top of page

ታህሳስ 6፣ 2015- በታለመለት የነዳጅ ድጎማ ስርዓት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮች አፋጣኝ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ተጠየቀ

  • sheger1021fm
  • Dec 15, 2022
  • 1 min read

ree

በታለመለት የነዳጅ ድጎማ ስርዓት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮች አፋጣኝ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ተጠየቀ።


የህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በታለመለት የነዳጅ ድጎማ ስርዓት አፈፃፀም ዙሪያ ያስጠናውን ጥናት ዛሬ በአዳማ ከተማ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ይፋ አድርጓል።


የጥናቱ ውጤት እንዳሳየው የነዳጅ ድጎማ አሰራሩ የተለያዩ ጠንካራ እና ደካማ ውጤቶች ታይተውበታል።


የነዳጅ ብክነትን መቀነሱ እና ተጨማሪ ገቢ ለመንግስት ማስገኘቱ የድጎማ ስርዓቱ ጠንካራ ጎኖች ተብለው ከተነሱት መካከል ናቸው።


የድጎማ አሰራሩ በ1 ወር ብቻ 1 ቢሊየን ብር ግምት ያለው ነዳጅ ከብክነት እንዲድን አግዟል የተባለ ሲሆን ወደ 3.5 ቢሊየን ብር ግምት ያለው ገቢ ለመንግስት አስገኝቷል ተብሏል።


በድጎማ ስርዓቱ አፈፃፀም ዙሪያ ታይተዋል ከተባሉ ችግሮች መካከል ደግሞ አንዳንድ ማደያዎች የነዳጅ እጥረት የተፈጠረ በማስመሰል በህገወጥ መንገድ በእጥፍ ዋጋ ነዳጅ ይሸጣሉ የሚለው ይገኝበታል።


በተሽከርካሪዎች ላይ ያልነበረ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ጋን ወይም ሳልቫቲዮ በመግጠም ድጎማው ለማይመለከተው ወገን ነዳጅ መቅዳት የሚለውም ሌላው ነው።


በአንዳንድ ማደያዎች በቴክኖሎጂ አሰራር ወይም ቴሌ ብር ለመሸጥ ፍላጎት ማጣት ይታያልም ተብሏል።


ስልጣናቸውን ተገን አድርገው ቤተሰቦቻቸውን በህገወጥ የነዳጅ ንግድ የሚያሳትፉ የመንግስት ተሿሚዎች አሉም ነው የተባለው።


በአሽከርካሪዎች በኩል ደግሞ የድጎማ ስርዓቱ ተጠቃሚ ሆነው ለህብረተሰቡ የትራንስፖርት አገልግሎት ከመስጠት ይልቅ በኮንትራት ስራ ላይ የተሠማሩ እንዳሉ ተጠቅሷል።


ነዳጅ በድጎማ እየገዙ በመንግስት ከተቀመጠው ታሪፍ በላይ የሚያስከፍሉ እንዳሉም ተነግሯል።


በነዳጅ ድጎማ አሰራር ዙሪያ የሚታዩ እነዚህ እና መሠል ችግሮች አፋጣኝ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ተጠይቋል፡፡


ንጋቱ ረጋሳ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Recent Posts

See All
ህዳር 25 2018 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሁለት ሚኒስትሮችን እና የአንድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሹመትን አፀደቀ።

ሹመታቸው በምክር ቤቱ የፀደቀላቸው የሠላም ሚኒስትሩ አቶ መሃመድ እድሪስ፤ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቢንያም ኤሮ ናቸው። አቶ መሃመድ እድሪስ የሰላም ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተሹመው  ስራ የጀመሩት ኀዳር 18 ቀን

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page