top of page

ሐምሌ 17፣2015 - የዩክሬይንና የሩሲያ፤ የእህልና የማዳበሪያ ምርት በአፋጣኝ ለአለም ገበያ እንዲቀርብ ተጠየቀ

ቻይና የዩክሬይንም የሩሲያም የእህልና የማዳበሪያ ምርት በአፋጣኝ ለአለም ገበያ የሚቀርብበት መላ እንዲመታ ጠየቀች፡፡


የቀዳሚው ስምምነት የጊዜ ገደብ ባለፈው ሳምንት አብቅቷል፡፡


ስምምነቱ የዩክሬይን የእህል እና የማዳበሪያ ምርት በጥቁር ባህር ወደቦች በኩል ለአለም ገበያ እንዲቀርብ የሚጠይቅ ነበር፡፡


ለሩሲያም ተመሳሳይ እድል ቢያስቀምጥም በምዕራባዊያን ማዕቀብ እና እንቅፋትነት የስምምነቱ ክፍል ስራ ላይ ሳይውል ቆይቷል፡፡


በዚህም የተነሳ ሩሲያ የስምምነቱን መቀጠል አልሻም ማለቷን አናዶሉ አስታውሷል፡፡


አሁን ግን ለመፍትሄው የዩክሬይንም የሩሲያም ምርት ለአለም ገበያ የሚቀርብበት መላ እንዲመታ መጠየቋ ተሰምቷል፡፡



የኔነህ ከበደ


ሸገርንወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz




bottom of page