top of page

የፌዴራል መንግስት ለክልሎች የደለደለው የበጀት

  • 14 hours ago
  • 1 min read

ሰኔ 4/2018


የፌዴራል መንግስት ለክልሎች ከደለደለው የበጀት ድጋፍ ትንሹ ለአዲስ አበባ የተመደበው 74.5 ሚሊዮን ብር ነው፡፡


ከፍተኛው ደግሞ ለኦሮሚያ ክልል 179.3 ቢሊዮን ብር ሆኖ መደልደሉን ከረቂቅ በጀቱ ተመልክተናል፡፡


ለመጪው የ2019 በጀት ዓመት የገንዘብ ሚኒስቴር ለፓርላማው ካቀረበው ረቂቅ በጀት እንደተመለከትነው ለ12 ክልሎች እና ለሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የተመደበው አጠቃላይ የበጀት ድጋፍ 520.5 ቢሊዮን ብር ነው፡፡


ከመካከሉ ሁለተኛው ትልቁ ድጋፍ ለአማራ ክልል የተያዘው 112.4 ቢሊዮን ብር ነው፡፡


ሶማሌ ክልል በሶስተኛ ደረጃ 51.9 ቢሊዮን ብር ለ2019 ዓ.ም በጀት ተደልድሎበታል፡፡


ለደቡብ ኢትዮጵያ 36.5 ቢሊዮን ፣ ለትግራይ 31.3 ቢሊዮን፣ ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ 30.9 ቢሊዮን ፣ ለሲዳማ ክልል ደግሞ 20.9 ቢሊዮን ብር ተመድርቧል፡፡


ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ከ16 እና ለአፋር ክልል ከ15 ቢሊዮን ብር በጀት በረቂቅ ደረጃ የተያዘ ሲሆን ቀሪዎቹ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ፣ ጋምቤላ ፣ ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እና ሐረሪ ህዝብ ክልል ከ9.5 እስከ 3.9 ቢሊዮን ብር የደረሰ በጀት ተደልድሎላቸዋል፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…








Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page