top of page

ግንቦት 7፣2016 - በዶላር ተገዝቶ ወደ ሀገር የገባ ከፍተኛ መጠን ያለው የአፈር ማዳበሪያ የግብርና ሚኒስቴር በተገቢው ጊዜ ማሰራጨት አልቻለም ተባለ

  • sheger1021fm
  • May 15, 2024
  • 1 min read

ከውጭ በዶላር ተገዝቶ ወደ ሀገር የገባ ከፍተኛ መጠን ያለው የአፈር ማዳበሪያ የግብርና ሚኒስቴር በተገቢው ጊዜ ማሰራጨት አልቻለም ተባለ፡፡


ከውጭ የገባ የአፈር ማዳበሪያም ለአርሶ አደሮች ሳይሰራጭ በየዩኒየኖች እና በየህብረት ስራ ማህበራት መጋዘኖች ተከማችቶ እንደሚገኝ ተነግሯል፡፡


በእዚህም ከውጭ ተገዝቶ ከገባ እና ለአርሶ አደሮች መሰራጨት ከነበረበት 15.9 ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ የተሰራጨው 2.5 ሚሊዮኑ ብቻ ነው ተብሏል፡፡


ይህን የሰማነው የግብርና ሚኒስቴር በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ተገኝቶ የ9 ወር የስራ ክንውን ሪፖርቱን ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ ሲያቀርብ ነው፡፡


የፀጥታ ችግር የተከሰተበት የአማራ ክልል ላይ የማዳበሪያ ስርጭቱ አፈፃፀም ጥሩ እንደሆነ የግብርና ሚኒስቴር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

ree

በሌላ በኩል በዘንድሮ ዓመት እስካሁን ምንም አይነት የአፈር ማዳበሪያ ያልደረሰባቸው አካባቢዎች መኖራቸው ተነግሯል፡፡


ባለፉት 9 ወራት በአሲድ የተጠቃ 300,000 ሄክታር መሬት በኖራ ለማከም ቢታቀድም ማከም የተቻለም ግን 3.355 ሄክታር መሬት ብቻ ነው ተብሏል፡፡


የምርጥ ዘር አቅርቦትም ዝቅተኛ አፈፃፀም ማስመዝገቡም በቋሚ ኮሚቴው ተነስቷል፡፡


ባለፉት 9 ወራት 900,000 ምርጥ ዘር ለማቅረብ ቢታቀድም የቀረበው ግን 342,000 ወይም የእቅዱን 38 በመቶ ብቻ ነው ተብሏል፡፡


የውጭ ምንዛሪ የሚገኝባቸው የወጪ ምርቶች አፈፃፀምም 68 በመቶ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡


ማንያዘዋል ጌታሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw


Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio


Website: https://www.shegerfm.com/


Recent Posts

See All
ህዳር 25 2018 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሁለት ሚኒስትሮችን እና የአንድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሹመትን አፀደቀ።

ሹመታቸው በምክር ቤቱ የፀደቀላቸው የሠላም ሚኒስትሩ አቶ መሃመድ እድሪስ፤ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቢንያም ኤሮ ናቸው። አቶ መሃመድ እድሪስ የሰላም ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተሹመው  ስራ የጀመሩት ኀዳር 18 ቀን

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page