ህዳር 25 2018 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሁለት ሚኒስትሮችን እና የአንድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሹመትን አፀደቀ።
- sheger1021fm
- 12 minutes ago
- 1 min read
ሹመታቸው በምክር ቤቱ የፀደቀላቸው የሠላም ሚኒስትሩ አቶ መሃመድ እድሪስ፤ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቢንያም ኤሮ ናቸው።
አቶ መሃመድ እድሪስ የሰላም ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተሹመው ስራ የጀመሩት ኀዳር 18 ቀን 2017 ዓ.ም እንደነበር ይታወሳል።
አቶ አዲሱ አረጋ ደግሞ ሐምሌ 25/ 2017 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትሩ የግብርና ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል፡፡
አንድ የምክር ቤቱ አባል በተለይ የሠላም ሚኒስትሩ አቶ መሃመድ እድሪስ ከተሾሙ ዓመት እንዳለፋቸው በመጥቀስ ሹመቱ እስከ አሁን በምክር ቤቱ ሳይጸድቅ መቆየቱ አግባብ ነው ወይ? የሚል ጥያቄ አንስተዋል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሠ ጫፎ በሰጡት ምላሽ በተለያዩ ምክንያቶች ሹመቱ በምክር ቤቱ ሳይፀድቅ መቆየቱን ተናግረው ማሳሰቢያውን ግን ተቀብለናል ብለዋል።
ምክር ቤቱም የሁለቱን ሚኒስትሮችን እና የስራ አስፈጻሚውን ሹመት በሙሉ ድምጽ አፅድቆታል።
ተሿሚዎቹም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት አማካይነት ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።
ንጋቱ ረጋሣ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp https://tinyurl.com/ycxjmm3s












Comments