top of page

ሚያዝያ 24፣2016 - የእስራኤል ፍልስጤም ጦርነት ወደ ውጪ በሚላክ የኢትዮጵያ አትክልትና ፍራፍሬ ምርት ላይ ተጽዕኖውን እያሳረፈ ነው ተባለ

  • May 2, 2024
  • 2 min read

የእስራኤል ፍልስጤም ጦርነት ወደ ውጪ በሚላክ የኢትዮጵያ አትክልትና ፍራፍሬ ምርት ላይ ተጽዕኖውን እያሳረፈ ነው ተባለ።


ጦርነቱ ምርቶቹን ለሚያጓጉዙ የመርከብ ኩባንያዎች የሚፈጸመውን ክፍያ በትንሹ ከሁለት ሺህ ዶላር በላይ እንዲጨምር ማድረጉ ተነግሯል።


የምርቶቹ የማስረከቢያ ጊዜ እንዲራዘም እያስገደደ ነውም ብሏል የኢትዮጵያ አትክልት፤ ፍራፍሬ ፤ ስራ ስር እና መዓዛማ ውጤቶች አምራቾችና ላኪዎች ማኅበር።


ኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ከምታገኝባቸው ምርቶች መካከል አበባ ፤ አትክልት፤ ፍራፍሬ ፤ ስራ ስር እና መዓዛማ የሆኑ ውጤቶች ይገኙበታል።


ይህ ዘርፍ ከቡና ቀጥሎ ለኢትዮጵያ ዶላር በማምጣት በሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚቀመጥ ነው።


በ2016 በጀት አመት ስምንት ወራት ያለውን አፈጻጸም እንኳን ስናይ ከ310 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ በማስገኘት በዚሁ ደረጃው ላይ ተቀምጧል።


በስምንት ወራቱ ቡና ከ715 ሚሊየን ዶላር በላይ በማስገባት ቀዳሚው ነው።

ከተቀሰቀሰ ወራትን ያስቆጠረው የእስራኤል ፍልስጤም ጦርነት ግን በተለይ፤ የአትክልትና ፍራፍሬ ፤ ስራ ስር እና መዓዛማ የሆኑ ውጤቶችን ንግድ እየፈተነው ነው ተብሏል።


ምርቶቹን የሚያጓጉዙ የመርከብ ኩባንያዎች ቀይ ባህርን በመተው በደቡብ አፍሪካ በኩል ዞረው እንዲሄዱ ነው ሲሉ ፤የኢትዮጵያ አትክልት፤ ፍራፍሬ ፤ ስራ ስር እና መዓዛማ ውጤቶች አምራቾችና ላኪዎች ማኅበር ዋና ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ ዘውዴ ተናግረዋል።

በችግሩ ምክንያት የምርት ማጓጓዣ ኮንቴነሮች እጥረት አጋጥሟል የሚሉት አቶ ቴዎድሮስ ፤ የመርከቦች የቆይታ ጊዜ መራዘሙን እና የማጓጓዣ ክፍያውም በትንሹ ከሁለት ሺህ ዶላር በላይ መጨመሩን አክለዋል።

የአበባ ምርት ግን አሁንም ድረስ ወደ ገዥ አገራት የሚላከው በአውሮፕላን ነው፡፡


ከአበባ፣ አትክልት፣ ፍራፍሬ፣ ስራ ስር እና መዓዛማ ምርቶች አበባ አሁንም ከፍ ያለውን ገቢ በማምጣት ቀዳሚው መሆኑ ተነግሯል።


አትክልት ብቻውን ተለይቶ ሲታይ ደግሞ ድርሻው ከ15 በመቶ በታች እንደሆነ ከዋና ዳይሬክተሩ ሠምተናል።


ኢትዮጵያ ግን ለአትክልት ልማት የተመቸ ተፈጥሮ እና ምቹ ዕድል አላት ብለዋል።


ለልማቱ የሚያስፈልጉ ግብአቶችን ማሟላት እና ተቀናጅቶ መስራት ኢትዮጵያ ከአትክልት የምታገኘውን ገቢ ያሳድጋሉ ከተባሉ የመፍትሄ ሃሳቦች መካከል ናቸው፡፡


ኔዘርላንድስ፣ እንግሊዝ፣ ጀርመን እና ጣሊያን የኢትዮጵያን የአበባ፣ አትክልት፣ ፍራፍሬ ፣ ስራ ስር እና መዓዛማ ምርቶች ከሚገዙ ሀገራት መካከል ናቸው፡፡


አሜሪካ፣ ካናዳ፣ ጃፓን፣ ኮሪያ እና አውስትራሊያም ሌሎቹ እንደሆኑ ሠምተናል።


ንጋቱ ረጋሣ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Recent Posts

See All
በኢትዮጵያ እያንዳንዱ ብሄረሰብ የራሱን ታሪክ ብቻ ለይቶና አጉልቶ የሚያቀርብበት ስርዐት መቀየር እንዳለበት የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ተናገሩ ።

ሐምሌ 23 2018 በኢትዮጵያ እያንዳንዱ ብሄረሰብ የራሱን ታሪክ ብቻ ለይቶና አጉልቶ የሚያቀርብበት ስርዐት መቀየር እንዳለበት የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ተናገሩ ። በኢትዮጵያ የብሄረሰቦች ታሪክ ጥልቅ ትስስር እና መስተጋብር ያለው ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የታሪክ ባለሞያዎች ማህበር ከላይፍ ኤንድ ፒስ ኢንስ

 
 
 
በ2018 በጀት ዓመት ከ1.2 ቢሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

ሐምሌ 23 2018 በ2018 በጀት ዓመት ከ1.2 ቢሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። በየዓመቱ በሀገሪቱ የሚገኘው የምርት መጠን እያደገ እንደሚመጣ ሪፖርቶች ያመልክታሉ። በገበያው ውስጥ ግን የምርት ዋጋ ከአመት አመት እየጨመረ እንጂ ሲቀንስም አይታይም። ይህ ለምን ሆነ? እውነትስ

 
 
 
እድሜያቸው ከ14 እስከ 24 የሆኑ አፍላ ወጣቶች በተለይም ሴቶች ላይ እየታየ ያለው የኤች አይ ቪኤድስ ስርጭት በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ መምጣቱን፣ ይህም ከፍተኛ ትኩረትእንደሚያስፈልገው ኔፕ ፕላስ (NEP+) የተባለ ድርጅት ተናገረ።

ሐምሌ 23 2018 እድሜያቸው ከ14 እስከ 24 የሆኑ አፍላ ወጣቶች በተለይም ሴቶች ላይ እየታየ ያለው የኤች አይ ቪኤድስ ስርጭት በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ መምጣቱን፣ ይህም ከፍተኛ ትኩረትእንደሚያስፈልገው ኔፕ ፕላስ (NEP+) የተባለ ድርጅት ተናገረ። Network of Networks of HIV Positives in

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page