top of page

ታህሳስ 7፣ 2015- በመንግስት ግዥና ጨረታ የሚሳተፉ አቅራቢዎች በገቡት ውል መሠረት ግዴታቸውን እንዲወጡ ጠንካራ የቁጥጥር ስርዓት ሊኖር ይገባል ተባለ

  • sheger1021fm
  • Dec 16, 2022
  • 1 min read

Updated: Dec 17, 2022



በመንግስት ግዥና ጨረታ የሚሳተፉ አቅራቢዎች በገቡት ውል መሠረት ግዴታቸውን እንዲወጡ ጠንካራ የቁጥጥር ስርዓት ሊኖር ይገባል ተባለ።


ይህ የተባለው በመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን እንዲሁም በመንግስት ግዢ አገልግሎት አሰራር ዙሪያ በተካሄዱ የቁጥጥር ስራዎች የተለዩ ግኝቶችና የመፍትሔ ሃሳቦች ዙሪያ በአዳማ ይፋ በሆነበት መድረክ ላይ ነው፡፡


በሁለቱ ተቋማት አሰራር ዙሪያ ቁጥጥሩን አካሂዶ ግኝቶችን እና ምክረ ሃሳቦችን ለሚመለከታቸው በመድረኩ ይፋ ያደረገው የህዘብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ነው።


በመድረኩ ላይ ሲነገር እንደሠማነው በመንግስት ግዥና ጨረታ የሚሳተፉ አቅራቢዎች በገቡት ውል መሠረት ግዴታቸውን መወጣት ላይ ችግሮች አሉ።


የሚፈለገውን ዕቃ በወቅቱ ያለማቅረብ እና ጥራታቸው የተጓደሉ ምርቶችን ማስረከብ ከችግሮቹ መካከል እንደሆኑ ተነግሯል።


አቅም የሌላቸው አቅራቢዎች በመንግስት ግዢና ጨረታ እንዲሳተፉ የማድረግም ችግር እንዲሁ ተጠቅሷል።


ባሉት ቀነ ገደብ ዕቃዎችን የማያስረክቡ እንዱሉም ተነግሯል።

በወቅቱ በሚያስረክቡት ላይ በውሉ መሠረት እርምጃ ያለ መውሰድ ይታያልም ነዉ የተባለው።


አቅራቢዎችን ለመቆጣጠር ጠንካራ ስርዓት ሊዘረጋ እንደሚገባ የህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በምክረ ሃሳቡ ጠቅሷል።


ንጋቱ ረጋሳ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Recent Posts

See All
ጀማሪ የስራ ፈጣሪዎች ምርቶች እና አገልግሎቶቻቸውን የሚጠቀሙ ሰዎች ጋር ለመድረስ እንደሚቸገሩ ይናገራሉ፡፡

ጥር 14/2018   ጀማሪ የስራ ፈጣሪዎች ምርቶች እና አገልግሎቶቻቸውን የሚጠቀሙ ሰዎች ጋር ለመድረስ እንደሚቸገሩ ይናገራሉ፡፡   ለዚህም ተስማሚ የሽያጭ ቦታ በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት አለመቻል፣ የበጀት እጥረትን ጨምሮ ሌሎች ችግሮች እንደሚያጋጥሟቸው ይሰማል፡፡   ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች የሚገጥማቸውን ችግር ያቀላል፣ ም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page