top of page

ጥቅምት 23፣2016 - የባህር ማዶ ወሬዎች

  • Nov 3, 2023
  • 1 min read

#ሳውድ አረቢያ


በሳውድአረቢያ ለጋዛ ተፈናቃይ ፍልስጤማውያን መደገፊያ የገንዘብ እርዳታ ማሰባሰብ ተጀመረ፡፡


ንጉስሳልማን እና አልጋ ወራሽ ሞሐመድ ቢን ሳልማን የእርዳታ ማሰባሰቡ ዋነኞቹ አቀላጣፊዎች እንደሆኑ አረብ ኒውስ ፅፏል፡፡


ንጉሱእና አልጋ ወራሹ ለዚሁ ዓላማ 80 ሚሊዮን የሳውዲ ሪያል መለገሳቸው ታውቋል፡፡


የሳውዲአረቢያ የሞስሊም ምሁራን መማክርት ሸንጎ ዋና ፀሐፊ ዜጎች በእርዳታ ማሰባሰቡ በስፋት እንዲካፈሉ ጥሪ አቅርበዋል ተብሏል፡፡


ከወዲሁምየሳውዲ ዜጎች እርዳታ እየለገሱ መሆኑ ታውቋል፡፡


ሳውዲአረቢያ እስራኤል የጋዛ ጥቃቷን እንድታቆም ከሚጠይቁት አገሮች አንዷ እንደሆነች ዘገባው አስታውሷል፡፡


የእስራኤልጦር የጋዛ ከተማን በሙሉ ከበባዬ ውስጥ አስገብቻታለሁ አለ፡፡


ጦሩበሐማስ ጠቅላይ መምሪያ ፣ በማዘዣ ጣቢያዎቹ እና በሮኬት ማስወንጨፊያ መሰረተ ልማቶቹ ላይ ድብደባ እየፈፀምኩ ነው ማለቱን ቢቢሲ ፅፏል፡፡


ሐማስበእስራኤል ላይ ድንገት ደራሽ ጥቃት ካደረሰ ወዲህ ለወር ያህል ጊዜ እስራኤል ጋዛን ያለ እረፍት በአየር እየደበደበችው ነው፡፡


የእስራኤልየአየር ጥቃት በሰላማዊ ፍልስጤማዊያን ላይ ሳይቀር ከፍተኛ እልቂት እያስከተለ ነው ይባላል፡፡


የጋዛየጤና ሹሞች እንዳሉት እስካሁን በእስራኤል ድብደባ የተገደሉት ፍልስጤማዊያን ብዛት ከ9,000 በልጧል፡፡


የሰላማዊፍልስጤማዊያንን ሞት ስቃይ እና መከራ ለመቀነስ ከየአቅጣጫው የተኩስ አቁም ጥሪ እየቀረበ ቢሆንም እስራኤል ግን ይሄንን አልሰማም እያለች ነው፡፡



የአሜሪካየህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለእስራኤል የጦር ወቅት መደገፊያ የ14.3 ቢሊዮን ዶላር ለማቅረብ የሚያስችለውን ህግ ማፅደቁ ተሰማ፡፡


ፕሬዘዳንትጆ ባይደን በህጉ ላይ ፊርማቸውን ማኖራቸው አጠራጥሯል፡፡


ባይደንቀደም ሲል ለዩክሬይን የጦር ወቅት መደገፊያ እና ለሌሎችም ጸጥታ ነክ ተግባራት ማከናወኛ አብረው የ106 ቢሊዮን ዶላር ጥያቄ አቅርበው እንደነበር አኒ ኒውስ አስታውሷል፡፡


የህዝብተወካዮቹ ምክር ቤት ሪፖብሊካኞች ለእስራኤል የታቀደውን መደገፊያ ብቻ ነጥለው ማፅደቃቸው ታውቋል፡፡


ጉዳዩዴሞክራቶችን ከሪፖብሊካውያኑ ጋር እያነታረከ ነው::


የህዝብተወካዮቹ ምክር ቤት አብዛኞቹ እንደራሴዎች ሪፖብሊካውያን እንደሆኑ ዘገባው አስታውሷል፡፡


ጉዳዩበብዙ ማነጋገሩ እንደማይቀር ተገምቷል፡፡


የኔነህከበደ


የሸገርንወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
የሐምሌ 23 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ግብፅ በግብፅ የሜዴትራኒያን የባህር ዳርቻ የነበረ የአሜሪካ የጋዝ ማጠራቀሚያ መርከብ በድሮን ተመታ ተባለ፡፡ ሁለት የደህንነት ምንጮች መርከቡ በድሮን እንደተመታ አረጋግጠውልኛል ሲል ሬውተርስ ፅፏል፡፡ መርከቡ በድሮን እንደተመታ በእሳት መያያዙ ታውቋል፡፡ ቃጠሎው ወደ ሌላ መርከብም ተጋብቶ ነበር ተብሏል፡፡ ኋላ ግን

 
 
 
የሐምሌ 22 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#አሜሪካ አሜሪካ እና ሳውዲ አረቢያ ኢራቅ ውስጥ በአፍቃሪ ኢራን ታጣቂዎች ይዞታ ላይ ድብደባ ፈፀሙ፡፡ ሰሞኑን ሳውዲ አረቢያ በኢራቅ የሚገኙ አፍቃሪ ኢራን ታጣቂዎች በድሮን ጥቃት አድርሰውብኛል ስትል እንደነበር አልጀዚራ አስታውሷል፡፡ ሳውዲ ጥቃቱን ከማውገዝ በተጨማሪ መበቀሌ አይቀርም በሚል ዝታ ነበር፡፡ በኢራቆቹ አ

 
 
 
የሐምሌ 21 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ጃፓን የጃፓን ደቡባዊ ምዕራብ ክፍል በርዕደ መሬት ተመታ፡፡ ርዕደ መሬቱ የደረሰው ኩማማቶ የተባለው የአገሪቱ ክፍል እንደሆነ ኒኪ እስያ ፅፏል፡፡ የመሬት ነውጡ የተቀሰቀሰው ከምድር በ10 ኪሎ ሜትር ጥልቀት መሆኑ ታውቋል፡፡ ነውጡ በርዕደ መሬት መለኪያ /ሬክተር ስኬል/ 7 ነጥብ 1 ሆኖ መመዝገቡ ታውቋል፡፡ ቀደም ሲ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page