ጥቅምት 6 2018 - የኢትዮጵያ የሚዲያ የልህቀት ማዕከል ስራ ጀመረ፡፡
- sheger1021fm
- Oct 16
- 1 min read
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ስራ የጀመረው ማዕከሉ የሚዲያ ተቋማትንና የባለሞያዎችን አቅም የመገንባት ስራን ይሰራል ተብሏል።
ማዕከሉ የተመሰረተው በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን መሆኑን በዝግጅቱ ላይ ሲነገር ሰምተናል፡፡
በልህቀት ማዕከሉ መክፈቻ ዝግጅት ላይ የሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ ሌሎች ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችና ሚኒስትሮች ተገኝተዋል፡፡

በልህቀት ማዕከሉ በጋዜጠኝነት ሥነ ምግባር እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ስልጠና እንደሚሰጥ የተነገረ ሲሆን ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች እና ተቋማት ጋር በትብብር እንደሚሰራም ተነግሯል።
የማዕከሉ መቋቋም ዋና ዓላማ የጋዜጠኞችን የሙያ እውቀት እና ክህሎትን ማሳደግ ላይ በትኩረት መስራት ነው ተብሏል።
በአለም አቀፍ የሚዲያ አሰራር መሰረት ባለሙያው ከጋዜጠኝነት ትምህርት ባለፈ በህግ፣ በጤና፣ በፖለቲካ፣ በውሀ ዘርፍ እና በሌሎችም ሙያዎች የሰለጠነ መሆንን ያስገድዳል፤ ነገር ግን በኢትዮጵያ ይህ ዓይነቱ አሰራር አይታይም ተብሏል፡፡
ይህንን ችግር ለመፍታትም የሚዲያ የልህቀት ማዕከሉን መመስረት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል መባሉን በመክፈቻ ዝግጅቱ ላይ ሲነገር ሰምተናል፡፡
ቴዎድሮስ ወርቁ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s












Comments