top of page

ከተረፈ ምርቶች፣ አገልግሎቶቻቸውን ከጨረሱ ባትሪዎች አካባቢን የማይጎዱ ምርቶችን የሚሰሩትን ወጣቶች

  • 2 hours ago
  • 1 min read

ሰኔ 3 2018


ከተረፈ ምርቶች፣ አገልግሎቶቻቸውን ከጨረሱ ባትሪዎች አካባቢን የማይጎዱ ምርቶችን የሚሰሩትን ወጣቶችንና እነሱን የሚረዱ ተቋማት እንዲደገፉ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጠየቀ፡፡


ከተረፈ ምርቶች የንፅህና መጠበቂያ፣ ከሰል የመሳሰሉ ምርቶች የሰሩ ወጣቶችም፤ ቆሻሻ ሀብት እየፈጠረላቸው እንደሆነ ነግረውናል፡፡


ወጣቶቹ ወደ ስራ ሲገቡ አስፈላጊውን የሞያና የገንዘብ ድጋፍ እንደተደረገላቸው ተናግረዋል፡፡


ገንዘብና ሞያዊ ድጋፍ ካደረጉት መካከል ሪችፎር ቼንጅ አንዱ ነው፡፡


ድርጅቱ በሃሳብ ደረጃ የነበሩ 33 ድርጅቶች ንግድ መጀመር እንዲችሉ የሞያ ስልጠና እና ለእያንዳንዳቸው የ200 ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ተናግሯል፡፡


ወደ ሥራ ገብተው እራሳቸውን በሀሳብ እና በፋይናንስ በማሳደግ ላይ ለሚገኙ 8 ድርጅቶች ደግሞ 1.5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጌለው ብሏል።


ድርጅቱ ብቁ ናቸው ያላቸውን 75 ስራ ፈጣሪዎችን እውቅና ሰጥቷቸዋል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…

ማርታ በቀለ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…









Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page