top of page

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሥነ ምግባር ጥሰት በፈጸሙ 54 ሠራተኞቹ ላይ የተለያየ መወሰዱን ተናገረ፡፡

  • sheger1021fm
  • 1 hour ago
  • 1 min read

ታህሳስ 7/2018

 

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሥነ ምግባር ጥሰት በፈጸሙ 54 ሠራተኞቹ ላይ የተለያየ መወሰዱን ተናገረ፡፡

 

አምስቱ ከስራ የተሰናበቱ መሆናቸውን ሠምተናል፡፡

 

የተለያየ የስነ ምግባር ጥሰት በፈጸሙ ሃምሳ አራት ሰራተኞቹ ላይ የተለያዩ እርምጃዎችን እንደወሰደ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናግሯል፡፡

 

ሰራተኞቹ ላይ እርምጃው የተወሰደው ባለፉት አምስት ወራት የተገኙ መረጃዎችን መሰረት በማድረግ እንደሆነ የአገልግሎቱ የኮሙኒኬሽን ስራ አስፋጸሚ አቶ አንዋር አብራር ነግረውናል፡፡

 

ree

መረጃውን መሰረት በማድረግ በተየወሰደው እርምጃ አምስቱ ከስራቸው ተሰናብተዋል ብለዋል፡፡

 

የስነ ምግባር ጥሰት ተፈጽሞባቸው የተገኙ ዋና ዋና የስራ ክፍሎችንም ስራ አስፈጻሚው ነግረውናል፡፡

 

ከአገልግሎት ጠያቂዎች ያልተገባ ጥቅም መጠየቅ፤ የቆጣሪ ንባብን ዝቅ አድርጎ መመዝገብ እና ቆጣሪ ያለ አግባብ መነካካት ሰራተኞቹ ፈጽመዋቸዋል ከተባሉ የስነ ምግባር ጥሰቶች መካከል እንደሆኑ ሰምተናል፡፡

 

አገልግሎቱ ወደፊትም ከህብረተሰቡ የሚቀርበሉትን ጥቆማዎች መሰረት በማድረግ ተገቢውን የእርምት እርምጃ እንደሚወስድ አቶ አንዋር ነግረውናል፡፡

 

ንጋቱ ረጋሳ

 

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page