top of page

የካቲት 16፣2016 - ከደሴ ሸዋሮቢት፣ ደ/ብረሀን የሚደረግ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ለጊዜው እንዲቆመ መወሰኑ ተሰማ

  • Feb 24, 2024
  • 1 min read

ከደሴ፣ ሸዋሮቢት፣ ደ/ብረሀን እንዲሁም ከደ/ብረሀን፣ ሸዋሮቢትና ደሴ የሚደረግ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ለጊዜው እንዲቆመ መወሰኑ ተሰማ።


ውሳኔው እወቁት ያለው የማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖስት መሆኑን የአማራ ክልል ኮሙኒኬሽን አውርቷል፡፡

በዚህም መሰረት ከዛሬ ጀምሮ የትኛውም አይነት የትራንስፖርት አገልግሎት ከደሴ፣ ሸዋሮቢት፣ ደ/ብረሀን እንዲሁም ከደ/ብረሀን ሸዋሮቢትና ደሴ ላልተወሰነ ጊዜ እንዲቆም ተብሏል፡፡

የትራንስፖርት ክልከላው የተላለፈው ኮማንድ ፖስቱ ‘’ፅንፈኛ ሀይሎች’’ ሲል የጠቀሳቸው ሃይሎች ላይ እርምጃ እየወሰደ በመሆኑ ሰላማዊ ዜጎች ጉዳት እንዳይደርስባቸው እና አካባቢውን በአጭር ቀናት ከፅንፈኛ ሀይሉ ነፃ ለማድረግ የኦፕሬሽን ስራ የተጀመረ ስለሆነ ነው ተብሏል፡፡


የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዲቆም የተወሰነ መሆኑ ታውቆ ህብረተሠቡ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የፀጥታ ሀይሉም ውሳኔው ይፈፀም ዘንድ ክትትል እንዲያደርግ ኮማንድ ፖስቱ መወሰኑ ተሰምቷል፡፡



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Recent Posts

See All
የሐምሌ 24 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ኮንጎ በኮንጎ ኪንሻሣ በኢቦላ የሚያዙ ሕሙማንና ወረርሽኙ የሚገድላቸው ሰዎች ብዛት በጣሙን እየጨመረ ነው ተባለ፡፡ በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጠው ሰዎች ብዛት ከ3 ሺህ 400 መብለጡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ወረርሽኙ የገደላቸው ሰዎች ብዛት ከ1 ሺህ 500 በላይ መድረሱ ተነግሯል፡፡ በአገሪቱ በኢቦላ በሽታ የሚያዙ ሰዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page