ኢትዮጵያ ለመጪው በጀት ዓመት ከያዘችው አጠቃላይ በጀት ከ542 ቢሊዮን ብር በላዩን ያለባትን የብድር እዳ ለመክፈል የተደለደለ ነው፡፡
- 12 hours ago
- 1 min read
ሰኔ 4/2018
ኢትዮጵያ ለመጪው በጀት ዓመት ከያዘችው አጠቃላይ በጀት ከ542 ቢሊዮን ብር በላዩን ያለባትን የብድር እዳ ለመክፈል የተደለደለ ነው፡፡
ይህም ለክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች መደገፊያ ከያዘው በጀት ከ21 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ ያለው ነው፡፡
መንግስት አጠቃላይ በዓመቱ ለተለያዩ ክፍያዎች ከመደበው ደግሞ የ59.9 በመቶው ድርሻ የያዘ ነው፡፡
በበጀት ዓመቱ እዳ ለመክፈል የተጠየቀው 581.1 ቢሊዮን ብር ሲሆን የተያዘው በጀት ደግሞ 542.1 ቢሊዮን ብር መሆኑን ረቂቅ በጀቱ ያሳያል፡፡

ይህም እዳ ለመክፈል ከሚያስፈልገው ገንዘብ የ78.8 ቢሊዮን ብር ልዩነት መኖሩን ያሳያል፡፡
በሌላ በኩል ለ2019 በጀት ዓመት 124.4 ቢሊዮን ብር ለመጠባበቂያ እና ለሌሎች ክፍያዎች በሚል 904.6 ቢሊዮን ብር በጀት ተይዟል፡፡
ለሌሎች ክፍያዎች ተብሎ ከተመደበው በጀት 26.3 በመቶው ወይም 238.1 ቢሊዮን ብሩ ክልሎች ለበጀት ድጋፍ ፣ 542.1 ቢሊዮን ብሩ ለእዳ ክፍያና 124.4 ቢሊዮን ብሩ ለመጠባበቂያ የተደለደለ ነው፡፡
ትዕግስት ዘሪሁን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i





Comments