top of page

የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ከሰሞኑ የዋግነር አመፅ የማነሳሳት ሙከራ ጀርባ የምዕራባዊያን እጅ ስለመኖሩ እየመረመርን ነው አሉ

  • Jun 29, 2023
  • 1 min read

ሰኔ 20፣2015


የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ከሰሞኑ የዋግነር አመፅ የማነሳሳት ሙከራ ጀርባ የምዕራባዊያን እጅ ስለመኖሩ እየመረመርን ነው አሉ፡፡


ላቭሮቭ በዋግነር የተነሳው አመፅ እንደሚሳካ በአሜሪካ የደህንነት መስሪያ ቤቶች አስቀድሞ ተስፋ ተደርጎ እንደነበር ማንሳታቸውን አል አረቢያ ፅፏል፡፡


እንደውም የአሜሪካ የደህንነት ሹሞች ከዋግነሮች አመፅ መቀስቀስ አስቀድሞ ምልክቶችን አይተናል ማለታቸውን ላቭሮቭ ተናግረዋል፡፡


አመጹ በ24 ሰዓታት ጊዜ መክኗል፡፡


በጉዳዩ የምዕራባዊያን እጅ እንዳለበት ለማወቅ በሩሲያ የደህንነት መስሪያ ቤት እየተመረመረ መሆኑን ላቭሮቭ ተናግረዋል፡፡


የስልጡን ቅጥረኛ ወታደሮች አቅራቢው የዋግነር ኩባንያ የበላይ እና የአመፁ መሪ ውጥናቸውን ትተው ወደ ቤላሩስ ማምራታቸው ታውቋል፡፡



የኔነህ ከበደ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
የሐምሌ 23 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ግብፅ በግብፅ የሜዴትራኒያን የባህር ዳርቻ የነበረ የአሜሪካ የጋዝ ማጠራቀሚያ መርከብ በድሮን ተመታ ተባለ፡፡ ሁለት የደህንነት ምንጮች መርከቡ በድሮን እንደተመታ አረጋግጠውልኛል ሲል ሬውተርስ ፅፏል፡፡ መርከቡ በድሮን እንደተመታ በእሳት መያያዙ ታውቋል፡፡ ቃጠሎው ወደ ሌላ መርከብም ተጋብቶ ነበር ተብሏል፡፡ ኋላ ግን

 
 
 
የሐምሌ 22 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#አሜሪካ አሜሪካ እና ሳውዲ አረቢያ ኢራቅ ውስጥ በአፍቃሪ ኢራን ታጣቂዎች ይዞታ ላይ ድብደባ ፈፀሙ፡፡ ሰሞኑን ሳውዲ አረቢያ በኢራቅ የሚገኙ አፍቃሪ ኢራን ታጣቂዎች በድሮን ጥቃት አድርሰውብኛል ስትል እንደነበር አልጀዚራ አስታውሷል፡፡ ሳውዲ ጥቃቱን ከማውገዝ በተጨማሪ መበቀሌ አይቀርም በሚል ዝታ ነበር፡፡ በኢራቆቹ አ

 
 
 
የሐምሌ 21 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ጃፓን የጃፓን ደቡባዊ ምዕራብ ክፍል በርዕደ መሬት ተመታ፡፡ ርዕደ መሬቱ የደረሰው ኩማማቶ የተባለው የአገሪቱ ክፍል እንደሆነ ኒኪ እስያ ፅፏል፡፡ የመሬት ነውጡ የተቀሰቀሰው ከምድር በ10 ኪሎ ሜትር ጥልቀት መሆኑ ታውቋል፡፡ ነውጡ በርዕደ መሬት መለኪያ /ሬክተር ስኬል/ 7 ነጥብ 1 ሆኖ መመዝገቡ ታውቋል፡፡ ቀደም ሲ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page