top of page

መጋቢት 18፣2016 - "የኛ ማይክሮ ፋይናንስ" ለሴቶች፣ ለአካል ጉዳተኞች እና ወጣቶች በልዩ ሁኔታ ብድር እየሰጠ መሆኑን ተናገረ

  • Mar 27, 2024
  • 1 min read

የዛሬ ሁለት ዓመት ስራ የጀመረው "የኛ ማይክሮ ፋይናንስ" ለሴቶች፣ ለአካል ጉዳተኞች እና ወጣቶች በልዩ ሁኔታ ብድር እየሰጠ መሆኑን ተናገረ።


ከብት ለሚያደልቡ፣ ንብ ለሚያንቡ የከተማ ግብርና ላይ ለተሰማሩም በልዩ የብድር መንገድ ይስተናገዳሉ ተብሏል።


ለሴቶች፣ ለወጣቶች እና አካል ጉዳተኞች የሚሰጠው ብድር ከሌሎች አይነቶች ዝቅተኛ ወለድ የሚሰላበት እንዲሁም ንግድ ፍቃድ ባይኖራቸውም ተበዳሪዎቹ ስራቸውን በትክክል እየሰሩ መሆናቸው ከተረጋገጠ ብድር ይሰጣቸዋል ሲሉ የድርጅቱ የኦፕሬሽን ዘርፍ ተጠባባቂ ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ ደራሽ በሀይሉ ለሸገር ነግረዋል።


የኛ ማይክሮ ፋይናንስ በሁለት ዓመት ቆይታው ለ500 ሰዎች ብድር ሰጥቻለሁ፣ ከ10,000 በላይ የቆጠቡ ደንበኞችም አሉኝ ብሏል።


ድርጅቱ በ40 ሚሊዮን ብር የተፈረመ ካፒታል እና በ10 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል የተቋቋመ ሲሆን አሁን ላይ የተከፈለ ካፒታሉ 160 ሚሊዮን ብር መድረሱን ሰምተናል።


የኛ ማይክሮ ፋይናንስ በሳምንት ሰባቱንም ቀናት እሰራለሁ፣ ለቀረበልኝ የብድር ጥያቄም መስፈርቱን ካሟላ አንድ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ብድር እለቃለሁ ብሏል።


በአዲስ አበባ 3 ቅርንጫፎች እንዳሉት የተናገረው ድርጅቱ ወደ ክልልም ለማስፋት የአዋጭነት ጥናቱ እያለቀ መሆኑን አስረድቷል።



ንጋቱ ሙሉ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
የነሐሴ 4 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሳውዲ_አረቢያ በሳውዲ አረቢያ ጂዛን በሚገኝ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ከባድ ቃጠሎ ተቅስቅሶ ነበር ተባለ፡፡ በጂዛኑ ማጣሪያ ላይ ቃጠሎ ተቅስቅሶ የነበረው ከባድ ፍንዳታ ከተሰማ በኋላ እንደሆነ አናዶሉ ፅፏል፡፡ በጁቢየል የተፈጥሮ ጋዝ ማሰናጃ ከተማም ቃጠሎ ተቀስቅሶ ነበር ተብሏል፡፡ የሳውዲ ምንጮች ቃጠሎዎቹ ተቀስቅሰው እ

 
 
 
በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡

ነሐሴ 4 2018 በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት በበኩሉ ሳያጠፋ የምንቀጣው አሽከርካሪ የለም እንዲያውም ሁሉንም ህጎች እናስከብር ብንል የማይቀጣ አሽከርካሪ አይኖርም ብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ.... ምህረት ስዩም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page