top of page

ጥር 9፣2016 - የባህር ማዶ ወሬዎች

  • Jan 18, 2024
  • 2 min read

በአፍሪካዊቱ ደሴታማ አገር ኮሞሮስ ከምሽት እስከ ንጋት የሚዘልቅ የሰዓት እላፊ ሥራ ላይ ዋለ፡፡


የሰዓት እላፊው ሥራ ላይ የዋለው በአገሪቱ በተካሄደው ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ በስልጣን ላይ የሚገኙት አዛሊ አሱማኒ አሸንፈዋል መባሉን ተከትሎ ግጭት በመፈጠሩ እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡


ተቃዋሚዎች አሱማኒ አሸንፈውበታል በተባለው ምርጫ ተጭበርብሯል እያሉ ነው፡፡


በርዕሰ ከተማዋ ሞሮኒ ለተቃውሞ አደባባይ የወጡ የተቃዋሚዎች ደጋፊዎች ከፀጥታ አስከባሪዎች ጋር መጋጨታቸው ታውቋል፡፡


የሰዓት እላፊውም ይሄንኑ ግጭት የተከተለ ነው ተብሏል፡፡#የሁቲ_ታጣቂዎች


የየመን ሁቲዎች በኤደን ባህረ ሰላጤ አንዲት የአሜሪካ መርከብን በአጥቂ ሰው አልባ በራሪ አካል/ድሮን መምታታቸው ተሰማ፡፡


ሁቲዎቹ ትናንት ምሽት በአሜሪካ መርከብ ላይ የድሮን ጥቃት መሰንዘራቸውን የአሜሪካ የጦር ሹሞች እንደተናገሩ አረብ ኒውስ ፅፏል፡፡


ጥቃት አድርሰዋል የተባሉት ሁቲዎች ግን ፈጥነው ሀላፊዎቹ እኛ ነን አላሉም፡፡


በሌላኛዋ የአሜሪካ መርከብ ላይ ጥቃት የተሰነዘረው አሜሪካ የሁቲዎቹን ንቅናቄ ዳግም በአለም አቀፍ አሸባሪነት መፈረጇን ተከትሎ መሆኑ ታውቋል፡፡


ሁቲዎቹ አሜሪካ ያሻትን ብትለንም እኛ ግን ፍልስጤማውያንን ከመደገፍ ወደ ኋላ አንልም ብለዋል በቃል አቀባያቸው አማካይነት፡፡


ትናንት በሁቲዎቹ የድሮን ጥቃት ተሰንዝሮባታል የተባለችው መርከብ ቃጠሎ አጋጥሟት ነበር ቢባልም የጉዳቷ መጠን በዝርዝር አልተጠቀሰም፡፡




አሜሪካ የየመን ሁቲዎችን ንቅናቄ ዳግም በልዩ አለም አቀፍ አሸባሪነት ፈረጀችው፡፡


ፍረጃው በልዩ ልዩ ማዕቀቦችም ጭምር የታገዘ እንደሆነ የአሜሪካ ድምፅ የእንግሊዘኛው አገልግሎት በድረ ገጹ ፅፏል፡፡

ያም ሆኖ በማእቀቡ እንደ ምግብ መድሐኒት እና የነዳጅ ዘይት ያሉ መሰረታዊ አቅርቦቶች እንደማይስተጓጎሉ የአሜሪካ ሹሞች ተናግረዋል፡፡


ሁቲዎቹ እስራኤል የጋዛ ዘመቻዋን ካላቆመች በቀይ ባህር ከእስራኤል ጋር አንዳች ቁርኝት ያላቸውን መርከቦች እንደሚመቱ ሲዝቱ ቆይተዋል፡፡


በአሜሪካ እና ብሪታንያም ይዞታቸውን መደብደብ ከጀመሩ ወዲህም ሁቲዎቹ ጥቃታቸውን አላቆሙም፡፡


ሁቲዎቹ በአሜሪካ በቀድሞው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአስተዳደር ዘመን መጨረሻ በአሸባሪነት ተፈርጀው በፕሬዘዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር ከአሸባሪነትን ተፍቀው እንደነበር ዘገባው አስታውሷል፡፡



በቅርቡ በአገር ክህደት ክስ የተመሰረባቸው የሴራሊዮን የቀድሞ ፕሬዘዳንት ኧርነስት ባይ ኮሮማ ወደ ውጭ አገር እንደሚያመሩ ተሰማ፡፡


ኧርነስት ባይ ኮሮማ ወደ ውጭ አገር የሚያመሩት በጤና እክል ምክንያት በውጭ አገር ህክምና እንዲከታተሉ በአገሪቱ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፈቃድ በማግኘታቸው እንደሆነ አልጀዚራ ፅፏል፡፡


የቀድሞው ፕሬዘዳንት ቀደም ሲል ከጥቂት ወራት በፊት በአገሪቱ ተሞክሮ ነበር በተባለ የመንግስት ግልበጣ እጃቸውን አስገብተዋል ተብለው በአገር ክህደት ክስ እንደተመሰረሰተባቸው ዘገባው አስታውሷል፡፡


ኧርነስት ባይ ኮሮማ የመንግስት ግልበጣ ተሞክሮ ነበር ከተባለበት ጊዜ አንስቶ በቁም እስር ላይ ናቸው፡፡


የቀድሞው ፕሬዘዳንት ለህክምና ወደ ውጭ አገር እንዲሄዱ ቢፈቀድላቸውም በፍርድ ቤት የተከፈተባቸው ክስ አለመቋረጡ ታውቋል፡፡


የሴራሊዮን መንግስት የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ አከብራለሁ ማለቱ ተሰምቷል፡፡




የየመን ሁቲዎች በኤደን ባህረ ሰላጤ አንዲት የአሜሪካ መርከብን በአጥቂ ሰው አልባ በራሪ አካል/ድሮን መምታታቸው ተሰማ፡፡


ሁቲዎቹ ትናንት ምሽት በአሜሪካ መርከብ ላይ የድሮን ጥቃት መሰንዘራቸውን የአሜሪካ የጦር ሹሞች እንደተናገሩ አረብ ኒውስ ፅፏል፡፡


ጥቃት አድርሰዋል የተባሉት ሁቲዎች ግን ፈጥነው ሀላፊዎቹ እኛ ነን አላሉም፡፡


በሌላኛዋ የአሜሪካ መርከብ ላይ ጥቃት የተሰነዘረው አሜሪካ የሁቲዎቹን ንቅናቄ ዳግም በአለም አቀፍ አሸባሪነት መፈረጇን ተከትሎ መሆኑ ታውቋል፡፡


ሁቲዎቹ አሜሪካ ያሻትን ብትለንም እኛ ግን ፍልስጤማውያንን ከመደገፍ ወደ ኋላ አንልም ብለዋል በቃል አቀባያቸው አማካይነት፡፡


ትናንት በሁቲዎቹ የድሮን ጥቃት ተሰንዝሮባታል የተባለችው መርከብ ቃጠሎ አጋጥሟት ነበር ቢባልም የጉዳቷ መጠን በዝርዝር አልተጠቀሰም፡፡


የኔነህ ከበደ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Recent Posts

See All
የሐምሌ 23 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ግብፅ በግብፅ የሜዴትራኒያን የባህር ዳርቻ የነበረ የአሜሪካ የጋዝ ማጠራቀሚያ መርከብ በድሮን ተመታ ተባለ፡፡ ሁለት የደህንነት ምንጮች መርከቡ በድሮን እንደተመታ አረጋግጠውልኛል ሲል ሬውተርስ ፅፏል፡፡ መርከቡ በድሮን እንደተመታ በእሳት መያያዙ ታውቋል፡፡ ቃጠሎው ወደ ሌላ መርከብም ተጋብቶ ነበር ተብሏል፡፡ ኋላ ግን

 
 
 
የሐምሌ 22 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#አሜሪካ አሜሪካ እና ሳውዲ አረቢያ ኢራቅ ውስጥ በአፍቃሪ ኢራን ታጣቂዎች ይዞታ ላይ ድብደባ ፈፀሙ፡፡ ሰሞኑን ሳውዲ አረቢያ በኢራቅ የሚገኙ አፍቃሪ ኢራን ታጣቂዎች በድሮን ጥቃት አድርሰውብኛል ስትል እንደነበር አልጀዚራ አስታውሷል፡፡ ሳውዲ ጥቃቱን ከማውገዝ በተጨማሪ መበቀሌ አይቀርም በሚል ዝታ ነበር፡፡ በኢራቆቹ አ

 
 
 
የሐምሌ 21 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ጃፓን የጃፓን ደቡባዊ ምዕራብ ክፍል በርዕደ መሬት ተመታ፡፡ ርዕደ መሬቱ የደረሰው ኩማማቶ የተባለው የአገሪቱ ክፍል እንደሆነ ኒኪ እስያ ፅፏል፡፡ የመሬት ነውጡ የተቀሰቀሰው ከምድር በ10 ኪሎ ሜትር ጥልቀት መሆኑ ታውቋል፡፡ ነውጡ በርዕደ መሬት መለኪያ /ሬክተር ስኬል/ 7 ነጥብ 1 ሆኖ መመዝገቡ ታውቋል፡፡ ቀደም ሲ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page