top of page

መጋቢት 11፣2016 - የባህር ማዶ ወሬዎች

  • Mar 20, 2024
  • 2 min read


የአውሮፓ ህብረት አባሎች በየአገሮቻቸው ታግዶ የሚገኝን የሩሲያ ገንዘብ ለዩክሬይን የጦር መሳሪያ መግዣ ሊያውሉት ነው ተባለ፡፡


በጉዳዩ ላይ የህብረቱ አባል አገሮች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ነገ ተሰብስበው እንደሚመክሩበት አሶሼትድ ፕሬስ ፅፏል፡፡


በአውሮፓ ህብረት አባል አገሮች ታግዶ የሚገኘው የሩሲያ ገንዘብ 200 ቢሊዮን ዩሮ ያህል እንደሆነ ይገመታል፡፡


የህብረቱ የውጭ ጉዳይ ሀላፊ ጆሴፍ ቦሬል ታግዶ የሚገኘውን የሩሲያ ገንዘብ ለዩክሬይን የጦር መሳሪያ መግዣ ማዋላችን አይቀሬ ነው ማለታቸው ተሰምቷል፡፡


ዩክሬይን በአሁኑ ወቅት የጦር መሳሪያ እና የተተኳሾች እጥረት እንደገጠማት ይነገራል፡፡




የኬንያ ሰራተኞች ለድሆች እና ባለዝቅተኛ ገቢዎች ቤት መገንቢያ የ 1.5 በመቶ ተጨማሪ ግብር ሊከፍሉ ነው፡፡


ፕሬዘዳንት ዊሊያም ሩቶ ሕጉ ስራ ላይ እንዲውል ፊርማቸውን እንዳኖሩበት ቢቢሲ ፅፏል፡፡


ከተጨማሪ የግብር ክፍያው የሚሰበሰበው ገቢ ለድሃ እና ባለ ዝቅተኛ ገቢ ኬንያውያን የመኖሪያ ቤት መገንቢያ ይውላል ተብሏል፡፡


ይሁንና አዲሱ የግብር ክፍያ በተቃዋሚዎች እና በብዙ ግብር ከፋዮች እየተነቀፈ መሆኑ ታውቋል፡፡


ይሁንና ይሄ የግብር ዓይነት መደበኛ ባልሆነው ዘርፍ ከሚገኙ ሰራተኞች እንዴት እንደሚሰበሰብ ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም፡፡


የቤት መገንቢያውን ገንዘብ የሚያስተዳድር መስሪያ ቤት እንደሚቋቋም ተጠቅሷል፡፡



የፀጥታው ምክር ቤት የየመን ሁቲዎች በቀይ ባህር ተላላፊ መርከቦች ላይ የሚፈፅሙትን ጥቃት ያለ አንዳች መዘግየት እንዲያቆሙ ጠየቃቸው፡፡


ድርጊታቸውንም እንዳወገዘው አረብ ኒውስ ፅፏል፡፡


ሁቲዎቹ እስራኤል የጋዛ የጦር ዘመቻዋን ካላቆመች በተባባሪዎቿ መርከቦች ላይ ጥቃታችንን አናቆምም ባዮች ናቸው፡፡


መርከብ መትተው እስከ ማስጠም ደርሰዋል፡፡


ምክር ቤቱ ቀደም ሲል የሁቲዎቹ ጥቃት እንዲቆም ውሳኔ ማሳለፉን ዘገባው አስታውሷል፡፡


ሁቲዎቹ የምክር ቤቱን ውሳኔ እንዲያከብሩ ተጠይቀዋል፡፡


የቀይ ባህሩ ቀውስ ያለ ሁነኛ መፍትሄ እንደዘለቀ ነው ተብሏል፡፡


የየመንን ሰሜናዊ ክፍል የሚያስተዳድሩት ሁቲዎቹ የኢራን ሁነኛ የጦር እና የፖለቲካ አጋሮች ተደርገው ይቆጠራሉ፡፡



የደቡብ አፍሪካ ፓርላማ አፈ ጉባኤው ኖሶቪዌ ማፒሣ ንካኩላ መኖሪያ ቤት በአገሪቱ ልዩ ፖሊስ መፈተሸ ተሰማ፡፡


የአፈ ጉባኤዋ የጆሃንስበርግ መኖሪያ ቤት የተበረበረው የአገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት ፈፅመውታል በተባለው ምዝበራ ምክንያት እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡


ንካኩላ የመከላከያ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት ባልተገባ ሁኔታ ለተሰጠ መንግስታዊ ኮንትራት ጉቦ ተቀብለዋል ተብለው ስማቸው በክፉ እየተነሳ መሆኑ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡


ፖሊስ በመኖሪያ ቤታቸው ብርበራ ያደረገው በአቃቤ ህግ ጥያቄ መሰረት ነው ተብሏል፡፡


ንካኩላ የመከላከያ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት አንድ የትራንስፖርት ኩባንያ ወታደራዊ ቁሳቁሶችን እንዲያጓጉዝ ባልተገባ ሁኔታ ጨረታውን እንዲያሸንፍ ላደረጉበት የ120 ሺህ ዶላር ጉቦ ተቀብለዋል እየተባለ ነው፡፡


የኔነህ ከበደ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
የሐምሌ 23 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ግብፅ በግብፅ የሜዴትራኒያን የባህር ዳርቻ የነበረ የአሜሪካ የጋዝ ማጠራቀሚያ መርከብ በድሮን ተመታ ተባለ፡፡ ሁለት የደህንነት ምንጮች መርከቡ በድሮን እንደተመታ አረጋግጠውልኛል ሲል ሬውተርስ ፅፏል፡፡ መርከቡ በድሮን እንደተመታ በእሳት መያያዙ ታውቋል፡፡ ቃጠሎው ወደ ሌላ መርከብም ተጋብቶ ነበር ተብሏል፡፡ ኋላ ግን

 
 
 
የሐምሌ 22 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#አሜሪካ አሜሪካ እና ሳውዲ አረቢያ ኢራቅ ውስጥ በአፍቃሪ ኢራን ታጣቂዎች ይዞታ ላይ ድብደባ ፈፀሙ፡፡ ሰሞኑን ሳውዲ አረቢያ በኢራቅ የሚገኙ አፍቃሪ ኢራን ታጣቂዎች በድሮን ጥቃት አድርሰውብኛል ስትል እንደነበር አልጀዚራ አስታውሷል፡፡ ሳውዲ ጥቃቱን ከማውገዝ በተጨማሪ መበቀሌ አይቀርም በሚል ዝታ ነበር፡፡ በኢራቆቹ አ

 
 
 
የሐምሌ 21 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ጃፓን የጃፓን ደቡባዊ ምዕራብ ክፍል በርዕደ መሬት ተመታ፡፡ ርዕደ መሬቱ የደረሰው ኩማማቶ የተባለው የአገሪቱ ክፍል እንደሆነ ኒኪ እስያ ፅፏል፡፡ የመሬት ነውጡ የተቀሰቀሰው ከምድር በ10 ኪሎ ሜትር ጥልቀት መሆኑ ታውቋል፡፡ ነውጡ በርዕደ መሬት መለኪያ /ሬክተር ስኬል/ 7 ነጥብ 1 ሆኖ መመዝገቡ ታውቋል፡፡ ቀደም ሲ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page