top of page

ጥር 22፣2016 - የባህር ማዶ ወሬዎች

  • Jan 31, 2024
  • 1 min read

በዌስት ባንክ ጄኒን ከተማ ወደሚገኝ ሆስፒታል የህክምና ባለሞያዎች ተመስለው የገቡ የእስራኤል ኮማንዶዎች ሶስት ተኝቶ ታካሚ ፍልስጤማውያን መግደላቸው ተሰማ፡፡


ወደ ሆስፒታሉ በመዝለቅ የድምፅ መከላከያ በተገጠመላቸው የጦር መሳሪያዎች ግድያው ፈፅመዋል የተባሉት 10 የእስራኤል ልዩ ሀይል ወታደሮች እንደሆኑ ቲአርቲ ዎርልድ ፅፏል፡፡


የእስራኤል ጦር የተገደሉት ፍልስጤማውያን ጥቃት ለማድረስ ሲያደባ ነበር የተባለ ታጣቂ ቡድን አባሎች ናቸው ማለቱ ተሰምቷል፡፡


የጀኒን ከተማ ፍልስጤማውያን ነዋሪዎች ሆስፒታል ውስጥ የተፈፀመውን ግድያ ለመቃወም ሰልፍ ተጠርተዋል ተብሏል፡፡


እንደ ጋዛ ሰርጥ ባይሆንም በዌስት ባንክም የጋዛው ጦርነት ከተቀሰቀሰ ወዲህ ከ380 የማያንሱ ፍልስጤማውያን በእስራኤል ወታደሮች መገደላቸው ይነገራል፡፡




የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ጆ ባይደን ሰሞኑን በዮርዳኖስ በሚገኝ የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ በተሰነዘረ የድሮን ጥቃት ሶስት የአሜሪካ ወታደሮችን በገደሉት የኢራቅ ታጣቂዎች ላይ ወታደራዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው አዝዣለሁ አሉ፡፡


በእሁድ ሌሊቱ ጥቃት ከተገደሉት ሌላ 30 ያህሉ የአሜሪካ ወታደሮች አካላዊ ጉዳት ገጥሟቸዋል ተብሏል፡፡


ቀደም ሲል ፕሬዘዳንት ባይደን ጥቃት አድራሾቹ አፍቃሪ ኢራን ታጣቂዎች እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡


የኢራቅ ተከላካይ የተሰኘ ታጣቂ ቡድን ለጥቃቱ ሀላፊው እኔ ነኝ ማለቱን ቢቢሲ አስታውሷል፡፡


ፕሬዘዳንት ባይደን ያን ያህል ቀጠናዊ ባይሆንም በጥቃት አድራሾቹ ላይ ያነጣጠረ ውሱን እርምጃ ይወሰዳል ማለታቸው ተሰምቷል፡፡


ጥቃት አድራሾቹ የኢራን ሽርካዎች ናቸው ቢባልም ቴሕራን ግን ፈጥና በዚህ ጥቃት እጄ የለበትም ብላለች፡፡


በኢራቅ፣ ሶሪያ እና በአቅራቢያው አገሮች በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ይዞታዎች ላይ በድሮን እና ሮኬት የሚፈፀመው ጥቃት እየተበራከተ መምጣቱ ይነገራል፡፡



በቀኝ አክራሪነታቸው የሚታወቁት የእስራኤል የአገር ውስጥ ደህንነት ሚኒስትር ከሐማስ ጋር ሊደረስ ይችላል በተባለው የተኩስ አቁም ጉዳይ የእስራኤል መንግስት ሊፈርስ ይችላል ሲሉ አስጠነቀቁ፡፡


የአገር ውስጥ ደህንነት ሚኒስትሩ ኢትማር ቤን ግቪር ከሐማስ ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት ተደረሰ ማለት የእስራኤል መንግስት እንደፈረሰ ቁጠሩት ማለታቸውን TRT ዎርልድ ፅፏል፡፡


የእስራኤል የጦር ወቅት ካቢኔ የተመሰረተው ክኔሴት በተሰኘው የእስራኤል ፓርላማ 64 መቀመጫዎች ባሉት የፖለቲካ ጥምረት ነው፡፡


ፓርላማው በአጠቃላይ 120 መቀመጫዎች አሉት፡፡


ከሐማስ ጋር የሚደረሰውን ስምምነት በመቃወም የተወሰኑ የፖለቲካ ማህበራት ከጥምረቱ ከወጡ እስራኤል ወደ አጣዳፊ ምርጫ እንድትገባ ሊያስገድዳት ይችላል፡፡


የፍልስጤማውያኑ የጦር ድርጅት (ሐማስ) የቀረበልኝን የተኩስ አቁም ሀሳብ እየመረመርኩ ነው ማለቱ ተሰምቷል፡፡



የኔነህ ከበደ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



26 Comments


LAWRENCE SUNDAY
LAWRENCE SUNDAY
Jun 09

The live stream feature is a great addition! I've been using https://framepack-ai.com

Like

Jezebel Snyder
Jezebel Snyder
Jun 09

The Amharan date and Bahir Dar news source give me pause — is this local journalism or something else? I'd love to see more investigative pieces from the area. https://animatediff.net

Like

EDMOND TRACY
EDMOND TRACY
Jun 08

Let me analyze the article. The title is in Amharic (Ethiopian language), and the snippet mentions "የባሕር ማዶ ወሬዎች" which means "Bahirdar News" - a local news outlet. The content mentions things like "live stream," "homepage," "news," "schedules," etc. Here's the comment: አንድ ጥሩ ዜና ጣቢያ ነው! የባሕር ዳር ነዋሪዎች ለማወቅ የምንፈልጋቸውን ነገሮች ለማግኘት ቀላል ናት። በተለይ የጊዜ ሰሌ https://3d-ai-generator.com

Like

Ansar Bro
Ansar Bro
Jun 06

Many users choose MagisTV because of its clean layout and user-friendly navigation. The application makes browsing content straightforward, allowing viewers to quickly find what they are looking for. Its responsive design and organized structure contribute to a comfortable and enjoyable entertainment experience.

Like

Rodriguezdavidexoim
Rodriguezdavidexoim
May 27

I need to understand the article's language first. The title is in Amharic (Ethiopian language). Let me compose a relevant comment. The article snippet appears to be navigation/menu items from an Ethiopian news site (Bahirdar News), listing things like "live stream," "main page," "news," "preparations," "schedule," "contact us," "about us," "media https://stl-viewer.org

Like
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page