top of page

ከአርሶ አደሮች እና አቅራቢዎች በፈረሡላ 8,000 እና 9,000 ብር ይገዛ የነበረ ቡና ዋጋ በእጥፍ በመጨመሩ ላኪዎች እየተቸገሩ ነው ተባለ።

  • sheger1021fm
  • 53 minutes ago
  • 1 min read

ህዳር 25 2018

 

ከአርሶ አደሮች እና አቅራቢዎች በፈረሡላ 8,000 እና 9,000 ብር ይገዛ የነበረ ቡና ዋጋ በእጥፍ በመጨመሩ ላኪዎች እየተቸገሩ ነው ተባለ።

 

ላኪዎች በዚህ ዋጋ ቡና እየገዙ ለአለም ገበያ ማቅረብ እንደሚከብዳቸው የኢትዮጵያ ቡና ማህበር ተናግሯል።

 

አርሶ አደሮች እና ላኪዎች ዋጋውን ከፍ ያደረጉት ወደፊት ይበልጥ ይጨምራል በሚል ግምት እንደሆነም ማህበሩ ጠቅሷል።

 

ወደ ውጪ ቡና የሚልኩ ነጋዴዎች ከአርሶ አደሮች እና አቅራቢዎች ምርቱን የሚገዙበት ዋጋ ከተወሰነ ጊዜ ወዲህ ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን የኢትዮጵያ ቡና ማህበር ተናግሯል፡፡

 

የማህበሩ ዋና ስራ አስኪያጅ ግዛት ወርቁ እንዳሉት ቀደም ሲል በፈረሱላ ስምንት ሺህ እና ዘጠኝ ሺህ ብር ከአርሶ አደሮችና አቅራቢዎች ይገዛ የነበረ ቡና አሁን በፈረሱላ እስከ ሃያ ሺህ ብር እየተባለ ነው፡፡

 

አንድ ፈረሱላ ቡና በሃያ ሺህ ብር ገዝቶ ወደ ለውጪ ገበያ ማቅረብ ለላኪዎች ከባድ ነው ብለዋል፡፡

 

አርሶ አደሮች እና አቅራቢዎች ዋጋ እየጨመሩ ያሉት ወደፊት ይበልጥ መሸጫው ከፍ ይላል በሚል ግምት እንደሆነ አቶ ግዛት ተናግረዋል።

 

አሁን ያለው የአለም አቀፍ ቡና መሸጫ ግን ዋጋው እንደሚጨመር ሳይሆን እንደሚቀንስ የሚያመለክት ነው ብለዋል።

 

ላኪዎች ከአርሶ አደሮች እና አቅራቢዎች ቡናን የሚገዘቡት ዋጋ ካልተስተካከለ ምርቱን ለአለም ገበያ ማቅረብ አስቸጋሪ ይሆናል ሲሉ አቶ ግዛት ስጋታቸውን ተናግረዋል።

 

ቡና ደግሞ ለኢትዮጵያ ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሪ የሚያስገኝ ምርት በመሆኑ ነገሩ እንደ ቀላል ሊታይ የሚችል አይደለም ሲሉ አክለዋል።

 

ችግሩን ለመፍታት መንግስት መመሪያ ማውጣት ይችላል ያሉት አቶ ግዛት ለላኪዎች ማበረታቻዎችን ማቅረብም ሌላው አማራጭ እንደሆነ ጥቅሰዋል።

 

ዋጋው አሁን ባለበት የሚቀጥል ከሆነ ኢትዮጵያ የምታገኘው ገቢ ብቻ ሳይሆን ወደ ውጪ የምትልከው ቡና መጠንም እንደሚቀንስ አቶ ግዛት ተናግረዋል።

 

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…

ንጋቱ ረጋሣ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇

Recent Posts

See All
ህዳር 25 2018 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሁለት ሚኒስትሮችን እና የአንድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሹመትን አፀደቀ።

ሹመታቸው በምክር ቤቱ የፀደቀላቸው የሠላም ሚኒስትሩ አቶ መሃመድ እድሪስ፤ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቢንያም ኤሮ ናቸው። አቶ መሃመድ እድሪስ የሰላም ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተሹመው  ስራ የጀመሩት ኀዳር 18 ቀን

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page