top of page

መጋቢት 17፣2016 - የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ም/ቤት አባላቱ የሚገጥማቸውን ችግር ያቃልላል ያለውን የዲጂታል ስርዓት ይፋ አደረገ

  • Mar 26, 2024
  • 1 min read

የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት በአለም አቀፍ ንግድ ላይ የተሠማሩ አባላቱ የሚገጥማቸውን ችግር ያቃልላል ያለውን የዲጂታል ስርዓት ይፋ አደረገ።

 

የዲጂታል ስርዓቱ በአለም አቀፍ ንግድ ለተሰማሩ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት የገበያ መዳረሻዎችን እና ህጎችን የተመለከቱ መረጃዎችን የሚሰጥ መሆኑ ተጠቅሷል።

 

የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት 17 ሺህ አባላት አንዳሉት የተናገሩት የምክር ቤቱ ዋና ፀሃፊ አቶ ሺበሺ ቤተማርያም፤ ከእነዚህ መካከል ከ10 ሺህ የሚበልጡት በአለም አቀፍ ንግድ የተሰማሩ ናቸው ብለዋል።

 

ከእነዚህ ከ10 ሺህ የሚበልጡት የምክር ቤቱ አባላት፤ 76 በመቶዎቹ ላኪዎች እንደሆኑ አቶ ሺበሺ ተናግረዋል።

 

22.6 በመቶዎቹ ደግሞ አስመጪዎች ናቸው ብለዋል።

 

በአለም አቀፍ ንግድ የተሠማሩት አነዚህ የምክር ቤቱ አባላት በርከት ያሉ ችግሮች እንደሚገጥሟቸው ዋና ፀሃፊው ተናግረዋል።

 

ስለ ውጪ ገበያ በቂ ግንዛቤ አለመኖር እና የመረጃ እጥረት ከእነዚህ መካከል እንደሆኑ ጠቅሰዋል።

 

ችግሮቹን ለመፍታት የዲጂታል ፖርታል ከGIZ ጋር በመተባበር ምክር ቤቱ አዘጋጅቷል ብለዋል ።

 

በዚህም በአለም አቀፍ ንግድ ላይ የተሠማሩ የምክር ቤት አባላት በውጪ ስላሉ የገበያ ዕድሎች በቀላሉ ማወቅ እንደሚችሉ ተጠቅሷል።

 

ስለ ገዥ ሀገራት ህጎችና የጥራት መስፈርቶችም እንዲሁ መረጃ ይኖራቸዋል ተብሏል።

 

ምክር ቤቱ በአለም አቀፍ ንግድ የተሰማሩ አባላቱን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ተጨማሪ ስራዎችን ወደፊትም እንደሚሰራ ዛሬ ከሰአት በኋላ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ሲናገር ተገኝተን ሠምተናል፡፡

 

ንጋቱ ረጋሳ

 


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

 

 

Recent Posts

See All
የሐምሌ 24 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ኮንጎ በኮንጎ ኪንሻሣ በኢቦላ የሚያዙ ሕሙማንና ወረርሽኙ የሚገድላቸው ሰዎች ብዛት በጣሙን እየጨመረ ነው ተባለ፡፡ በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጠው ሰዎች ብዛት ከ3 ሺህ 400 መብለጡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ወረርሽኙ የገደላቸው ሰዎች ብዛት ከ1 ሺህ 500 በላይ መድረሱ ተነግሯል፡፡ በአገሪቱ በኢቦላ በሽታ የሚያዙ ሰዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page