሰጥተናል፤ በተለያየ ምክንያት ያልሰሙ ካልሆኑ በስተቀር ሌሎቹ ስለ ጉዳዩ በቂ መረጃ ነበራቸው ሲሉ መልሰዋል፡፡


መንግስት አስቤና መክሬ ስራውን ጀመርኩኝ ቢልም የሚታየው ግን ከዛ የተለየ ነው፡፡


በቅርብ ጊዜ ውስጥ የተገነቡ፣ ከቀናት በፊት የተተከለው፣ የተገነባና የተቀባው ሁሉ ዛሬ ፍርስራሽ ሆኗል፡፡

ይህ በኢኮኖሚ ላይ የሚኖረው ተፅዕኖ ምንድነው?


የእለት ጉርሱን ተሯሩጦ የሚያገኘው ኢ-መደበኛ ስራ ላይ የተሰማራው የከተማው ህዝብስ በዚህ የማፍረስ መገንባት፣ የመኖሪያ ቦታውን የመቀየር ሒደት ምን ያህል ተጎጂ ነው?


ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
የቤት ገዢዎችን የመግዛት አቅም ለማበርታት እንዲያግዝ ፖሊሲ የተዘጋጀለት የሞርጌጅ ባንክ እንዲቋቋም ተጠየቀ።

ሚያዝያ 20/2018 የቤት ገዢዎችን የመግዛት አቅም ለማበርታት እንዲያግዝ ፖሊሲ የተዘጋጀለት የሞርጌጅ ባንክ እንዲቋቋም ተጠየቀ። በኢትዮጵያ ያለው የግለሰቦች ቤት የመግዛት አቅም ከጊዜ ጊዜ እየቀነሰ መምጣት፣የብርየመግዛት አቅም መዳከም የግለሰቦች ቤት የመግዛት አቅም አብሮ ተዳክሟል ይላሉ የሪል እስቴት

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page