በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የነዳጅ አቅርቦት ችግር የወርቅ ምርትን በ30 በመቶ እንዲቀንስ ምክንያት ሆኗል
- 2 hours ago
- 1 min read
ሰኔ 5/2018
የወርቅ ማዕድን ከሚመረትባቸው ክልሎች መካከል የሆነው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ የነዳጅ እጥረቱ፤ በወርቅ መገኘት የነበረበትን ገቢ እያሳጣ መሆኑን ተናገረ፡፡
ባለፉት 2 ወራት ብቻ የነዳጅ አቅርቦት ችግር የወርቅ ምርትን በ30 በመቶ እንዲቀንስ ምክንያት ሆኗል ብሏል፡፡
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ የማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ፤ የነዳጅ አቅርቦት ችግሩ ከባለፉት ወራት የተሻለ ቢሆንም አሁንም ግን ችግሩ በማዕድን ዘርፉ ላይ ጥላውን እንዳጠላበት ተናግሯል።
በሌላ በኩል ክልሉ በዘንድሮው 9 ወራት 6222.5 ኪ.ግ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ማድረጉንም ሰምተናል።
ባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከ47 ኩንታል በላይ ወርቅ ገቢ እንዳደረገም ተነግሯል።
በዚህም አጠቃላይ በማዕድን ዘርፉ ከ83 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል ሲል ቢሮው ነግሮናል።
የክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ቱጃኔ አደም የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትን ተከትሎ በሀገሪቱ ላይ የተከሰተው የነዳጅ እጥረት በበርካታ የልማት ዘርፎች ላይ ተጽእኖ እንዳሳደረ አንስተዋል።
እንደ ቤንሻጉል ጉሙዝ ክልልም በተለይ ማዕድን የማውጣት ስራውን አስተጓጉሎታል፣ በዚህም ሀገር ከማዕድን ሀብቷ ማግኘት የሚገባትን ገቢ እያሳጣት ነው ብለዋል።
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…..
ፍቅሩ አምባቸው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i

