ኢትዮጵያ ከአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት 261 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለማግኘት የሚያስችላትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሷ ተሰማ።
- sheger1021fm
- 12 minutes ago
- 1 min read
ታህሳስ 2/2018
ኢትዮጵያ ከአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት 261 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለማግኘት የሚያስችላትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሷ ተሰማ።
ይህ የብድር አቅርቦት ስምምነት #IMF ለኢትዮጵያ ለመስጠት ካሰበው የ4 ዓመት የ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር አቅርቦት አካል ነው።
የIMF እና የኢትዮጵያ መንግስት ሀላፊዎች በአዲስ አበባ እና በበይነ መረብ ባደረጉት የአራተኛው ዙር የብድር አቅርቦት ውይይት ላይ ኢትዮጵያ 261 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት የሚያስችላት የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተጠቅሷል።

ይህን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት የ IMF አስተዳደር እና የስራ አስፈጻሚ ቦርድ በመጪዎቹ ሳምንታት ያፀድቀዋል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተቋሙ ጠቅሷል።
የIMF የ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር አቅርቦት የተቋሙ የስራ አስፈጻሚ ቦርዱ ከዓመት በፊት ያጸደቀው እና የኢትዮጵያ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አካል ነው።
የ261 ሚሊዮን ዶላር ክፍያ ለኢትዮጵያ እንዲለቀቅ ከተደረገ በአጠቃላይ በፕሮግራሙ ስር ለኢትዮጵያ የተሰጠው የገንዘብ ድጋፍ ወደ 2.13 ቢሊዮን ዶላር ይደርሳል፡፡
ንጋቱ ሙሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1








