top of page

ታህሳስ 3፣ 2015- አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ በ2014 በጀት ዓመት የተጣራ 344.9 ሚሊዮን ብር ማትረፉን ተናገረ

  • sheger1021fm
  • Dec 12, 2022
  • 1 min read

Updated: Dec 13, 2022


ree

ታህሳስ 3፣ 2015


አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ በ2014 በጀት ዓመት የተጣራ 344.9 ሚሊዮን ብር ማትረፉን ተናገረ፡፡


ትርፉ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ27.1 በመቶ ዕድገት አሳይቷል ተብሏል።


ባንኩ ይህን ትርፍ ያገኘሁት በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ባጋጠመው ጦርነት እና የፖለቲካ አለመረጋጋት፣ የኮረና ወረርሽኝ፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ንረት እና ሌሎች ተፅዕኖዎችን ተቋቁሜ ነው ብሏል፡፡


ባንኩ በበጀት ዓመቱ 1.5 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን የተናገረ ሲሆን፤ ይህም ባለፈው ዓመት ከተገኘው ጋር ሲነፃፀር የ32 በመቶ ወይንም የ365 ሚሊዮን ብር ዕድገት አሳይቷል ሲል በሪፖርቱ ተናግሯል።


አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ ለደምበኞቹ የሰጠው አጠቃላይ ብድር 6.1 ቢሊዮን ብር ደርሷል ብሏል።


ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የብር 1.6 ቢሊዮን ብር ወይም የ35 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን ጠቅሷል፡፡

ከፍተኛው ብድር የተሰጠው ለውጭ ንግድ ሲሆን 47 በመቶ ድርሻ ይይዛል ብሏል፡፡


የሀገር ውስጥ ንግድና አገልግሎት 19 በመቶ፣ ኮንስትራክሽን 15 በመቶ፣ ማምረቻ 8 በመቶ፣ የገቢ ንግድ 6 በመቶ በመያዝ ሌሎች ተበዳሪ ዘርፎች መሆናቸውን ከሪፖርቱ ተመልክተናል፡፡


ባንኩ በሂሳብ ዓመቱ መጨረሻ በደምበኞች እጅ ከሚገኘው ብድር ውስጥ 96.8 በመቶ ጤናማ ብድር ነው ያለ ሲሆን የተበላሸ ብድር 3.2 በመቶ ነው ይህም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ካስቀመጠው 5 በመቶ መስፈርት በታች መሆኑን አስረድቷል።


ጠቅላላ ሀብቴ 10.8 ቢሊዮን ብር፣ አጠቃላይ ካፒታሌ ድግሞ 2.2 ቢሊዮን ብር ደርሶልኛል ብሏል፡፡


ብንኩ ማህበራዊ ኃላፊነትን ለመወጣት በሰሜኑ ጦርነት ጉዳት ለደረሰባቸው 3 ሚሊዮን ብር፤ ለተስፋ አዲስ የህጻናት ካንሰር ህሙማን መረጃ ማእከል 60 ሺ ብር ድጋፍ ማድረጉን ተናግሯል፡፡


እንዲሁም የውጭ ሀገራት ገንዘቦችን ደንበኞች በባንኩ በኩል ሲቀበሉ እና ሲመነዝሩ ከተገኘው ገቢ 1.5 ሚሊዮን ብር ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ሰጥቻለሁ ብሏል፡፡


ንጋቱ ሙሉ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Recent Posts

See All
ህዳር 25 2018 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሁለት ሚኒስትሮችን እና የአንድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሹመትን አፀደቀ።

ሹመታቸው በምክር ቤቱ የፀደቀላቸው የሠላም ሚኒስትሩ አቶ መሃመድ እድሪስ፤ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቢንያም ኤሮ ናቸው። አቶ መሃመድ እድሪስ የሰላም ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተሹመው  ስራ የጀመሩት ኀዳር 18 ቀን

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page