top of page

መጋቢት 19፣2016 - ''የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በተወሰኑ የአማራ አካባቢዎች ላይ ትንኮሳ ጀምሯል'' የአማራ ክልል

  • Mar 28, 2024
  • 1 min read

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በተወሰኑ የአማራ አካባቢዎች ላይ ትንኮሳ ጀምሯል ሲል ዛሬ የአማራ ክልል ባወጣው መግለጫ ተናገረ፡፡


ከቀናት በፊት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የአማራ ክልል በተማሪዎች የመማሪያ መፅሐፍት የትግራይ ክልልን ቦታዎች የራሱ አስመስሎ በካርታው በማካተት እያስተማረበት ነው ሲል መክሰሱ ይታወሳል፡፡


በዚሁ መግለጫው የአማራ ክልል ማስተካከያ የማያደርግ ከሆነ ለሚፈጠረው ችግር ሀላፊነቱን ይወስዳል ማለቱም ይታወሳል፡፡


የአማራ ክልል በበኩሉ ጊዜአዊ አስተዳደሩ የመማሪያ መፅሐፍትን በማጣቀስ ያወጣው መግለጫ ዛቻና ፀብ አጫሪነት ሲል ገልጾታል፡፡


በተጨማሪም ወደ አማራ ክልል ካርታ ተካቷል ያላቸውን ስፍራዎች የሚገኙ ህዝቦችን ታሪካዊ እውነታና ተጨባጭ ማስረጃዎችን እንዲሁም ነባራዊ አቅን የካደ አሳሳች መግለጫ ሲልም ገልፆታል፡፡


ሁለቱ ክልሎች በይገባኛል የሚወዛገቡባቸው ቦታዎች መኖራቸው የሚታወቅ ነው፡፡



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
የነሐሴ 4 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሳውዲ_አረቢያ በሳውዲ አረቢያ ጂዛን በሚገኝ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ከባድ ቃጠሎ ተቅስቅሶ ነበር ተባለ፡፡ በጂዛኑ ማጣሪያ ላይ ቃጠሎ ተቅስቅሶ የነበረው ከባድ ፍንዳታ ከተሰማ በኋላ እንደሆነ አናዶሉ ፅፏል፡፡ በጁቢየል የተፈጥሮ ጋዝ ማሰናጃ ከተማም ቃጠሎ ተቀስቅሶ ነበር ተብሏል፡፡ የሳውዲ ምንጮች ቃጠሎዎቹ ተቀስቅሰው እ

 
 
 
በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡

ነሐሴ 4 2018 በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት በበኩሉ ሳያጠፋ የምንቀጣው አሽከርካሪ የለም እንዲያውም ሁሉንም ህጎች እናስከብር ብንል የማይቀጣ አሽከርካሪ አይኖርም ብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ.... ምህረት ስዩም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page