top of page

መጋቢት 14፣2016 - ዛሬ ማለዳ በእንጦጦ ጋራ ስር የመሬት መንቀጥቀጥ አጋጥሞ ነበር ተባለ

  • Mar 23, 2024
  • 1 min read

ከጥዋቱ 1 ሰዓት ከ45 ደቂቃ 25 ሰኮንድ የቆየ የመሬት መንቀጥቀጥ በእንጦጦ ጋራ ስር ማጋጠሙን ሰምተናል።

የመሬት መንቀጥቀጡ በርዕደ መርት መለኪያ(በሬክትር ልኬት )2.0 ሆኖ መመዝገቡን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ  የስፔስ ሳይንስ እና አስትሮኖሚ ተቋም ሀላፊ ፕሮፈሰር አታላይ አየለ ለሸገር ነግረዋል።


ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ እና ፉሪ ተራራ ሥር በሚገኙ መሣሪያዎች የተመዘገበ መሆኑ ተነግሯል።


የመሬት መንቀጥቀጡ የተፈጠረው 9.1113 ኬክሮስና 38.753 ኬንትሮስ መስመሮች በሚገናኙበት ነጥብ ላይ ያረፈ ሲሆን ይህም በእንጦጦ ጋር ስር መሆኑን ማወቅ ተችሏል ተብሏል።


በሰሜን አዲስ አበባ በተለይም ፎቅ ላይ ያሉ ነዋሪዎች ንዝረቱን መስማታቸውን አስረድተዋል።


የመሬት መንቀጥቀጡ ጉዳት የማድረስ አቅሙ በጣም ዝቅተኛ መሆኑንም ፕሮፈሰር አታላይ ነግረውናል።


ንጋቱ ሙሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
ከህዳሴ ግድብ ከ11 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ዓሣ ተመረተ፡፡

ሐምሌ 21 2018 ከህዳሴ ግድብ ከ11 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ዓሣ ተመረተ፡፡ የዓሣ ምርቱ ወደ መሃል ሃገር እየተጫነ ለአዲስ አበባ ገበያ እየቀረበ ነውም ተብሏል፡፡ ታላቁ የህዳሴ ግድብ መገንባቱን ተከትሎ በተፈጠረው ንጋት ሰው ሰራሽ ሃይቅ በኢትዮጵያ ትልቁና ከ70 በላይ ደሴቶች ያሉት የውሃ አካል ነው፡፡ ከቅርብ

 
 
 
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 30.65 ቢሊዮን ዶላር የሚጠይቅ የኃይል ማስፋፊያ ዕቅድ ይፋ አደረገ።

ሐምሌ 20 2018 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 30.65 ቢሊዮን ዶላር የሚጠይቅ የኃይል ማስፋፊያ ዕቅድ ይፋ አደረገ። እቅዱ የኔትወርክ ማሻሻያ እና ማስፋፊያ፣ የሰብስቴሽን እና ተያያዥ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች፣ ስማርት ግሪድ እና ቆጣሪ ማስፋፋትን እንደሚያካትት አገልግሎቱ ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page